ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ/Holy Trinity University
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
9 994
المشتركون
+124 ساعات
+67 أيام
-2930 أيام
أرشيف المشاركات
ሊቀ ብርሃናት ቆሞስ ዶ/ር አባ ጴጥሮስ ሰሎሞን(ረዳት ፕሮፌሰር) የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር የዩኒቨርሲቲያችንና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፊሎሎጂና በነገረ መለኮት መምህር የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ስብከተ ወንጌል ኃላፊ እና የገዳሙ የቦርድ አስተዳደር ጸሐፊ ሲሆኑ ከዚህ በፊትም በውጪው ዓለም በሀገረ ጣልያንበኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በአስተዳዳሪነትአገልግለዋል
የትምህርት ዝግጅት
1ኛ በቅ/ሥ/ዩ የመጀመሪያ ዲግሪ በነገረ መለኮት (እጅግ በከፍተኛ ማዕረግ)
2ኛ በነገረ መለኮት ግራጅዌት ዲፕሎማ
3ኛ ሁለተኛ ዲግሪ በቅ/ሥ/ዩ (እጅግ በከፍተኛ ማዕረግ)
4ኛ ከአ/አ ዩኒቨርሲቲ ሦስተኛ ዲግሪ(PHD) አግኝተዋል
ኅትመት
በርካታ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር በማቅረብ ያሳተሙ ሲሆን ተማሪዎችን በማስተርስ (MA) በዶክትሬት (PHD) እያማከሩ ይገኛሉ
በዛሬው ዕለት 5/9/18 ዓ.ም ያቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ
''Communal Sanctity and Divine Synergy in the Hagiography of Six Saints''
በሚል የአንድነትና መንፈሳዊ ቅድስና የሚያሳየውን የስድስቱን ቅዱሳን በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት መቄት ወረዳ ምዕራፈ ቅዱሳን ጎረጎር ቅድስት ማርያም የሚገኘውን ገድል ከቅዱሳኑ ሕይወትና ኅልፈታቸው ከዚያም በኋላ ስለተገባላቸው ቃልኪዳን እጅግ ልዩ በሆነ አቀራረብ (point of view) በዩኒቨርሲቲው አዳራሽ ለታዳሚዎች አቅርበዋል በዚህ በቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ ላይ እጅግ በርካታ አባቶች ከዩኒቨርሲቲያችን አካዳሚክ ም/ፕሬዚደንት አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ (ፕሮፌሰር) ጀምሮ በርካታ የዪኒቨርሲቲው ረዳት ፕሮፌሰሮች ፋካሊቲ ዲኖች መምህራን የአሁንና የቀድሞም ተማሪዎች ታድመዋል። በተለይ የቅዱሳኑ የሕይወት አንድነት በዚህ ዘመን ላለን ኦርቶዶክሳውያን እጅግ አስተማሪ መሆኑ ተብራርቷል (ዘርዕ ንፁህ ዘይፈሪ ውስተ ስጋሆሙ ለቅዱሳን ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ)የሚለውን የአባ ጊዮርጊስ ድርሰትን በማያያዝ የ፮ቱ ቅዱሳን ሕይወት ገድላቸው እንደሚነግረን ሰፊ ትምህርት የተገኘበት በጥያቄና መልስ የታጀበ ከመሆኑም በላይ በዚህ ዘመን ከቤተክርስቲያኗ እውቅና ውጪ ለሚታተሙ ገድላት እጅግ አስተማሪ መሆኑን ሳንጠቁም አናልፍም
በዚህ ጥናት ፮ቱ ቅዱሳን ተጋድሏቸው የፈፀሙት ተዓምራትና የተገባላቸው ቃል ኪዳን እንዲሁም የተደረሰላቸው መልክ በቁጥር ስድስት ሲሆኑ ነገር ግን በአንድ ላይ ሆኖ የቀረበበትን ስንመለከት መንፈሳዊው ዓለም በአንድ መንፈስ ቅዱስ የሚመራ መሆኑን ገድሉን ልዩ እንደሚያደርገው እኛም ዛሬ ከነዚህ ቅዱሳን ይህንን ሕይወት መማር እንደሚገባን በአንድነት መጸለይ ማንኛውንም መንፈሳዊ ተግባር መፈፀም እንደሚገባንና ለሌላውም አርአያ መሆን እንደሚያስፈልግ በመግለጽ ጥናታቸውን አጠቃልለዋል።ይህንን ጥናት ያደረጉት አባት ቦታው ድረስ ሄደው በብራና የተጻፈውን ገድል አግኝተው ሳይሆን የታተመውን መጽሐፍ መነሻ በማድረግ ሲሆን ወደፊት ቀጣይ ሰፊ ጥናት ሊደረግበት የሚገባ መሆኑን በማሳሰብ ከቤቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ በመስጠትና ገንቢ ሀሳቦችን በመቀበል እጅግ በአማረ ሁኔታ ምሁራዊ ጥናት አቅርበዋል።ለአባታችን ረጅም ዕድሜ ከሰፊ ጤንነት ጋር አምላከ ቅዱሳን ያድልልን እንላለን። አሜን
ሊቀ ብርሃናት ቆሞስ ዶ/ር አባ ጴጥሮስ ሰሎሞን(ረዳት ፕሮፌሰር) የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር የዩኒቨርሲቲያችንና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፊሎሎጂና በነገረ መለኮት መምህር የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ስብከተ ወንጌል ኃላፊ እና የገዳሙ የቦርድ አስተዳደር ጸሐፊ ሲሆኑ ከዚህ በፊትም በውጪው ዓለም በሀገረ ጣልያንበኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በአስተዳዳሪነትአገልግለዋል
የትምህርት ዝግጅት
1ኛ በቅ/ሥ/ዩ የመጀመሪያ ዲግሪ በነገረ መለኮት (እጅግ በከፍተኛ ማዕረግ)
2ኛ በነገረ መለኮት ግራጅዌት ዲፕሎማ
3ኛ ሁለተኛ ዲግሪ በቅ/ሥ/ዩ (እጅግ በከፍተኛ ማዕረግ)
4ኛ ከአ/አ ዩኒቨርሲቲ ሦስተኛ ዲግሪ(PHD) አግኝተዋል
ኅትመት
በርካታ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር በማቅረብ ያሳተሙ ሲሆን ተማሪዎችን በማስተርስ (MA) በዶክትሬት (PHD) እያማከሩ ይገኛሉ
በዛሬው ዕለት 5/9/18 ዓ.ም ያቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ
''Communal Sanctity and Divine Synergy in the Hagiography of Six Saints''
በሚል የአንድነትና መንፈሳዊ ቅድስና የሚያሳየውን የስድስቱን ቅዱሳን በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት መቄት ወረዳ ምዕራፈ ቅዱሳን ጎረጎር ቅድስት ማርያም የሚገኘውን ገድል ከቅዱሳኑ ሕይወትና ኅልፈታቸው ከዚያም በኋላ ስለተገባላቸው ቃልኪዳን እጅግ ልዩ በሆነ አቀራረብ (point of view) በዩኒቨርሲቲው አዳራሽ ለታዳሚዎች አቅርበዋል በዚህ በቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ ላይ እጅግ በርካታ አባቶች ከዩኒቨርሲቲያችን አካዳሚክ ም/ፕሬዚደንት አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ (ፕሮፌሰር) ጀምሮ በርካታ የዪኒቨርሲቲው ረዳት ፕሮፌሰሮች ፋካሊቲ ዲኖች መምህራን የአሁንና የቀድሞም ተማሪዎች ታድመዋል። በተለይ የቅዱሳኑ የሕይወት አንድነት በዚህ ዘመን ላለን ኦርቶዶክሳውያን እጅግ አስተማሪ መሆኑ ተብራርቷል (ዘርዕ ንፁህ ዘይፈሪ ውስተ ስጋሆሙ ለቅዱሳን ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ)የሚለውን የአባ ጊዮርጊስ ድርሰትን በማያያዝ የ፮ቱ ቅዱሳን ሕይወት ገድላቸው እንደሚነግረን ሰፊ ትምህርት የተገኘበት በጥያቄና መልስ የታጀበ ከመሆኑም በላይ በዚህ ዘመን ከቤተክርስቲያኗ እውቅና ውጪ ለሚታተሙ ገድላት እጅግ አስተማሪ መሆኑን ሳንጠቁም አናልፍም
በዚህ ጥናት ፮ቱ ቅዱሳን ተጋድሏቸው የፈፀሙት ተዓምራትና የተገባላቸው ቃል ኪዳን እንዲሁም የተደረሰላቸው መልክ በቁጥር ስድስት ሲሆኑ ነገር ግን በአንድ ላይ ሆኖ የቀረበበትን ስንመለከት መንፈሳዊው ዓለም በአንድ መንፈስ ቅዱስ የሚመራ መሆኑን ገድሉን ልዩ እንደሚያደርገው እኛም ዛሬ ከነዚህ ቅዱሳን ይህንን ሕይወት መማር እንደሚገባን በአንድነት መጸለይ ማንኛውንም መንፈሳዊ ተግባር መፈፀም እንደሚገባንና ለሌላውም አርአያ መሆን እንደሚያስፈልግ በመግለጽ ጥናታቸውን አጠቃልለዋል።ይህንን ጥናት ያደረጉት አባት ቦታው ድረስ ሄደው በብራና የተጻፈውን ገድል አግኝተው ሳይሆን የታተመውን መጽሐፍ መነሻ በማድረግ ሲሆን ወደፊት ቀጣይ ሰፊ ጥናት ሊደረግበት የሚገባ መሆኑን በማሳሰብ ከቤቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ በመስጠትና ገንቢ ሀሳቦችን በመቀበል እጅግ በአማረ ሁኔታ ምሁራዊ ጥናት አቅርበዋል።ለአባታችን ረጅም ዕድሜ ከሰፊ ጤንነት ጋር አምላከ ቅዱሳን ያድልልን እንላለን። አሜን
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
