uz
Feedback
ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ/Holy Trinity University

ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ/Holy Trinity University

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ/Holy Trinity University analitikasi

ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ/Holy Trinity University (@holytrinityunversity) Ingliz til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 10 079 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 19 596-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 3 297-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 10 079 obunachiga ega bo‘ldi.

07 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 92 ga, so‘nggi 24 soatda esa 0 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 68.55% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 21.56% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 6 906 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 172 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.
  • Tematik yo‘nalishlar: Kontent semester, e.c, iii, undergraduate kabi asosiy mavzularga jamlangan.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Kanal uchun tavsif kiritilmagan.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 08 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

10 079
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+427 kunlar
+9230 kunlar
Postlar arxiv
ሊቀ ብርሃናት ቆሞስ ዶ/ር አባ ጴጥሮስ ሰሎሞን(ረዳት ፕሮፌሰር) የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር የዩኒቨርሲቲያችንና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፊሎሎጂና በነገረ መለኮት መምህር የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ስብከተ ወንጌል ኃላፊ እና የገዳሙ የቦርድ አስተዳደር ጸሐፊ ሲሆኑ ከዚህ በፊትም በውጪው ዓለም በሀገረ ጣልያንበኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በአስተዳዳሪነትአገልግለዋል የትምህርት ዝግጅት 1ኛ በቅ/ሥ/ዩ የመጀመሪያ ዲግሪ በነገረ መለኮት (እጅግ በከፍተኛ ማዕረግ) 2ኛ በነገረ መለኮት ግራጅዌት ዲፕሎማ 3ኛ ሁለተኛ ዲግሪ በቅ/ሥ/ዩ (እጅግ በከፍተኛ ማዕረግ) 4ኛ ከአ/አ ዩኒቨርሲቲ ሦስተኛ ዲግሪ(PHD) አግኝተዋል ኅትመት በርካታ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር በማቅረብ ያሳተሙ ሲሆን ተማሪዎችን በማስተርስ (MA) በዶክትሬት (PHD) እያማከሩ ይገኛሉ በዛሬው ዕለት 5/9/18 ዓ.ም ያቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ ''Communal Sanctity and Divine Synergy in the Hagiography of Six Saints'' በሚል የአንድነትና መንፈሳዊ ቅድስና የሚያሳየውን የስድስቱን ቅዱሳን በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት መቄት ወረዳ ምዕራፈ ቅዱሳን ጎረጎር ቅድስት ማርያም የሚገኘውን ገድል ከቅዱሳኑ ሕይወትና ኅልፈታቸው ከዚያም በኋላ ስለተገባላቸው ቃልኪዳን እጅግ ልዩ በሆነ አቀራረብ (point of view) በዩኒቨርሲቲው አዳራሽ ለታዳሚዎች አቅርበዋል በዚህ በቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ ላይ እጅግ በርካታ አባቶች ከዩኒቨርሲቲያችን አካዳሚክ ም/ፕሬዚደንት አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ (ፕሮፌሰር) ጀምሮ በርካታ የዪኒቨርሲቲው ረዳት ፕሮፌሰሮች ፋካሊቲ ዲኖች መምህራን የአሁንና የቀድሞም ተማሪዎች ታድመዋል። በተለይ የቅዱሳኑ የሕይወት አንድነት በዚህ ዘመን ላለን ኦርቶዶክሳውያን እጅግ አስተማሪ መሆኑ ተብራርቷል (ዘርዕ ንፁህ ዘይፈሪ ውስተ ስጋሆሙ ለቅዱሳን ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ)የሚለውን የአባ ጊዮርጊስ ድርሰትን በማያያዝ የ፮ቱ ቅዱሳን ሕይወት ገድላቸው እንደሚነግረን ሰፊ ትምህርት የተገኘበት በጥያቄና መልስ የታጀበ ከመሆኑም በላይ በዚህ ዘመን ከቤተክርስቲያኗ እውቅና ውጪ ለሚታተሙ ገድላት እጅግ አስተማሪ መሆኑን ሳንጠቁም አናልፍም በዚህ ጥናት ፮ቱ ቅዱሳን ተጋድሏቸው የፈፀሙት ተዓምራትና የተገባላቸው ቃል ኪዳን እንዲሁም የተደረሰላቸው መልክ በቁጥር ስድስት ሲሆኑ ነገር ግን በአንድ ላይ ሆኖ የቀረበበትን ስንመለከት መንፈሳዊው ዓለም በአንድ መንፈስ ቅዱስ የሚመራ መሆኑን ገድሉን ልዩ እንደሚያደርገው እኛም ዛሬ ከነዚህ ቅዱሳን ይህንን ሕይወት መማር እንደሚገባን በአንድነት መጸለይ ማንኛውንም መንፈሳዊ ተግባር መፈፀም እንደሚገባንና ለሌላውም አርአያ መሆን እንደሚያስፈልግ በመግለጽ ጥናታቸውን አጠቃልለዋል።ይህንን ጥናት ያደረጉት አባት ቦታው ድረስ ሄደው በብራና የተጻፈውን ገድል አግኝተው ሳይሆን የታተመውን መጽሐፍ መነሻ በማድረግ ሲሆን ወደፊት ቀጣይ ሰፊ ጥናት ሊደረግበት የሚገባ መሆኑን በማሳሰብ ከቤቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ በመስጠትና ገንቢ ሀሳቦችን በመቀበል እጅግ በአማረ ሁኔታ ምሁራዊ ጥናት አቅርበዋል።ለአባታችን ረጅም ዕድሜ ከሰፊ ጤንነት ጋር አምላከ ቅዱሳን ያድልልን እንላለን። አሜን