Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 373 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 571,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 195 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 373 名订阅者。
根据 05 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 30,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.23%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.08% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 418 次浏览,首日通常累积 1 397 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 20。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 06 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 373
订阅者
-424 小时
-197 天
+3030 天
帖子存档
የዛሬው የችቦ ማብራት ሰርዓት በፎቶ
፨መልካም የአገልግሎት ዘመን ፨
✞
#በዓለ_ርዕሰ_ዐውደ_ዓመት_ዮሐንስ_ወቅዱስ_ራጉኤል
#እንኳን_አደረሳቹ
#አዲስ_ዓመት
ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ የመሸጋገሪያው ዕለት በየዓመቱ ቅዱስ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራል፡፡ የዘመን መለወጫ፣ እንቁጣጣሽ፣ ሌላም መጠሪያ ስሞቹ ናቸው፡፡ በግእዝ ርእሰ ዐውደ ዓመትም ይባላል፡፡ ይህ በዓል የዓመት መጀመሪያ እንደመሆኑ መጠን በየዓመቱ ወሮች በመጀመሪያ ቀን ይከበራል፡፡ ያን ጊዜ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር እኩል 12 ሰዓት ይሆናል፡፡ ዓመቱን ጠንቅቀው ሲቆጥሩ 364 ቀናት ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ “ለዘመን መታወቂያው ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትንም ፈጠረ” ይላልና /ሔኖክ. 21፥49/፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ በፍል ውኃ አጥለቅልቆ በኃጢአት ሕይወት ይኖሩ የነበሩት የኖኅ ዘመን ሰዎች ቀጥቶ ካጠፋ በኋላ ከንፍር ውኃ ምድር የተገለጠችበት ወር ነው /ኩፋሌ. 7፥1/፡፡ “በመጀመሪያው ወር ምድር ታየች የንፍር ውኃም ከምድር ደረቀ” የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል መሠረት አድርገው የአቡሻኸር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥ ያስቀምጣሉ፡፡
✞
የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀኖናዊ ሥርዐት ያጠኑ ሊቃውንት ደግሞ አዲስ ዓመት መስከረም አንድ ቀን መሆኑን አስመልክተው በክታባቸው እንዳስቀመጡት በአራቱ ወንጌላውያን ዘመኑን ይከፍሉታል፡፡ ምክንያቱም በዘመነ ዮሐንስ ተፀንሶ በዘመነ ማቴዎስ ተወልዶአል፡፡ በዘመነ ማርቆስ ተጠምቋል፡፡ በዘመነ ሉቃስ ተሰቅሎ ዓለምን ከፍዳና ከመርገም ነጻ አውጥቷል፤ እያሉ ታሪካዊ ሐረጋቸውን ጠብቆ አራቱ ወንጌላውያን ተከትለው ያለ እንቅፋት እንደሚጓዙ ያስረዳሉ::
#እንቁጣጣሽ
ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ የጠቢቡ ሰሎሞንን ዝና ሰምታ ኢየሩሳሌም ተጉዛ ስትመለስ “እንቁ ለጣትሽ /ለጣትሽ እንቁ/ በማለት ከእንቁ የተሠራ የጣት ቀለበት ንጉሥ ሰሎሞን እጅ መንሻ እንዲሆናት አበርክቶላት ነበርና ይህን ታሪክ መነሻ አድርገው “እንቁጣጣሽ” የሚለው ስያሜ ከዚያ እንደመጣ የታሪክ ድርሳናት ያስረዱናል ፡፡ በኢትዮጵያ የዘመን መለወጫ ዕለት ምድሪቱ በክረምቱ ዝናብ ረስርሳ ድርቀቷ ተወግዶ በአርንጓዴ እጸዋት ተውባ ሜዳው፣ ሸለቆውና ተራራው በአደይ አበባ ተንቆጥቁጠው የሚታዩበት ወቅት በመሆኑ ዕለቱ “እንቁጣጣሽ” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
በዚህ ወቅት ሕፃናትና ልጃገረዶች ነጭ ባሕላዊ ልብስ በመልበስ ለምለም ቄጤማና አደይ አበባ በመያዝ በአካባቢያቸው በመዞር አዲስ ዘመን መበሠሩን “እንኳን አደረሳችሁ” በማለት በቸርነቱ ዓመታትን የሚያፈራርቀውን እግዚአብሔርን በዝማሬ ያመሰግናሉ፡፡
መልካም_አዲስ_ዓመት
#Share
#ጳጉሜ_ሦስት
#አንኳን_ለሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሩፋኤል_በዓለ_ሲመቱ_ቅዳሴ_ቤቱ_እና_ለአቡን_መልከ_ጼዴቅ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓል_በሰላም_አደረሳቹ
#ቅዱስ_ሩፋኤል ከሊቃነ መላእክት ሦስተኛው ሲሆን የስሙ ትርጓሜ እግዚአብሄር ሐኪሜ ነው ማለት ነው፡፡ የመጀመሪያው ዕድል ፋንታውም ራማ ነበረች ከዛም መናብርት(በራማ ሰማይ ሁለተኛ ክፍል ላይ የሰፈሩ፣በነገድ 10 ለሚሆኑ፣ በፍጥነታቸው እጅግ ረቂቃን ፤ ከነፍስ ይለቅ የሚፈጥኑ ) ተብለው ሊሚጠሩ መላእክት አለቃ ሆኖ ተሹማል ቦኃላም መጋብያን ለሚባሉ ሃያ ሶስቱ ነገድ ሾሞታል፡፡ ይህችም ዕለት በዓለ #ሲመቱ ናት፡፡ሰማያዊውን መዝገብ (መዝገበ ፀሎት) ላይ የተሾመ ነው
❖
ሐዋርያትም ጌታችንን ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲያስተዋውቃቸው በለመኑት ጌዜ ፡ጌታም ሦስቱን ሊቃናት ጠራቸው ቅዱስ ሩፋኤልንም ክብሩን እንዲንግራቸው ጌታችን አዘዘው ፤ ቅዱስ ሩፋኤልም በዙ ምስጢራትምን አና ስለ ቃልኪዳኑ ( ስሙን ለሚጠሩ እና መታሰቢያውን ለሚያደርጉ ) ነግሮዋቸዋል
በመጽሐፈ ጦቢት ለይ ተጽፎ እንደምናገኝው እርሱ አዛርያን መስሎ ጦብያን ለትዳር አብቅቶ ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ፡ የጦቢትን ዓይን አብርቷል፡፡
❖
በዚህችም ዕለት ከእስክንድርያ ውጪ በደሴት የታነፀች ፡ በከበር ሊቀ ጳጳስ ቴዎፍሎስ ዘመን በውስጧ ተአምር የገለፀባት የከበረችበት ዕለት ነው:: ( #ቅዳሴ ቤቱ)፡፡
ይህም እንዲህ ነው ሃብታም ሴት ከብዙ ሰው ጋር ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ መጣች ፡ ከባሏም የወረሰችው ብዙ ገንዘብ አላት በእርሱም ቤት አንጻር ያለውን ኮረብታ አስቆፈረችው በጥቅምት ወር ዐሥራ ስምንት ቀን እንደጻፍን የወርቅ መዝገብ ተገለጠ፡፡
በዚያም ወርቅ ብዙዎች አብያተ ቤተክርስቲያናትን አነፀ ፤ ከነርሱም አንዲቱ በመልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ስም የታነጸች ናት፡፡ ተሠርታም ባለቀች ጌዜ በዚህች ቀን አከበራት ፡፡
ብዙ ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈጽማ ተናወጸች ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና የሰዎቹ ብዛትም በከበደው ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሳሳው፡፡
ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሄር በከበረ ጩኅት ወደ እግዚአብሄር ጮሁ፡፡ ያን ጊዜም የከበረ ቅዱስ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ እንዲ አለው "እግዚአብሄር አዞካል እና ሳትናወጽ ፀጥ ብለክ ቁም" ፡፡ አንበሪውም ጸጥ ብሎ ቆመ አልታወከም በውስጧም ድንቅ ተአምሮች ተገለጡ ለህሙማንም ፈውስ ሆነ፡፡
❖
ይህችም ቤተክርስቲያን እስላሞች እስከ ተነሱባት ኖረች ከዚህም ቦሃላ ለሁለተኛ ጊዜ ያ አንበሪ ተናወጻ ደሴቲቱም በላይዋ ከሚኖሩ ብዙ ሕዝብ ጋር ሰመጠች ፡፡
#ቅዱስ_ሩፋኤል
· መስተፈስሒ (ልቡናን ደስ የሚያሰኝ)
· አቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት)
· መዝገበ ፀሎት ( የፀሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው)
· ለቀ መናብርት
· ፈታሔ ማኅጸን እንዲሁም ምጥን የሚያቀል
እየተባለም ይጠራል፡፡
ምልጃውና ጠብቆቱ አይለየን
#ካህኑ_መልከ_ጼድቅ
ካህኑ መልከ ጼድቅ ቅዱስ "ጳውሎስ ለመልኩ ቁጥር የለውም ለዘመኑም ጥንትና ፍጻሜ የለውም "ይለዋል ዕብ 7÷3 ሐዋርያው ይህንን ያለው ለወልደ እግዚአብሔር ምሳሌ ሲያደርገው እንጂ ትውልዱም ከነገደ ካም ነው፡፡ ወላጆቹም ሚልኪ እና ሰሊማ ይባላሉ
ገና ከእናቱ ማኅፀን የተመረጠ ቅዱስ ካህን ፡ ንጉሠ ሳሌም ይባላል፡፡ ካህኑ መልከ ጼድቅ እጅግ ክቡርም ነው ፡፡
አባታችን አብርሃም ጠላቶቹን ድል አድርጎ ከምርኮ በተመለሰ ጊዜም ካህኑ ሊቀበለው ወይኑን እና ህብሰቱን ይዞ መጣ፡፡ ወይኑን እና ህብሰቱን የ ቅዱስ ሥጋ እና ደሙ ካህኑ መልከ ጼድቅ የካህናት ፣ አበ ብዙኃን አብርሃም ደግሞ የምእመናን ምሳሌ ሆነዋል፡፡
#ጳጉሜ_ሦስት #ኢትዮጽያዊው ንጉሥ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዕረፍቱ ነው
#ርኃወተ_ሰማይ
ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት አራተኛዋ መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት ለሰው ልጆች ከፍጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች ርኃወተ ሰማይ፤ ሰማይ የሚከፍትባት ቀን ተብላለች፡፡
ሰማይ መከፍት መዘጋት ኖሮበት ሳይሆን ፤ መላእክት የሰው ልጆችን ልመና ያለከልካይ የሚያሳርጉበት ዕለት ስለሆነ አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የፀሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንዲህ ተባለ እንጂ፡፡
✞
#እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለአጼ ናኦድ እንደነገረችው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳ ስለሚታሰቡ ፡ የእግዚአብሄር የምሕረቱት መዝገቡ ስለሚከፈት፡ ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል፡፡
በቅዱስ ሩፋኤል መሪነት በዚህች ዕለት ለዓመት የሚበቃ ምህረት ይገኛል፡፡
ስለዚህም አባቶቻችን በዚ ዕለት 365 አቡነ ዘበሰማያት ሲጸልዩ ያድራሉ ፡፡ የጌታ ምጽአት ጭም የሚታሰብባት ዕለት ናት፡፡
በረከቱ ይድረሰን አሜን
የጳጕሜን መርኃ ግብር፤
፠መጨረሻው ቀን ይህንን ይመስላል፠
መዝሙር በዘማሪት ጽጌ ማርያም እና ዲ/ን አብርሃም
ይመልከቱ፡፡
https://youtu.be/iIAiFxEeCtk
የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
6h ·
#እንኳን ደስ አላቹህ
#በሰንበት ት/ቤታችን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አዘጋጅነት ትምህርት ሰጪነት እና አስተባባሪንተ ከነሐሴ 11 አስከ ጳጕሜን 1 በኦሮሚኛ ቋንቋ ሲሰጥ የቆየውን የተተኪ መምህራን ስልጠና ብፁዕነታቸው አቡነ ናተናኤል በተገኙበት በትላንተናው ዕለት (ጳጕሜን 1፤ 2012 ዓ.ም) 15 ተማሪዎችን አስመርቋል ፡፡
በምርቃቱ ላይ የጮቢ ወረዳ ቤተክህነተ ጸሐፊ፣ የከታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤ/ክ አስተዳዳሪ ፣አንዲሁም የእግዚአብሄር አብ ቤ/ክ የጸበል ቤት ኃላፊ የሆኑት በኲረ ምዕመናን ክፍለ ማርያም ተገኝተዋል፡፡
ምርቃቱ የተካሄደው በከታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም ሲሆን ከተመረቁት 15 ተማሪዎች ዘጠኙ ዲቁናን ከአቡነ ናትናኤል ተቀብለዋል፡፡ ሁለቱ ደግሞ አናቦንስጢስ ተባርከዋል ፡፡
#የተመረቁት ተማሪዎች የተወጣጡት በጮቢ ወረዳ ከሚገኙት ከ11 ቤተክርስቲያኖች መካከል ከሶስቱ ማለትም፤-ከ ጮቢ መድኃኔዓለም ፣ ከመጠቆሚያ ማርያም እና ከኦፉ ሚካኤል ነው፡፡
#የመማርያ ቦታ ላመቻቹት ለከታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም እና ለፍኖተ ሰላም ሰ/ትቤት ፣ በአገልግሎቱ ላይ ለተባበሩ እና ላስተባበሩ አገልጋዮች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡ለተመረቁትም ተማሪዎችም የምስክር ወረቀት ተሰቷል፡፡
#በጮቢ ወረዳ ከሚከኙት 11 አብያተ ክርስቲያኖት ፤ አንድና ሁለት አባ ወራዎች ብቻ የሚገኙባቸው ሁለት ቤተክርስቲያኖች ስላሉ ሕንጻው ፈርሶ አጸዱ ብቻ ቀርቷል ፡፡በተጨማሪም ከ 11 ደግም ሁለቱ ፤ስምንት እና አስር ብቻ የሚጠጉ አባወራዎች ስላሉት የሁለቱም ደብር ታቦታት ወደ ጮቢ መድኃኔዓለም እና መጠቆሚያ ማርያም ሄደዋል፡፡ ስለዚህም ይህን የምናነብ ሁላችን ወደፊት ትልቅ ስራ እንደሚጠብቀን ልብ ልንል ይገባል፡፡
#ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት ለተመረቁት ትማሪዎች በድጋሚ እንኳን ደስ አላቹህ አያለ መልካም የአገልግሎት ዘመንን ይመኛል ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሄር
#ጳጕሜን_
ዓመትን በዘመናት ስንከፋፍለው በ4ት ዘመናት ይከፈላል፤ ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ዘመነ ክረምት (ከሰኔ 26 እስከ መስከረም 25) ነው፤ በዘመነ ክረምት ውስጥ ደግሞ ከሚውሉት መካከል ከነሐሴ 28 እስከ ጳጕሜን ፭ት (በሠግር ዓመት ፮ት) ድረስ ያለው #ዘመነ_በርዮድ_ ይባላል፤ ይህም ወደ አዲስ ዘመን የሚያሻግረን ነው፡፡ በቅዱስ ያሬድ ድጓ መሠረትም ጎሕ (ውጋገን)፣ ነግህ (ንጋት)፣ ጽባሕ (ጥዋት)፣ ብርሃን፣ መዓልት (ዕለት)፣ ጌና (ልደት) ይባላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም (ዘመንን ቀንን በቊጥር ሰጣቸው፣ በውስጧም ያለውን ፍጥረት አስገዛቸው፡፡) እንዲል /ሲራክ 17፥2/
ጳጕሜን ማለት ጭማሪ ማለት ነው፤ ይህም በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት በስድስት መቶ ዓመት አንዴ ደግሞ ሰባት ቀን በመሆን የምትመጣ ናት፡፡ ጳጕሜን በአራት ዓመት አንዴ (ማለትም በዘመነ ሉቃስ መጨረሻ በዘመነ ዮሐንስ ቅበላ ስድስት ቀን ትሆናለች)፡፡ በዚህም ሃገራችን ኢትዮጵያ የዐሥራ ሦስት ወራት ጸጋ /Thirty months of sunshine/ በመባል ትታወቃች፡፡
#የጳጕሜን_ጾም_ጾመ_ዮዲት_
በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጕሜን ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም በተጨማሪ ጾመ ዮዲት በመባል ይታወቃል፤ ጾሙ እንደ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው፡፡ ጾመ ዮዲት የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ /እዚህ ላይ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ላይ በጥፋት ሥራዋ በተደጋጋሚ የምትጠቀሰው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡/ ወደ ታሪኩ ስንመለስ የፋርስ ንጉሥ ናቡከደነጾር በሠራዊቱ ተመክቶ ሹም ጠላት አጥፋ፥ ድንበር አስፋ፤ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልህ፥ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ /ዮዲት 2፥2-7/፡፡ እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ 12ሺህ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡ 12ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሔድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ በዚህም ብዙ ጥፋት በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡
ዮዲት ባሏ ሞቶባት፤ ከወንድ ርቃ፥ ንጽሕናዋን ጠብቃ፥ በጾም፥ በቀኖና፥ በሐዘን ተወስና የምትኖር ነበረችና፤ በተፈጠረው ጥፋት ሕዝቡ ላይ ለመጣው መከራ፤ ማቅ ለብሳ፥ በራስዋ ላይ ትብያ ነስንሳ ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች፡፡ የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ እግዚአብሔር አምላክን ሕዝቡ የሚድኑበትን መንገድ ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ገለጸላት /ዮዲት 8፥2/ ፡፡ ከዚህ በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት እስራኤላውያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል፡፡
ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይል አግኝታ ነው፡፡ ስለዚህ ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንንና ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን ለመጎናጸፍ ጳጕሜን በፈቃድ እንጾማለን፡፡
#ጳጕሜን_የዕለተ_ምጽአት_መታሰቢያ_
የጳጕሜን ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትም ወር ነው፡፡ ይህም ጳጕሜን የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ፤ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ፥ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና ነው፡፡
#ጠበል_በወርኀ_ጳጕሜን_
ክርስቲያኖች ሁሉ በየዓመቱ በጳጕሜ ወር ሁሉም ተሰብስበው ከሌሊት ጀምረው በቤተክርስቲያን ተገኝተው ጠበል ይጠመቃሉ፡፡ ይህንን የምናደገውም እግዚአብሔር የተባረከ ዓመት እንዲሰጠን፣ ባሳለፍነው ዓመት የሰራነውን ኃጢአት ይቅር እንዲለን ነው፡፡ የምንጠመቀውም ንስሐ ገብተን ነው፡፡ በእግዚአብሔር ስም የተቀደሰው ጠበል ደግሞ ከበሽታችን ያድነናል፥ የተቀደስንም ያደርገናል፤ መጪውንም ሕይወታችን የተባረከ ያደርግልናል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
መልካም የአዲስ ዓመት ዋዜማ ጷጕሜን ይሁንልን፡፡
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
