uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 373 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 571-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 195-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 373 obunachiga ega bo‘ldi.

05 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 30 ga, so‘nggi 24 soatda esa -4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 22.23% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.08% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 418 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 397 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 20 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 06 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 373
Obunachilar
-424 soatlar
-197 kunlar
+3030 kunlar
Postlar arxiv
✞ #በዓለ_ርዕሰ_ዐውደ_ዓመት_ዮሐንስ_ወቅዱስ_ራጉኤል #እንኳን_አደረሳቹ #አዲስ_ዓመት ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ የመሸጋገሪያው ዕለት በየዓመቱ ቅዱስ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራል፡፡ የዘመን መለወጫ፣ እንቁጣጣሽ፣ ሌላም መጠሪያ ስሞቹ ናቸው፡፡ በግእዝ ርእሰ ዐውደ ዓመትም ይባላል፡፡ ይህ በዓል የዓመት መጀመሪያ እንደመሆኑ መጠን በየዓመቱ ወሮች በመጀመሪያ ቀን ይከበራል፡፡ ያን ጊዜ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር እኩል 12 ሰዓት ይሆናል፡፡ ዓመቱን ጠንቅቀው ሲቆጥሩ 364 ቀናት ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ “ለዘመን መታወቂያው ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትንም ፈጠረ” ይላልና /ሔኖክ. 21፥49/፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ በፍል ውኃ አጥለቅልቆ በኃጢአት ሕይወት ይኖሩ የነበሩት የኖኅ ዘመን ሰዎች ቀጥቶ ካጠፋ በኋላ ከንፍር ውኃ ምድር የተገለጠችበት ወር ነው /ኩፋሌ. 7፥1/፡፡ “በመጀመሪያው ወር ምድር ታየች የንፍር ውኃም ከምድር ደረቀ” የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል መሠረት አድርገው የአቡሻኸር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥ ያስቀምጣሉ፡፡ ✞ የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀኖናዊ ሥርዐት ያጠኑ ሊቃውንት ደግሞ አዲስ ዓመት መስከረም አንድ ቀን መሆኑን አስመልክተው በክታባቸው እንዳስቀመጡት በአራቱ ወንጌላውያን ዘመኑን ይከፍሉታል፡፡ ምክንያቱም በዘመነ ዮሐንስ ተፀንሶ በዘመነ ማቴዎስ ተወልዶአል፡፡ በዘመነ ማርቆስ ተጠምቋል፡፡ በዘመነ ሉቃስ ተሰቅሎ ዓለምን ከፍዳና ከመርገም ነጻ አውጥቷል፤ እያሉ ታሪካዊ ሐረጋቸውን ጠብቆ አራቱ ወንጌላውያን ተከትለው ያለ እንቅፋት እንደሚጓዙ ያስረዳሉ:: #እንቁጣጣሽ ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ የጠቢቡ ሰሎሞንን ዝና ሰምታ ኢየሩሳሌም ተጉዛ ስትመለስ “እንቁ ለጣትሽ /ለጣትሽ እንቁ/ በማለት ከእንቁ የተሠራ የጣት ቀለበት ንጉሥ ሰሎሞን እጅ መንሻ እንዲሆናት አበርክቶላት ነበርና ይህን ታሪክ መነሻ አድርገው “እንቁጣጣሽ” የሚለው ስያሜ ከዚያ እንደመጣ የታሪክ ድርሳናት ያስረዱናል ፡፡ በኢትዮጵያ የዘመን መለወጫ ዕለት ምድሪቱ በክረምቱ ዝናብ ረስርሳ ድርቀቷ ተወግዶ በአርንጓዴ እጸዋት ተውባ ሜዳው፣ ሸለቆውና ተራራው በአደይ አበባ ተንቆጥቁጠው የሚታዩበት ወቅት በመሆኑ ዕለቱ “እንቁጣጣሽ” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ በዚህ ወቅት ሕፃናትና ልጃገረዶች ነጭ ባሕላዊ ልብስ በመልበስ ለምለም ቄጤማና አደይ አበባ በመያዝ በአካባቢያቸው በመዞር አዲስ ዘመን መበሠሩን “እንኳን አደረሳችሁ” በማለት በቸርነቱ ዓመታትን የሚያፈራርቀውን እግዚአብሔርን በዝማሬ ያመሰግናሉ፡፡ መልካም_አዲስ_ዓመት #Share

#ጳጉሜ_ሦስት #አንኳን_ለሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሩፋኤል_በዓለ_ሲመቱ_ቅዳሴ_ቤቱ_እና_ለአቡን_መልከ_ጼዴቅ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓል_በሰላም_አደረሳቹ #ቅዱስ_ሩፋኤል ከሊቃነ መላእክት ሦስተኛው ሲሆን የስሙ ትርጓሜ እግዚአብሄር ሐኪሜ ነው ማለት ነው፡፡ የመጀመሪያው ዕድል ፋንታውም ራማ ነበረች ከዛም መናብርት(በራማ ሰማይ ሁለተኛ ክፍል ላይ የሰፈሩ፣በነገድ 10 ለሚሆኑ፣ በፍጥነታቸው እጅግ ረቂቃን ፤ ከነፍስ ይለቅ የሚፈጥኑ ) ተብለው ሊሚጠሩ መላእክት አለቃ ሆኖ ተሹማል ቦኃላም መጋብያን ለሚባሉ ሃያ ሶስቱ ነገድ ሾሞታል፡፡ ይህችም ዕለት በዓለ #ሲመቱ ናት፡፡ሰማያዊውን መዝገብ (መዝገበ ፀሎት) ላይ የተሾመ ነው ❖ ሐዋርያትም ጌታችንን ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲያስተዋውቃቸው በለመኑት ጌዜ ፡ጌታም ሦስቱን ሊቃናት ጠራቸው ቅዱስ ሩፋኤልንም ክብሩን እንዲንግራቸው ጌታችን አዘዘው ፤ ቅዱስ ሩፋኤልም በዙ ምስጢራትምን አና ስለ ቃልኪዳኑ ( ስሙን ለሚጠሩ እና መታሰቢያውን ለሚያደርጉ ) ነግሮዋቸዋል በመጽሐፈ ጦቢት ለይ ተጽፎ እንደምናገኝው እርሱ አዛርያን መስሎ ጦብያን ለትዳር አብቅቶ ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ፡ የጦቢትን ዓይን አብርቷል፡፡ ❖ በዚህችም ዕለት ከእስክንድርያ ውጪ በደሴት የታነፀች ፡ በከበር ሊቀ ጳጳስ ቴዎፍሎስ ዘመን በውስጧ ተአምር የገለፀባት የከበረችበት ዕለት ነው:: ( #ቅዳሴ ቤቱ)፡፡ ይህም እንዲህ ነው ሃብታም ሴት ከብዙ ሰው ጋር ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ መጣች ፡ ከባሏም የወረሰችው ብዙ ገንዘብ አላት በእርሱም ቤት አንጻር ያለውን ኮረብታ አስቆፈረችው በጥቅምት ወር ዐሥራ ስምንት ቀን እንደጻፍን የወርቅ መዝገብ ተገለጠ፡፡ በዚያም ወርቅ ብዙዎች አብያተ ቤተክርስቲያናትን አነፀ ፤ ከነርሱም አንዲቱ በመልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ስም የታነጸች ናት፡፡ ተሠርታም ባለቀች ጌዜ በዚህች ቀን አከበራት ፡፡ ብዙ ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈጽማ ተናወጸች ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና የሰዎቹ ብዛትም በከበደው ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሳሳው፡፡ ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሄር በከበረ ጩኅት ወደ እግዚአብሄር ጮሁ፡፡ ያን ጊዜም የከበረ ቅዱስ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ እንዲ አለው "እግዚአብሄር አዞካል እና ሳትናወጽ ፀጥ ብለክ ቁም" ፡፡ አንበሪውም ጸጥ ብሎ ቆመ አልታወከም በውስጧም ድንቅ ተአምሮች ተገለጡ ለህሙማንም ፈውስ ሆነ፡፡ ❖ ይህችም ቤተክርስቲያን እስላሞች እስከ ተነሱባት ኖረች ከዚህም ቦሃላ ለሁለተኛ ጊዜ ያ አንበሪ ተናወጻ ደሴቲቱም በላይዋ ከሚኖሩ ብዙ ሕዝብ ጋር ሰመጠች ፡፡ #ቅዱስ_ሩፋኤል · መስተፈስሒ (ልቡናን ደስ የሚያሰኝ) · አቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት) · መዝገበ ፀሎት ( የፀሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው) · ለቀ መናብርት · ፈታሔ ማኅጸን እንዲሁም ምጥን የሚያቀል እየተባለም ይጠራል፡፡ ምልጃውና ጠብቆቱ አይለየን #ካህኑ_መልከ_ጼድቅ ካህኑ መልከ ጼድቅ ቅዱስ "ጳውሎስ ለመልኩ ቁጥር የለውም ለዘመኑም ጥንትና ፍጻሜ የለውም "ይለዋል ዕብ 7÷3 ሐዋርያው ይህንን ያለው ለወልደ እግዚአብሔር ምሳሌ ሲያደርገው እንጂ ትውልዱም ከነገደ ካም ነው፡፡ ወላጆቹም ሚልኪ እና ሰሊማ ይባላሉ ገና ከእናቱ ማኅፀን የተመረጠ ቅዱስ ካህን ፡ ንጉሠ ሳሌም ይባላል፡፡ ካህኑ መልከ ጼድቅ እጅግ ክቡርም ነው ፡፡ አባታችን አብርሃም ጠላቶቹን ድል አድርጎ ከምርኮ በተመለሰ ጊዜም ካህኑ ሊቀበለው ወይኑን እና ህብሰቱን ይዞ መጣ፡፡ ወይኑን እና ህብሰቱን የ ቅዱስ ሥጋ እና ደሙ ካህኑ መልከ ጼድቅ የካህናት ፣ አበ ብዙኃን አብርሃም ደግሞ የምእመናን ምሳሌ ሆነዋል፡፡ #ጳጉሜ_ሦስት #ኢትዮጽያዊው ንጉሥ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዕረፍቱ ነው #ርኃወተ_ሰማይ ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት አራተኛዋ መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት ለሰው ልጆች ከፍጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች ርኃወተ ሰማይ፤ ሰማይ የሚከፍትባት ቀን ተብላለች፡፡ ሰማይ መከፍት መዘጋት ኖሮበት ሳይሆን ፤ መላእክት የሰው ልጆችን ልመና ያለከልካይ የሚያሳርጉበት ዕለት ስለሆነ አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የፀሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንዲህ ተባለ እንጂ፡፡ ✞ #እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለአጼ ናኦድ እንደነገረችው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳ ስለሚታሰቡ ፡ የእግዚአብሄር የምሕረቱት መዝገቡ ስለሚከፈት፡ ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል፡፡ በቅዱስ ሩፋኤል መሪነት በዚህች ዕለት ለዓመት የሚበቃ ምህረት ይገኛል፡፡ ስለዚህም አባቶቻችን በዚ ዕለት 365 አቡነ ዘበሰማያት ሲጸልዩ ያድራሉ ፡፡ የጌታ ምጽአት ጭም የሚታሰብባት ዕለት ናት፡፡ በረከቱ ይድረሰን አሜን

የጳጕሜን መርኃ ግብር፤ ፠መጨረሻው ቀን ይህንን ይመስላል፠ መዝሙር በዘማሪት ጽጌ ማርያም እና ዲ/ን አብርሃም ይመልከቱ፡፡ https://youtu.be/iIAiFxEeCtk
የጳጕሜን መርኃ ግብር፤ ፠መጨረሻው ቀን ይህንን ይመስላል፠ መዝሙር በዘማሪት ጽጌ ማርያም እና ዲ/ን አብርሃም ይመልከቱ፡፡ https://youtu.be/iIAiFxEeCtk

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 6h · #እንኳን ደስ አላቹህ #በሰንበት ት/ቤታችን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አዘጋጅነት ትምህርት ሰጪነት እና አስተባባሪንተ ከነሐሴ 11 አስከ ጳጕሜን 1 በኦሮሚኛ ቋንቋ ሲሰጥ የቆየውን የተተኪ መምህራን ስልጠና ብፁዕነታቸው አቡነ ናተናኤል በተገኙበት በትላንተናው ዕለት (ጳጕሜን 1፤ 2012 ዓ.ም) 15 ተማሪዎችን አስመርቋል ፡፡ በምርቃቱ ላይ የጮቢ ወረዳ ቤተክህነተ ጸሐፊ፣ የከታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤ/ክ አስተዳዳሪ ፣አንዲሁም የእግዚአብሄር አብ ቤ/ክ የጸበል ቤት ኃላፊ የሆኑት በኲረ ምዕመናን ክፍለ ማርያም ተገኝተዋል፡፡ ምርቃቱ የተካሄደው በከታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም ሲሆን ከተመረቁት 15 ተማሪዎች ዘጠኙ ዲቁናን ከአቡነ ናትናኤል ተቀብለዋል፡፡ ሁለቱ ደግሞ አናቦንስጢስ ተባርከዋል ፡፡ #የተመረቁት ተማሪዎች የተወጣጡት በጮቢ ወረዳ ከሚገኙት ከ11 ቤተክርስቲያኖች መካከል ከሶስቱ ማለትም፤-ከ ጮቢ መድኃኔዓለም ፣ ከመጠቆሚያ ማርያም እና ከኦፉ ሚካኤል ነው፡፡ #የመማርያ ቦታ ላመቻቹት ለከታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም እና ለፍኖተ ሰላም ሰ/ትቤት ፣ በአገልግሎቱ ላይ ለተባበሩ እና ላስተባበሩ አገልጋዮች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡ለተመረቁትም ተማሪዎችም የምስክር ወረቀት ተሰቷል፡፡ #በጮቢ ወረዳ ከሚከኙት 11 አብያተ ክርስቲያኖት ፤ አንድና ሁለት አባ ወራዎች ብቻ የሚገኙባቸው ሁለት ቤተክርስቲያኖች ስላሉ ሕንጻው ፈርሶ አጸዱ ብቻ ቀርቷል ፡፡በተጨማሪም ከ 11 ደግም ሁለቱ ፤ስምንት እና አስር ብቻ የሚጠጉ አባወራዎች ስላሉት የሁለቱም ደብር ታቦታት ወደ ጮቢ መድኃኔዓለም እና መጠቆሚያ ማርያም ሄደዋል፡፡ ስለዚህም ይህን የምናነብ ሁላችን ወደፊት ትልቅ ስራ እንደሚጠብቀን ልብ ልንል ይገባል፡፡ #ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት ለተመረቁት ትማሪዎች በድጋሚ እንኳን ደስ አላቹህ አያለ መልካም የአገልግሎት ዘመንን ይመኛል ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሄር

#ጳጕሜን_ ዓመትን በዘመናት ስንከፋፍለው በ4ት ዘመናት ይከፈላል፤ ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ዘመነ ክረምት (ከሰኔ 26 እስከ መስከረም 25) ነው፤ በዘመነ ክረምት ውስጥ ደግሞ ከሚውሉት መካከል ከነሐሴ 28 እስከ ጳጕሜን ፭ት (በሠግር ዓመት ፮ት) ድረስ ያለው #ዘመነ_በርዮድ_ ይባላል፤ ይህም ወደ አዲስ ዘመን የሚያሻግረን ነው፡፡ በቅዱስ ያሬድ ድጓ መሠረትም ጎሕ (ውጋገን)፣ ነግህ (ንጋት)፣ ጽባሕ (ጥዋት)፣ ብርሃን፣ መዓልት (ዕለት)፣ ጌና (ልደት) ይባላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም (ዘመንን ቀንን በቊጥር ሰጣቸው፣ በውስጧም ያለውን ፍጥረት አስገዛቸው፡፡) እንዲል /ሲራክ 17፥2/ ጳጕሜን ማለት ጭማሪ ማለት ነው፤ ይህም በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት በስድስት መቶ ዓመት አንዴ ደግሞ ሰባት ቀን በመሆን የምትመጣ ናት፡፡ ጳጕሜን በአራት ዓመት አንዴ (ማለትም በዘመነ ሉቃስ መጨረሻ በዘመነ ዮሐንስ ቅበላ ስድስት ቀን ትሆናለች)፡፡ በዚህም ሃገራችን ኢትዮጵያ የዐሥራ ሦስት ወራት ጸጋ /Thirty months of sunshine/ በመባል ትታወቃች፡፡ #የጳጕሜን_ጾም_ጾመ_ዮዲት_ በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጕሜን ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም በተጨማሪ ጾመ ዮዲት በመባል ይታወቃል፤ ጾሙ እንደ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው፡፡ ጾመ ዮዲት የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ /እዚህ ላይ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ላይ በጥፋት ሥራዋ በተደጋጋሚ የምትጠቀሰው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡/ ወደ ታሪኩ ስንመለስ የፋርስ ንጉሥ ናቡከደነጾር በሠራዊቱ ተመክቶ ሹም ጠላት አጥፋ፥ ድንበር አስፋ፤ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልህ፥ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ /ዮዲት 2፥2-7/፡፡ እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ 12ሺህ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡ 12ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሔድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ በዚህም ብዙ ጥፋት በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡ ዮዲት ባሏ ሞቶባት፤ ከወንድ ርቃ፥ ንጽሕናዋን ጠብቃ፥ በጾም፥ በቀኖና፥ በሐዘን ተወስና የምትኖር ነበረችና፤ በተፈጠረው ጥፋት ሕዝቡ ላይ ለመጣው መከራ፤ ማቅ ለብሳ፥ በራስዋ ላይ ትብያ ነስንሳ ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች፡፡ የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ እግዚአብሔር አምላክን ሕዝቡ የሚድኑበትን መንገድ ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ገለጸላት /ዮዲት 8፥2/ ፡፡ ከዚህ በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት እስራኤላውያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል፡፡ ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይል አግኝታ ነው፡፡ ስለዚህ ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንንና ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን ለመጎናጸፍ ጳጕሜን በፈቃድ እንጾማለን፡፡ #ጳጕሜን_የዕለተ_ምጽአት_መታሰቢያ_ የጳጕሜን ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትም ወር ነው፡፡ ይህም ጳጕሜን የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ፤ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ፥ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና ነው፡፡ #ጠበል_በወርኀ_ጳጕሜን_ ክርስቲያኖች ሁሉ በየዓመቱ በጳጕሜ ወር ሁሉም ተሰብስበው ከሌሊት ጀምረው በቤተክርስቲያን ተገኝተው ጠበል ይጠመቃሉ፡፡ ይህንን የምናደገውም እግዚአብሔር የተባረከ ዓመት እንዲሰጠን፣ ባሳለፍነው ዓመት የሰራነውን ኃጢአት ይቅር እንዲለን ነው፡፡ የምንጠመቀውም ንስሐ ገብተን ነው፡፡ በእግዚአብሔር ስም የተቀደሰው ጠበል ደግሞ ከበሽታችን ያድነናል፥ የተቀደስንም ያደርገናል፤ መጪውንም ሕይወታችን የተባረከ ያደርግልናል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ መልካም የአዲስ ዓመት ዋዜማ ጷጕሜን ይሁንልን፡፡