2 980
订阅者
+924 小时
+427 天
+15230 天
帖子存档
ማስታወቂያ
በ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በሪሚዲያል (Remedial) መርሃ-ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምደባ ምርጫችሁን ከመስከረም 7/ 2019 ዓ.ም. እስከ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ም. ድረስ ወደ ትምህርት ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ ሆናችሁ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም እራሳችሁ እንድትሞሉ እንገልጻለን።
የማስፈንጠሪያ ሊንክ (Link): https://student.ethernet.edu.et/preferences
እንኳን አደረሳችሁ!
ማስታወቂያ ለወንዶ ገነት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በሙሉ
ከነገ ማለትም ከ05/01/19 ዓ.ም ጀምሮ መደበኛ መማር ማስተማር ስለሚጀምር ጠዋት 1: 45 ጀምሮ ዩኒፎርም በመልበስ በትምህርት ቤታችሁ በመገኘት ትምህርታችሁን እንድትከታተሉ በጥብቅ እናሳሰበለን።
📒 ፈረቃ 1 ጠዋት
12ኛ ክፍል እና 9ኛ ክፍል
📒 ፈረቃ 2 ከሰዓት
11ኛ ክፍል እና 10ኛ ክፍል
ት/ቤቱ!
ለ2018ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ለተፈተናችሁ
የሪሚዲያል መርሃ ግብር የዩኒቨርሲቲ ቅበላ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ።
ለ2019 ዓ/ም የሪሚዲያል መርሃ ግብር ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ በተማሪዎች ውጤት፣ በዩኒቨርሲቲዎች የቅበላ አቅም፣ እና በሀገራዊ የትምህርት ፍትሃዊነት መርህ ላይ ተመስርቶ መወሰኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
በዚህም መሰረት ከታችን የተገለጸውን ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ለሪሚዲያል መርሃ ግብርየዩኒቨርሲቲ ቅበላ ብቁ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
1. የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች
👉 ከ600 ውስጥ 240 እና ከዚያ በላይ (40%)
2. የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች
👉 ከ600 ውስጥ 228 እና ከዚያ በላይ (38%)
በልዩ ድጋፍ የሚታይ የተማሪ ምድብ
1. ከአፋር፣ ሶማሌ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቤላ ክልሎች የተፈጥሮ ወይም ማህበራዊ ሳይንስ ለተፈተኑ ወንድና ሴት ተማሪዎች
👉 ከ600 ውስጥ 222 እና ከዚያ በላይ (37%)
2. ከአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች የተፈጥሮ ወይም ማህበራዊ ሳይንስ ለተፈተኑ ተማሪዎች
👉 ከ600 ውስጥ 222 እና ከዚያ በላይ (37%)
3. በማህበራዊ ሳይንስ የተፈተኑ ዓይነ ስውር ወንድና ሴት ተማሪዎች
👉 ከ500 ውስጥ 185 እና ከዚያ በላይ (37%)
4. በተፈጥሮ ወይም በማህበራዊ ሳይንስ የተፈተኑ መስማት የተሳናቸው ወንድና ሴት ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 222 እና ከዚያ በላይ (37%) ሆኗል።
ማስታወቂያ
ለነባር ተማሪዎች በሙሉ
የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 18/2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ መቆየቱ ይታወቃል። ከ10ኛ -12ኛ ክፍል ያላችሁ ነባር ተማሪዎች እሰከ 05/13/2018 ዓ.ም ብቻ ምዝገባ የሚካሄድ ይሆናል።
የምዝገባ ቀናት ከተጠናቀቀ በኋላ ለሚፈጠር መጉላላት ት/ቤቱ ኃላፊነት አይወስድም።
ት/ቤቱ
ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-
Ø የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን።
Ø ማስፈንጠሪያ (Link) https://student.ethernet.edu.et/
ማሳሰቢያ፡-
v የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል።
የትምህርት ሚኒስቴር
ለነባር ተማሪዎች በሙሉ
የ2019 ዓም የተማሪዎች ምዝገባ ነሐሴ 18/2018 ዓም እነደተጀመረ ይታወቃል የ9ኛ ክፍል ምዝገባ ያጠናቀቅን ሲሆን ከ10ኛ -12ኛ ክፍል ነባር ተማሪዎች እሰከ 30/12/2018 ዓም ብቻ በነኚ 5ተከታታይ የሥራ ቀናት በአካል ተገኝታችሁ እንድትመዘገቡ በጥብቅ እናሳስባለን።
ከተጠቀሰው ቀን ውጪ የማንመዘግብ መሆኑን እና የምዝገባ ቁጥር ከሞላ በመሽኛ ከት/ቤቱ የምትለቁ መሆኑን በጥብቅ አሳስባለሁ።
ት/ቤቱ
የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም መግቢያ ፈተና የምዝገባ ጥሪ
===============================
በአገራችን እየተመዘገበ ያለውን የኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠልና ብልፅግናን ለማረጋገጥ የአገሪቱን በሳይንስና ቴክኖሎጂ የሰለጠነ የሰው ሀይል ፍላጎት ለማሟላት በመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ከፍተኛ የለውጥ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ይህንንም እውን ለማድረግ ልዩ ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የተደራጁትን የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራት ማዕከላት በማድረግ በዘርፉ ብቃት ያላቸውን ሙያተኞችን እያፈሩ ይገኛሉ፡፡
በመሆኑም በ2019 ዓ.ም የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና ኦንላይን (Online) በመስጠት መቀበል ይፈልጋሉ፡፡
የትምህርት መስኮች፡-
አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
ኢንጂነሪንግ
- አርክቴክቸር
- ሲቪል ኢንጂነሪንግ
- ወተር ሪሶርስ ኢንጂነሪንግ
- ኬሚካል ኢንጂነሪንግ
- ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ
- ማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ
- ኤሌክትሪካል ፓወር እና ኮንትሮል ኢንጂነሪንግ
- ኤሌክትሮኒክስ እና ኮሚኒኬሽን ኢንጂነሪንግ
- ኮምፒዩተር ሳይንስና ኢንጂነሪንግ
- ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ
አፕላይድ ሳይንስ
- አፕላይድ ባዮሎጂ
- አፕላይድ ኬሚስትሪ
- ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ
- ፋርማሲ
- አፕላይድ ፊዚክስ
- አፕላይድ ጂኦሎጂ
- አፕላይድ ማቲማቲክስ
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
ኢንጂነሪንግ
- አርክቴክቸር
- ሲቪል ኢንጂነሪንግ
- ኬሚካል ኢንጂነሪንግ
- ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ
- ኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ
- ኤሌክትሮሜካኒካል ኢንጂነሪንግ
- ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ
- ኢንቫይሮሜንታል ኢንጂነሪንግ
አፕላይድ ሳይንስ
- ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ
- ፉድ ሳይንስና አፕላይድ ኒዩትሪሽን
- ጂኦሎጂ
- ባዮቴክኖሎጂ
የምዝገባ ጊዜ፡-
- ከነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 3 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ለሊቱ 6 ሰዓት ይሆናል፡፡
የምዝገባ ቦታ፡
- የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online) በ https://stuoexam.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et; www.astu.edu.et ድህረ ገፅ በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡
ፈተናው የሚሰጥበት ቀን፡- በድህረ ገፃችን የምዝገባው ቀን ካበቃበት በኋላ እናሳውቃለን ፡፡
ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ፡-
- በምዝገባ ወቅት በመረጡት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
· የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ይህንኑ አውቃችሁ ቅድሚያ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
· በቂ አመላካቾች የሌሉባቻው የፈተና ጣቢያዎች በቅርበት ወደሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ሊታጠፉ እንደሚችሉ እናሳውቃለን፡፡
· ለፈተና የሚቀርቡት የአመልካቾች ስም ዝርዝራቸው እና የፈተና ጣቢያዎች በሚከተሉት ድረ-ገፆች፡- www.aastu.edu.et ; www.astu.edu.et እንደአመቺነቱም በe-mail የሚገለፅ ይሆናል፡፡
· አመልካቾች ከወዲሁ ፈተናው በሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች፣ ማለትም (ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል) ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ፣ ሂሳብና እንግሊዝኛ እንዲዘጋጁ ይመከራል፡፡
· ፈተና የሚሰጠው በቀጥታ (online) ስለሆነ አመልካቾች በፈተና ጊዜ ሊያጋጥም የሚችል ግራ መጋባትን ለማስቀረት በምዝገባ ጊዜ ከመመዝገቢያ ፎርማቱ ጋር ተያይዞ የቀረበውን የሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ ይመከራል፡፡
· አመልካቾች ለፈተና ሲቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት፣ የሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና አድሚሽን ካርድ (ወይም መታወቂያ) እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
· የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡
· በውጤታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ከላይ በተጠቀሱት ድህረ-ገፆች ይገለፃል፡፡
· በመስፈርቱ መሰረት ያልተመረጡ አመልካቾች ከዚህ በፊት እንደሚደረገው በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የሚመደቡ ይሆናል፡፡
· በፈተናው ዕለት ማንኛውንም የሞባይል ስልኮችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ ነው፡፡
· በፈተና ወቅት ያልተገባ ተግባር መፈፀም በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ ከታች የተጠቀሱትን ድረ-ገፆች እና ቴሌግራም ቻናላችንን መጎብኘት ይቻላል፡፡
www.astu.edu.et; www.aastu.edu.et
Telegram:https://t.me/AdamaSTU_ASTU
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
ውድ ተማሪዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ!!👏👏👏🏆🏆🏆
እኛም እጅግ በጣም ደስ ብሎናል።
ለቀጣይ ተፈታኝ ተማሪዎቻችን ትልቅ የሞራል ስንቅ ነው።
🎉 እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉
የወንዶ ገነት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን በአገር አቀፍ ፈተና ባስመዘገባችሁት ውጤት ከልብ እንኳን ደስ አላችሁ!
ይህ ውጤት የተማሪዎቻችን ትጋትና ብርታት፣ የመምህራን ያላሰለሰ ጥረት፣ የወላጆች ድጋፍ እና የትምህርት ቤታችን የጋራ ስራ ውጤት ነው።
ተማሪዎቻችን የዛሬው ስኬት የነገ የበለጠ ትልቅ ስኬት መነሻ እንዲሆንላችሁ እየተመኘን፣ በቀጣይ የትምህርትና የሕይወት ጉዞአችሁ ሁሉ የላቀ ስኬት እንዲገጥማችሁ እንመኛለን።
እንኳን ደስ አላችሁ!
የወንዶ ገነት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በእናንተ ይኮራል! 🌟🎓
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት
ተፈታኞች ውጤታችሁን ከምሽቱ 1:00 ጀምሮ ማየት ትችላላችሁ
አዲስ አበባ — የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ተፈታኞች ውጤታቸውን ማየት የሚችሉበትን አማራጮች ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ የተመቻቹትን ዲጂታል አማራጮች በመጠቀም ውጤታቸውን መመልከት ይችላሉ።
ውጤት መመልከቻ አማራጮች፡
1ኛ በድረ-ገጽ (Website): https://result.eaes.et
2ኛ.በቴሌግራም ቦት (Telegram): https://result.eaes.et/telegram
3ኛ በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS): https://result.eaes.et/sms
የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜና መንገድ አገልግሎቱ አያይዞ እንዳሳወቀው፣ በውጤቱ ላይ ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳይጠበቅባቸው በኦንላይን ማቅረብ ይችላሉ።
ቅሬታ ለማስገባት https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ መጠቀም የሚቻል ሲሆን፣ ማመልከቻው ከዛሬ ነሐሴ 19 እስከ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል። የተሰጠውን ምላሽም በተመሳሳይ ሊንክ መከታተል ይቻላል።
©️የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ጉርሻ page
🌴🌴🌴
ማስታወቂያ ለትምህርት ቤታችን ተማሪዎች በሙሉ
የ2019ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ እየተከናወነ ይገኛል። ተማሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ
ለአዲስ ተማሪዎች
1ኛ የስምንተኛ ክፍል ውጤት መግለጫ ካርድ ኮፒ
2ኛ ክፍያ የተከፈለበት የባንክ ደረሰኝ
3ኛ የስፖርትና መታወቂያ 70 ብር
4ኛ የወላጅና የተማሪ አንድ አንድ ጉርድ ፎቶ
ለነባር ተማሪዎች
1ኛ ከክፍል ወደ ክፍል የተዘዋወራችሁበት የውጤት መግለጫ ካርድ
2ኛ ክፍያ የተከፈለበት የባንክ ደረሰኝ
3ኛ የስፖርት 20 ብር
4ኛ የወላጅና የተማሪ አንድ አንድ ጉርድ ፎቶ
የክፍያ መጠን፡ 500 ብር
📌ዉጤት ልክ እንደወጣ ዉጤታቹን የምታዩበት websites እነዚህ ናቸው ::
አድራሻዎቹ፡
1. ዌብ ሳይት 🌐፡ https://result.eaes.et
2. ቴሌግራም ፡ https://t.me/EAESbot
3. አጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS) ፡ 6284
የ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዋና ዋና መረጃዎች‼️
📊 የማለፊያ ውጤት
• 70,544 ተማሪዎች ፈተናውን አልፈዋል።
• ይህም 12.8% የማለፊያ ምጣኔ ነው።
• 565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።
💻 በፈተና አሰጣጥ ዘዴ
• በኦንላይን የተፈተኑ — 18.37% አልፈዋል።
• በወረቀት የተፈተኑ — 4.2% አልፈዋል።
የክልሎች የማለፊያ ምጣኔ
* አዲስ አበባ — 32.4%
* ሀረሪ — 22.76%
*አማራ — 15%
• ድሬዳዋ — 11.92%
• ትግራይ — 11.2%
• ጉምዝ — 10.53%
• ደቡብ — 9.2%
• ሶማሌ — 9%
• ሲዳማ — 6.95%
• ጉምዝ — 6.1%
• ደቡብ ኢትዮጵያ — 4.2%
