uz
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Assaye Derbie analitikasi

Assaye Derbie (@asayede) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 346 obunachidan iborat bo'lib, Bloglar toifasida 2 649-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 354-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 346 obunachiga ega bo‘ldi.

24 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -112 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 39.43% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 12.21% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 656 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 752 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 33 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Kanal uchun tavsif kiritilmagan.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 25 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Bloglar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

14 346
Obunachilar
-724 soatlar
-387 kunlar
-11230 kunlar
Postlar arxiv
"ሕዝባችን ጦርነት ሰልችቶታል" በማለቱ የተነሳ በእነ ናትናኤል መኮነንና ሙክታሮቢች ትዕዛዝ ወደ እስር ቤት የተወረወረ ወንድማችንን ፍቱት።
"ሕዝባችን ጦርነት ሰልችቶታል" በማለቱ የተነሳ በእነ ናትናኤል መኮነንና ሙክታሮቢች ትዕዛዝ ወደ እስር ቤት የተወረወረ ወንድማችንን ፍቱት።

ከእነ ቀለጠ የበሰበሰ መንጋጋ አብንን መንግጎ ማውጣት የኔ፣ ያንተ፣ ያንቺ ግዴታ ነው። የአምሳ ሚሊዮን ሕዝብ ድርጅት አምስት በማይሞሉ ኅሊና ቢሶች ሊዳከም የቻለው በእነሱ ብርታት ሳይሆን በእኛ ድከመ
ከእነ ቀለጠ የበሰበሰ መንጋጋ አብንን መንግጎ ማውጣት የኔ፣ ያንተ፣ ያንቺ ግዴታ ነው። የአምሳ ሚሊዮን ሕዝብ ድርጅት አምስት በማይሞሉ ኅሊና ቢሶች ሊዳከም የቻለው በእነሱ ብርታት ሳይሆን በእኛ ድከመት ነው።

ተደራዳሪ ቡድኑ ደቡብ አፍሪካ ሄዶ በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ ይጨቃጨቃል። ጠሚው ከስንዴ ማሳ መሀከል ቁሞ "ህውሓት እራሱ የጻፈውን ሕገ መንግሥት ካከበረ የክልሉ አስተዳዳሪ ሁኖ ይቀጥላል" የሚል ውሳ
ተደራዳሪ ቡድኑ ደቡብ አፍሪካ ሄዶ በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ ይጨቃጨቃል። ጠሚው ከስንዴ ማሳ መሀከል ቁሞ "ህውሓት እራሱ የጻፈውን ሕገ መንግሥት ካከበረ የክልሉ አስተዳዳሪ ሁኖ ይቀጥላል" የሚል ውሳኔ ያስተላልፋል። 😆

አማራን አንድ የሚያደርጉ፣ አማራነትን ከፍ የሚያደርጉ መሪዎች እንፈልጋለን። አማራን የሚበትን አስተሳሰብ ይዘው በአመራርነት የተቀመጡ ኃይሎችም መልቀቅ አለባቸው። በብሄር ከፋፍለው ሲያባሉን የነበሩት
አማራን አንድ የሚያደርጉ፣ አማራነትን ከፍ የሚያደርጉ መሪዎች እንፈልጋለን። አማራን የሚበትን አስተሳሰብ ይዘው በአመራርነት የተቀመጡ ኃይሎችም መልቀቅ አለባቸው። በብሄር ከፋፍለው ሲያባሉን የነበሩት ሰዎች፣ ዛሬ ደግሞ በጎጥ እየከፋፈሉን ነው። የተማረው የአማራ ሀይልም ጥቅምንና የግል ክብርን ማዕከል ከማድረግ መቆጠብ አለበት። ኮለኔል ደመቀ ዘውዱ

ስለ ስኳድ ከተናገርኩት‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ #ጋዜጠኛ:- ስኳድ የሚባለው ማን ነው? ዋነኛ ዓላማውስ ምንድን ነው? #የኔ_መልስ፦ ስኳድ የሚባለው ስብስብ ከአራቱም የአማራ ዞኖች የተውጣጡ አጋሰሶችን
+1
ስለ ስኳድ ከተናገርኩት‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ #ጋዜጠኛ:- ስኳድ የሚባለው ማን ነው? ዋነኛ ዓላማውስ ምንድን ነው? #የኔ_መልስ፦ ስኳድ የሚባለው ስብስብ ከአራቱም የአማራ ዞኖች የተውጣጡ አጋሰሶችን የያዘ አጥፊና ቀጣፊ ቡድን ሲሆን ዓላማው ደግሞ እንደሚከተለው ነው‼️ ➔የሕዝብ ክንድ የሆኑ ጀግኖች ላይ ግድያዎችን ማቀነባበር፤ ➔የአማራ ድምጽ የሆነ ሐቀኛ ልጆችን በትሕነግ ተላላኪነት እየፈረጁ ማሳሰር፤ ➔የአማራን ሕዝብ አንድነት የሚበጣጥሱና የሚያፈራርሱ ሤራዎችን ማዋቀር፤ ➔እንደ ወነግ ሕብረት እና ራዴፓ ካሉ አማራ ጠል አደረጃጀቶች ጋር በጋራ በመስራት ከትልቁ ክልል ውስጥ ትናንሽ ክልሎችን መፍጠር፤ ➔በቁጥጥር ስር የሚውሉና የሚገደሉ የአማራ ልጆችን መለየት፤ ➔የአማራን ሕዝብ ፋታ የሚያሳጡ አጀንዳዎችን ማሰራጨት፤ ➔ታላቁን ሕዝብ ከፖለቲካ ውጭ አድርጎ ለቁማርተኛ ኃይሎች አሳልፎ መስጠት፤ ➔በአማራ ክልል ውስጥ የሚፈጠሩ አደረጃጀቶች ውስጥ ሰርጎ በመግባት የተደራጁበትን ዓላማ ማኮላሸት፤ . . (ስለ መፍትሔው ከአፍታ በኋላ እመለስበታለሁ)

ከመዓዛ መሐመድ ጋር ያደረግነው ቆይታ

በትናንቱ የክርክር መድረክ ላይ የአቶ ልደቱ አንደበት የአንቺን እውነት፣ እውቀት እና የንግግር ክህሎት ማሸነፍ አልተቻለውም። እናም.... ሆዳም ፖለቲከኛ በመቀፍቀፍ የሚታወቀው የአማራ ሕዝብ አንቺን
በትናንቱ የክርክር መድረክ ላይ የአቶ ልደቱ አንደበት የአንቺን እውነት፣ እውቀት እና የንግግር ክህሎት ማሸነፍ አልተቻለውም። እናም.... ሆዳም ፖለቲከኛ በመቀፍቀፍ የሚታወቀው የአማራ ሕዝብ አንቺን መሰል ልባም ሴት በማፍራቱ ሊጽናና ይገባዋል።

አማራ ሚዲያ ማዕከል ጋር ያደረግኩት ቆይታ

የእነ ቀለጠ መግለጫ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔የአማራ ሕዝብ በጦርነት ላይ እንጂ በድርድር ላይ መሳተፍ እንደሌለበት የገለጸ፤ ➔ተዳራዳሪዎችን በአሸባሪ ድርጅት አጋርነት ፈርጆ ትሕ-ኦነግን ትርፋማ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ያደረገ፤ ➔በአማራ ሕዝብ ላይ ያቀደው ክሕደት እና ሸፍጥ ተደራሽ እንዳይሆን እንግሊዘኛ ቋንቋን የተጠቀመ፤ ➔ኢሕአዴግ ሕገ-መንግሥቱን ሲያረቅ የፈጸመውን አማራን የማግለል ተግባር በብልጽግና ዘመን ይደገም ዘንድ መንገድ የጠረገ፤ ➔መግለጫውን የጻፈው ቡድን ከትሕ-ኦነግ ኃይሎች ባልተናነሰ መልኩ ጸረ አማራ መሆኑን ይፋ ያወጣ፤ ➔ቡድኑ ከተሳካለት ወልቃይትን እና ራያን ብቻ ሳይሆን የአማራ ክልልን ሽጦ ኪሱን እና ከርሱን ከመሙላት የማይመለስ መሆኑን ያመላከተ፤ Share

በሆዱ የወደቀው ስኳድ ውድቅ ያደረጋቸው አእምሮዎች! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ የአማራ ሕዝብ አንደበት እና ክንድ የሆኑ ጀግኖችን ሲያስለቅም የከረመውና በሆዱ የወደቀው "ስኳድ" ዛሬ ባወጣው መግለጫ የአማራ
በሆዱ የወደቀው ስኳድ ውድቅ ያደረጋቸው አእምሮዎች! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ የአማራ ሕዝብ አንደበት እና ክንድ የሆኑ ጀግኖችን ሲያስለቅም የከረመውና በሆዱ የወደቀው "ስኳድ" ዛሬ ባወጣው መግለጫ የአማራ ማሕበር በአሜሪካ (ትሪፕል A) ያቀረባቸውን ተደራዳሪዎች "የትሕነግ አጋሮች" ብሎ ካጥላላቸው በኋላ ከፌደራል መንግሥት ውጭ ሌላ ተደራዳሪም ሆነ የአማራ ሕዝብ ወኪል ማየት እንደማይፈልግ ገልጿል። እናም... ለወገናቸው የሚታገሉ ጀግኖችን ሲያሳፍስ እንዲሁም ጠቃሚ አደረጃጀቶችን ሲያፈራርስ መክረሙ አንሶ ተደራዳሪ ሆነው ለመቅረብ የደፈሩ ልባሞችን የአሸባሪ አጋር አድርጎ ማንቋሸሽ የጀመረው ይህ የከሸፈ ቡድን በቀጣይ ጊዜያት "ከገዢው ፓርቲ ውጭ ሕዝባችንን ወክሎ ለምርጫ የሚቀርብ ሌላ ተፎካካሪ ፓርቲ አያስፈልግም" የሚል የአቋም መግለጫ ይዞ መምጣቱ አይቀርም።

ጋበዝኳችሁ

ከጎበዜ ሲሳይ ችሎት መልስ.... የወንድማችን የዋስትና ጉዳይ ለጥቅምት 22 ተቀጥሯል!!
+1
ከጎበዜ ሲሳይ ችሎት መልስ.... የወንድማችን የዋስትና ጉዳይ ለጥቅምት 22 ተቀጥሯል!!

ሃይ ጓዶች! እንዴት ሰነበታችሁ? በተወካይ ሲተዳደር የነበረውን የፌስቡክ ገጻችንን ተረክበናል። በቅርቡም በቀድሞ አቋማችን እና ጽናታችን የምንከሰት ይሆናል። በተረፈ በእስር በቆየሁባቸው ሰላሳ ምናምን
ሃይ ጓዶች! እንዴት ሰነበታችሁ? በተወካይ ሲተዳደር የነበረውን የፌስቡክ ገጻችንን ተረክበናል። በቅርቡም በቀድሞ አቋማችን እና ጽናታችን የምንከሰት ይሆናል። በተረፈ በእስር በቆየሁባቸው ሰላሳ ምናምን ቀናት የእኔና የቤተሰቦቼ አለኝታ ሆናችሁ የተገኛችሁ ወዳጆቼን አመሠግናለሁ። የፍትሕ ድምጽ ለሆናችሁኝ ወገኖችም ከወገቤ ጎንበስ ብዬ ምስጋናየን አቀርባለሁ። አሳዬ ደርቤ‼️

መጪው አዲስ ዓመት 🌻የተፈናቀሉ ወገኖች በፍጥነት ወደ ጎጇቸው የሚመለሱበትና ከስጋት ጸድተው የሚኖሩበት… 🌻ያለጥፋታቸው የታሰሩ ዜጎች ነጻነታቸውን የሚጎናጸፉበት… 🌻እረፍት አልባ የሆነው የወገን
መጪው አዲስ ዓመት 🌻የተፈናቀሉ ወገኖች በፍጥነት ወደ ጎጇቸው የሚመለሱበትና ከስጋት ጸድተው የሚኖሩበት… 🌻ያለጥፋታቸው የታሰሩ ዜጎች ነጻነታቸውን የሚጎናጸፉበት… 🌻እረፍት አልባ የሆነው የወገን ጦር አሸባሪ ኃይሎችን አጽድቶ የአገርን ሕልውና የሚያስከብርበት…. 🌻በግፍ የተጨፈጨፉ ንጹሐን ፍትሕ የሚያገኙበትና የእልቂት ዜና የማንሰማበት… 🌻ሥልጣን ላይ ያለው ኃይል ከተረኝነት እና ቁማርተኝነት አባዜ ተላቅቆ ክልሎችን በእኩል ዐይን የሚመለከትበት… 🌻በመንግሥትና በጠላት ወጥመድ ውስጥ ገብቶ ሲዋትት የከረመው የአማራ ሕዝብ በልጆቹ እገዛ ከቅርቃሩ ወጥቶ እራሱን የሚያስከብርበትና ወገኑን የሚያከብርበት… 🌻በመስመር ትግል ውስጥ ተቸንክረው የኖሩ ወገኖች ወደ አገራዊ እሳቤ ተሸጋግረው ያለ ባንክ እና ያለ መብራት ሳይሆን ያለ ህው-*ት የሚኖሩበት…. እንዲሆን እመኛለሁ፡፡ የትኛውም የአዲስ ዓመት ምኞት ግን ያለ እኛ ጥረት እና ድርጊት ሊሰምር ስለማይችል ከላይ የዘረዘርኳቸው ምኞቶች ይሰምሩ ዘንዳ እንደ አንድ ዜጋ የሚጠበቅብኝን ለማድረግ ለእራሴ ቃል ገብቻለሁ፡፡ አሳዬ ደርቤ መልካም አዲስ ዓመት!

photo content

photo content

"ከመንግሥት ጎን ካልሆንክ የጠላት ወገን ነህ" አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔አገር ውስጥ ተቀምጠው፣ ከትሕ-ኦነግ ታጣቂዎች ጎን ተሰልፈው፣ የአገር ጠባቂ የሆነውን መከላከያ ሠራዊት የአንድ ብሔርና የአንድ ጠቅላይ ሚኒስትር አገልጋይ አድርገው፣ የጌታቸው ረዳ የፕሮፖጋንዳ ክንፍ ሆነው.... ከመንግሥት ባለፈ አገር ለማፍረስ የሚተጉ እልፍ አእላፍ የኦነግ አክቲቪስቶችን ከዩቲዩብ ቻናላቸውና ከፌስቡክ ገጻቸው ጋር ላሳይህ እችላለሁ፡፡ ሆኖም ግን አገር አጣብቂኝ ውስጥ በወደቀችበት ጊዜ ከጠላት ጎን ተሰልፈው በአገር ላይ ዘመቻ ከከፈቱት ከእኒህ አክቲቪስቶች ጫጫታ ይልቅ የመዓዛ መሐመድ ዝምታ እንደ ትልቅ ወንጀል ተቆጠሮ ለሦስተኛ ጊዜ ወደ ወህኒ ስትወረወር ታያለህ፡፡ ➔የወሎ ወገናቸውን ከወራሪ ጥቃት ሊታደጉ ከጎጃምና ከጎንደር ምድር የመጡ ፋኖዎችን ሥም በማጠልሸት ወሎን ከወገኑ ነጥለው ለወራሪ ለማስረከብ የሚባትሉ........ አንዱን ጀብደኛ ሌላውን ጥቅመኛ በሚያደርጉ ፕሮፖጋንዳዎች የወሎ አማራ ፋኖን በመንደር የሚከፋፍሉ..... በሕብረት ሥም ልዩነት የሚዘራ ቡድን አዋቅረው ተፋቅሮ የኖረውን የወሎን ሕዝብ በሃይማኖትና በማንነት የሚሸነሽኑ..... በወራሪዎች ፈንታ ከምዕራብ ወሎ እና ከሰሜን ወሎ የዘመቱ ፋኖዎችን በሐሰት ፕሮፖጋንዳ የሚያብጠለጥሉ.... ጸረ-አማራ አክቲቪስቶችን እኩይ ተግባር በማስረጃ አስደግፈህ ብታቀርብ የሚሰማህ የመንግሥት አካል የለም፡፡ በሌላ መልኩ ግን የወገናቸው ልሳን ሆነው የሕዝብን አንድነት እና የመኖር መብት ለማስጠበቅ በአቅማቸው ልክ የሚተጉ ወገኖች የሆነ ስህተት የተገኘባቸው ቀን ከላይ የተጠቀሱት እኩይ ኃይሎች የፌስቡክ ዘመቻ እና ዛቻ ይከፍቱባቸዋል፡፡ በዚያች ቅጽበትም ሥልጣን ላይ ያለው ኃይል ሰለባውን ከእስር ቤት ወርውሮ በጸረ አማራነት የተደራጀ የትኛውም ኃይል ጠቁሞ የሚያሳስር እንጂ ተጠቁሞ የሚታሰር አለመሆኑን ያስረዳኻል፡፡ እናም እላለኹኝ… ከአሸባሪዎች ጋር የሚደረግን ትግል እንደ መልካም እድል ተጠቅሞ ‹‹ከመንግሥት ጎን ያልቆመ ሁሉ የጠላት ወገን ነው›› በሚል መናኛ አቋም የአማራ ድምጾችን የማክሰም እንቅስቃሴ ይቁም!!