uz
Feedback
Wondo Genet Secondary School

Wondo Genet Secondary School

Kanalga Telegram’da o‘tish

Educational purpose

Ko'proq ko'rsatish
2 811
Obunachilar
+224 soatlar
+357 kunlar
+12630 kunlar
Postlar arxiv
ማስታወቂያ ለ12ክፍል ተማሪዎች መኪና እየወጣ ስለሆነ ለሚፈጠረው ስለሆነ ለሚፈጠረው ነገረ ሀላፊነት አንወስድም።

ውድ ተማሪዎቻችን እንኳን አደረሳችሁ! መልካም የፈተና ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። ፈጣሪ ከእናንተ ጋር ይሁን ። አይዟችሁ። ተረጋግታችሁ ስሩ አትደንግጡ። በሰላም አስጀምሮ በሰላም ያስጨርሳችሁ።

ማስታወቂያ ለ2።ኛ ዙር ተፈታኞች በሙሉ ነገ አርብ የምትገቡ ተማሪዎች ልክ ጠዋት 12 ሰዓት ላይ እንድትገኙ እያሳሰብን አረፍዶ ለሚመጣ ተማሪ ሃላፊነት የማንወስድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ :- የመኪና መግቢያ ኩፖን በቂ ዕንቅልፍ ወስዶ በጊዜ ለመነሳት በጊዜ መተኛት ያስፈልጋል። መልካም የፈተና ጊዜ ይሁንላችሁ እግዚአብሔር አምላክ የያግዛችሁ!

ማሳሰቢያ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ዛሬ እረንቴሽን የሚሰጠው ለሁሉም ዙር ከround እስከ 2-round 6 ያላችሁ ሀላችሁም የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሁላችሁም ናችሁ። ከዛሬ ውጪ ሌላ ጊዜ የሚሰጥ ኦረንቴሽን አለመኖሩን ተረድታችሁ በጊዜበተገለጸው ሰዓት እንድትደርሱ አሳስባለሁ።

ምክር ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች እንኳን በጉጉት ስትጠብቁት ለነበረው ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ሳምንት በሰላም አደረሳችሁ። ይህ ለእናንተ ወሳኝ ጊዜ ነው። እስካሁን ትምህርታችሁን እያጠናችሁ ቆይታችኋል። መልካም ነው። ነገር ግን በፈተና ወቅት የምታከናውኗቸው ተግባራትም የጥናታችሁን ያህል ውጤታችሁ ላይ ተጽዕኖ አላቸው። ስለዚህ በዚህ ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባችሁና ምን ማድረግ እንደሌለባችሁ ጠንቅቃችሁ ማወቅ ይጠበቅባችኋል። ለዚህም ይረዳችሁ ዘንድ የሚከተሉትን ምክሮችን ከወዲሁ ተረድታችሁ ለመተግበር ዝግጁ ሁኑ! ⓵ በዋዜማው ስልክ መዝጋትና ከሚረብሹ ነገሮች ራስን ማራቅ ያስፈልጋል። ስልካችሁን መዝጋት ሀሳባችሁን ሊሰርቁ ከሚችሉ ማህበራዊ ሚዲያዎች መራቅ ይገባችኋል። በዚህ ወቅት ትኩረታችሁን ፈተናችሁ ላይ ብቻ አድርጉ፤ ⓶ በቂ እንቅልፍ ተኙ። በፈተና ዋዜማ ለማንበብ ብላችሁ በፍጹም አታምሹ። ባጭሩ በዚህ ቀን ተጨማሪ ሰዓት ከማንበብ ይልቅ ተጨማሪ ሰዓት መተኛት የተሻለ ዉጤት አለው። በቂ እንቅልፍ አለመተኛት በፈተና ወቅት ለድብርትና ለራስ ምታት ሊዳርግና ሥራችሁን ሊያበላሽ ይችላል። ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት ከባድ ምግቦችን አለመመገብ፤ ብዙ ቡና አለመጠጣት፤ እና ሌሎች አነቃቂ ነገሮችን አለመውሰድ ይመከራል፤ ⓷ ጠዋት ማልዶ መነሳት: በጊዜ ተነስቶ መዘጋጀት ከመቻኮል ጋር ተያይዞ ከሚመጣ መታወክ ያድናል። በተጨማሪም ወደፈተናው አዳራሽ በጊዜ ለመድረስ ያስችላል፤ ⓸ ቁርስ በአግባቡ መብላት: በፈተና ወቅት ቁርስ አለመብላት አእምሮአችን የሚፈልገውን ያህል ኃይል እንዳያገኝ ስለሚያደርግ ለማሰብ አቅም እንዲያንስ ያደርጋል። ስለዚህ ቀለል ያሉ ምግቦችን ተመግባችሁ መሄድ ይኖርባችኋል። ከባድ ምግቦችን መመገብ ደግሞ አእምሮአችን ምግብ የመፍጨት ሥራ ላይ ብቻ እንዲወጠር ስለሚያደርግ ድካምና እንቅልፍ ያመጣል፤ ⓹ ወደ መፈተኛ ቦታው ፈተናው ከሚጀምርበት ሰዓት በፊት ቀድሞ መድረስ ያስፈልጋል። ይህም ለመረጋጋት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አለው፤ ⓺ ከቤት ስትወጡ የፅህፈት መሳሪያዎቻችሁንና የመታወቅያ ካርዳችሁን መያዛችሁን እርግጠኛ ሁኑ። ይህም ከመንገድ ከመመለስና ከማርፈድ ያድናችኋል። ትርፍ እርሳሶችን እና የእርሳስ መቅረጫዎች መያዝ በጣም አስፈላጊ ነው፤ ⓻ ወደ ፈተና አዳራሽ ከመግባት በፊት ወደ መፀዳጃ ቤት መሄድ መልካም ነው። ምናልባት የፈተናው ሰዓት ረዥም ቢሆንና ሽንት ቢይዛችሁ መጨናነቅን ያመጣል። አቋርጣችሁ መውጣት ላይፈቀድላችሁ ይችላል፤ ⓼ መመሪያዎችን (instructions) በአግባቡ ማንበብና መተግበር ያስፈልጋል። በእያንዳዱ ፈተና ወረቀት ላይ ወይም የፈተናው ክፍሎች ላይ የሚሰጡትን መመሪያዎች በአግባቡ ማንበብና መተግበር ይኖርባችኋል፤ ⓽ አትደንግጡ! በደንብ ተንፍሱ! ብዙ ኦክስጂን ወደ ውስጣችን ማስገባት ብዙ ምግብ እንዲቀጣጠልና ኃይል እንዲመረት ስለሚያደርግ ጉልበትና ድፍረት ይጨምርላችኋል፤ ⓾ መልስ መመለስ ከመጀመራችሁ በፊት ጥያቄውን በደንብ ማንበብ ያስፈልጋል። ችኮላ ዋጋ ያስከፍላል ። ⓫ አንዱ ጥያቄ ከከበዳችሁ ዝለሉት፤ አንድ ጥያቄ ላይ ተጠምዳችሁ ብዙ ጊዜ የምታጠፉ ከሆነ ቀጥለው ለሚጠብቋችሁ ጥያቄዎች ጊዜ ሊያጥራችሁ ይችላል። ስትዘሉት ግን ጥያቄው ላይ ምልክት(flag🚩) ማድረጋችሁንና ከተሰጡት አማራጮች አንዱን መልስ በግምት ማጥቆራችሁን አትርሱ። ምልክት(flag🚩) አድርጎ ማለፍ ምናልባት በኋላ የተሰጠው ጊዜ ቢያልቅና ወደ ጥያቄው መመለስ ቢያቅታችሁ መልስ መስጫ ቦታው ባዶ ሆኖ እንዳይቀር ያደርጋል፤ ⓬ ቶሎ ለመውጣት አትቸኩሉ፤ ምንም አይጠቅማችሁም፤ ሰዓታችሁን አሟጥጣችሁ መጠቀማችሁን፤ ሁሉንም ጥያቄዎች በአግባቡ መመለሳችሁንና ማጥቆራችሁን አረጋግጡ። ጊዜ ቢተርፋችሁ ጥያቄዎቹን ለመከለስ ተጠቀሙበት፤ ⓭ ያልገባችሁ ማንኛውንም ነገር ሲኖር ፈታኞችን ለመጠየቅ አትፍሩ (ከመልስ በስተቀር😉)፤ ⓮ ልክ የፈተና ወረቀቱን ከመለሳችሁበት ጊዜ ጀምሮ የዚያ ትምህርት (subject) ነገር ማክተሙን በመገንዘብ ለቀጣዩ ፈተና እራስን ማዘጋጀት ይገባል። እንጂ፤ ስላለፈው ፈተና እያሰላልሰሉ መጨነቅ ለቀጣዩ ፈተና በምታደርጉት ዝግጅት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል። መልካም ዕድል!!!

ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉ በመጀመሪያ እንኳን ደስ አላችሁ 1. በፈተና ወቅት የምትመላለሱበትን ትራንሰፖርት በከተማው አሰተዳደር በኩል ስለተዘጋጀ አርብ የ2ኛው ዙር 45 ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ በር ላይ ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ላይ እንድትገኙ አሳስባለሁ። 2. ነገ ሐሙስ ከሰዓት ከቀኑ በ 8:00 ላይ ወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ለኦረንቴሽን ስለተጠራችሁ ቀደም ብላችሁ የደንብ ልብሳችሁን ለብሳችሁ ፀጉራችሁን ተስተካክላችሁ እንድትገኙ አሳስባለሁ።

ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ለተማሪዎች በሙሉ ዛሬ 24/10/2018 ዓም ከሰዓት 8:00 ሰዐት ላይ ኦረንቴሽን ስለሚኖር ሀላችሁም ተፈታኞች ት/ቤታችን ግቢ ውስጥ እንድትገኙ አሳስባለሁ። ማሳሰቢያ:- አለባበስ እና ወንዶች ፀጉራችሁን አሳጥራችሁ እንድትቀርቡ እናሳስባለን።

https://exp10.ethernet.edu.et/ በዚህ link እየገባችሁ ለmock exam የተለቀቀውን ፈተና ስሩ Username: Admission number Password: 1234

2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ዝግጅት የአፈፃፀምና ቀሪ ስራዎችን በሚመለከት የክልሉ ግብረ ሀይሉ ግምገማ ተካሄደ ። ሰኔ 18/2018 ዓ.ም የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት የዘንድሮ ሀገራዊ ፈተና የሚፈተኑ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ የ12ኛ ክፍል ፈተና ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ የሲዳማ ክልል ትምህርት ቢሮ ከግብረ ሀይል ጋር ግምገማ አድርገዋል። ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም እስከ ሀምሌ 17/2018 ዓ.ም ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና በስድስት ዙር የሚሰጥ ሲሆን በመጀመሪያ ሶስት ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የሚፈተኑና ቀጣይ ሶስት ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የሚፈተኑ ይሆናል ። የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጠው በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሚገኙ ሁሉም ካምፓሶች፣ከኮሌጆችና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት እንዲሁም በተመረጡ በመንግስትና ግል ትምህርት ቤቶች መሆኑንም ተገልጿል። በፈተና ላይ የመብራት፣የኔትወርክ የመሳሰሉት ችግር እንዳይፈጠር የቅንጅት ስራ መስራት እንደሚገባና የክትትልና ድጋፍ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በግምገማ ወቅት ተነስተዋል ። ክቡር አቶ በየነ ባራሳ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ የግብረ-ሀይል ሰብሳቢ እንደገለጹት ተማሪዎች በሁለቱም መንገድ ፈተናውን ያለ ምንም መስተጓጎል የጉዞ ቀናትን ጨምሮ በፈተና ቀናት ሰላማዊ ሆኖ እንድጠናቀቅ የሁሉም ባለድርሻ ቅንጅት መጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል።

👍

round 6(six).xlsx0.11 KB

Round 6.pdf4.27 KB

Round 5.pdf6.39 KB

round 5(five).xlsx0.26 KB

round 4(four).xlsx0.17 KB

Round 4.pdf5.05 KB

round 3(three).xlsx0.24 KB

Round 3.pdf6.04 KB

round 2.pdf4.75 KB

round 2(two).xlsx0.16 KB