KUE Community / አዲስ ነገር መረጃ /
Kanalga Telegram’da o‘tish
4 164
Obunachilar
+324 soatlar
-37 kunlar
-1830 kunlar
Postlar arxiv
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በደብረብርሀን እና አሰላ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ያሰለጠናቸውን 2,349 የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራንን አስመረቀ።
(ሰኔ 20/2018 ዓ.ም) በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው የምርቃት መርሀ ግብር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ስትራቴጂክ ካውንስል አባላትን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት አመራሮች፣የሁለቱ ኮሌጆች ዲኖችና መምህራን እንዲሁም የተመራቂ ቤተሰቦችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊና የመርሀግብሩ የክብር እንግዳ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ባስተላለፉት መልዕክት በከተማ አስተዳደሩ የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ተግባራዊ በማድረግ አዲስ አበባን ህጻናትን ለማሳደግ ምቹና ተመራጭ አፍሪካዊት ከተማ ለማድረግ እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በጫወታ የማስተማር ስነ ዘዴን ተግባራዊ በማድረግ በተማሪዎቹ ሁለንተናዊ እድገት ላይ መስራት መሆኑን አመላክተዋል።
ኃላፊው አያይዘውም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ህጻናቱ ለቀጣዩ የትምህርት ደረጃዎች መሰረት የሚጥሉበት የትምህርት እርከን እንደመሆኑ በዛሬው እለት የተመረቁ መምህራን በኮሌጆቹ በነበራቸው ቆይታ ባገኙት ዕውቀትና ክህሎት መሰረት በጫወታ የማስተማር ስነዘዴን በአግባቡ በመተግበር ተማሪዎችን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባቸው በመግለጽ ሁለቱን ኮሌጆች ጨምሮ ለመርሀግብሩ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አበራ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ የቅድመ አንደኛ ትምህርትን ውጤታማ ለማድረግ መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ ለተቋማቱን ግብአት ከማቅረብ ጀምሮ ለመምህራን ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰው በደብረ ብርሀን አሰላ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ተምረው በዛሬው እለት የተመረቁ መምህራንም የዚሁ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን በመግለጽ ለተመራቂዎች መልካም እድል ተመኝተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ከትምህርት ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑን የማህበሩ ፕሬዘዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ ገልጸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከሁለቱ ኮሌጆች ጋር በጋራ በመሆን መምህራኑን አሰልጥኖ በማስመረቁ በማህበራቸውና በተመራቂ መምህራን ስም ምስጋና አቅርበዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
የሙአዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ልጅ ተመርቋል!
#maleda :የእውቀትና የጥበብ ፍሬዎች ሲጎመሩ ማየት ለወላጅም ለሀገርም ትልቅ ደስታ ነው። ዛሬ በሀገራችን የኪነ-ጥበብና የማኅበራዊ ሕይወት ዘርፍ ጉልህ አሻራ ያኖሩት የሙአዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ልዩ የወላጅነት ኩራት ያጣጣሙበት ታሪካዊ ቀን ሆኗል።
የዲ/ን ዳንኤል ክብረት ልጅ አቤሜሌክ ዳንኤል ረጅም የታማኝነትና የጥናት ዓመታትን በስኬት አጠናቆ፣ ዛሬ ከአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ተመርቋል።
የአባት አደራ እና የራስ ጥረት ሲገናኙ ውጤቱ ሁልጊዜም ማማር ነው!"
ይህ የምረቃ ቀን የወጣቱ አቤሜሌክ የልፋት ውጤት ብቻ ሳይሆን፣ ልጆቻቸውን በዕውቀትና በስነ-ምግባር ቀርጸው ለዚህ ማዕረግ ያበቁት የወላጆቹ የድካም ፍሬ መገለጫ ጭምር ነው።
ለአቤሜሌክ ዳንኤል የወደፊት የሕይወትና የሥራ ዘመን ብሩህ እንዲሆንልህ እንመኛለን። ይህ የትምህርት መድረክ የትልቅ ጉዞ መጀመሪያ ይሁንህ! ከዩኒቨርሲቲው የቀሰምከው ዕውቀት ለራስህ የሚጠቅም፣ ለቤተሰብህ ኩራት የሚሆንና ለሀገርህም የሚተርፍ ፍሬ እንዲያፈራ ከልብ እንመኛለን።
ለአቤሜሌክ፣ ለዲ/ን ዳንኤል ክብረት እና ለመላው ቤተሰብ፦ እንኳን ደስ አላችሁ::
የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የምረቃ ስነስርዓት እየተካሄደ ነው
*** ** ***
(ኮትዩ፣ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም) ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በዲፕሎማ፣ በቅድመ ምረቃ፣ በድህረ ምረቃ ማለትም በማስትሬት እና በዶክትሬት ዲግሪ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 2882 ተማሪዎች በአደዋ ድል መታሰቢያ የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ በደማቅ ስነ-ስርዓት እያስመረቀ ነው፡፡
የምረቃ ስነስርዓቱ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እና የተማሪ ወላጆች በተገኙበት እየተከናወነ ሲሆን የ2018 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ!
- የህዝብ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት
#Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education
ለተጨማሪ መረጃ ይፋዊ ገጾቻችንን ይከታተሉ:
Facebook፡ https://web.facebook.com/www.kue.edu.et
Website: https://www.kue.edu.et/
YouTube: https://youtube.com/@kueducation
Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et)
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ2018ዓ.ም ለሁለተኛ ዙር ተማሪዎቹን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ፡፡
*****
(ባሌ-ሮቤ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ሕ.ዓ.ግ.ጽ)
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ለ18ኛ ጊዜ በተለያዩ ኮሌጆች ስር ያስተማራቸውን 1089/አንድ ሺ ሰማንያ ዘጠኝ /ተማሪዎቹን ነው በመጀመሪያ ድግሪ እና ማስተርስ ድግሪ በዛሬው እለት በደማቅ ሁኔታ ያስመረቀው፡፡
በምርቃቱ የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የአካደሚክ ፣ምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግር እና ማህበ/አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር በዛብህ ወንድሙ እንዳሉት መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ19 አመታት ቆይታው የዛሬዎቹን 1089 ተመራቂዎችን ጨምሮ ከሀምሳ ሺ በላይ /50,000/ በላይ ተማሪዎች አስተምሮ ማስመረቅ መቻሉን ገልጸዋል፡፡
የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እና የእለቱ የክብር እንግዳ የተከበሩ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ለተመራቂ ተማሪዎች እና ወላጆች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ካስተላለፉ በኋላ እንዳሉት ዛሬ እዚህ የተሰበሰብነው ለተራ ኩነት አይደለም፤ ህልም ወደ እውነት የተቀየረበትን ጉዞ ለማክበር ነው። ዛሬ የምናከብረው የትጋት ድል ነው፤ የጽናት ድል ነው፤ የወላጆች እንባ ወደ ደስታ የተለወጠበት ቀን ነው፤ የመምህራን ድካም ፍሬ ያፈራበት ቀን ነው።"የረጅም ጉዞ መጨረሻ የሌላ ጉዞ መጀመሪያ ነው። "ዛሬ አንድ ጉዞ ተጠናቋል፤ ነገር ግን ከዚህ በኋላ የምትጀምሩት ጉዞ ከዩኒቨርሲቲ ጉዞአችሁ የበለጠ ኃላፊነት፣ የበለጠ ፈተና እና የበለጠ እድል ያለው ነው ብለዋል፡፡
ክቡር ፐሬዝዳንቱ አክለውም ዛሬ የምትቀበሉት ዲግሪ በተለይ የጤና ባለሙያዎች ከሌሎች ሙያዎች የሚለየው አንድ ልዩ አደራ አለው። ከዛሬ ጀምሮ በእጃችሁ መሳሪያ ብቻ አይኖርም፤ የሰው ሕይወት አደራ ይኖራል።ታካሚ ወደ ሆስፒታል ሲመጣ ሁለት ነገሮችን ይዞ ይመጣል፤ ሕመሙን እና ተስፋውን። የምትሰጡት ሕክምና ሕመሙን ሊቀንስ ይችላል፤ ነገር ግን የምታሳዩት ርህራሄ፣ የምትናገሩት አጽናኝ ቃል እና የምትሰጡት ክብር ተስፋውን ያድሳል። የዛሬው ዓለም በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI)፣ በዲጂታል ጤና፣ በቴሌሜዲሲን እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እየተለወጠ ነው። ቴክኖሎጂ ብዙ ነገሮችን ልታደርግ ትችላለች፤ ግን ሰብዓዊ ርህራሄን፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባርን እና ሕሊናን ልትተካ አትችልም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በፕሮግሙ ማጠቃለያም ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተመራቂዎች ሜዳሊያ እና የዋንጫ ሽልማት ከክቡር ፕሬዝዳንቱ እጅ ተረክበዋል፡፡
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ጽ/ቤት
He thanked the organizers, facilitators, and participating teachers for their commitment and encouraged the graduates to apply the knowledge and skills they had acquired to enrich their professional practice and promote innovative, technology-enhanced education.
- Public and International Relations Executive Office
#Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education
Follow us for more information:
Facebook፡ https://web.facebook.com/www.kue.edu.et
Website: https://www.kue.edu.et/
YouTube:
https://youtube.com/@kueducation
Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et)
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook
The AI-Enhanced Pedagogy Training Workshop is Concluded Successfully at KUE
*** *** ***
(KUE, June 18, 2026) – Kotebe University of Education (KUE), in collaboration with the United States Embassy in Addis Ababa, successfully concluded a nine-day professional development workshop titled "AI-Enhanced Pedagogy," held from June 8–18, 2026.
According to the program coordinator, Dr. Dejen Chaka, the training focused on integrating artificial intelligence into education while emphasizing ethical principles, legal compliance, digital repositories, and the development of educational resources. The workshop empowered teachers to transition from being consumers of digital content to becoming creators of innovative learning materials. Participants gained practical experience in developing e-portfolios to showcase and store their digital work, creating e-books, designing interactive student worksheets using AI-powered tools like MagicSchool AI, enhancing language teaching skills, and exploring a wide range of other AI-supported educational applications.
During the closing ceremony, three participant representatives shared testimonials highlighting the practical knowledge, professional growth, and transformative experiences they gained throughout the training. They emphasized that the workshop had strengthened their confidence and equipped them with valuable digital skills that they will apply in their classrooms.
Delivering his closing remarks, the lead trainer, Professor Nega Worku Debela, reflected on the participants' inspiring journey of learning, discovery, and innovation over the past nine days. He noted that the workshop climaxed in remarkable achievements, with participants acquiring advanced digital competencies and AI-enhanced pedagogical skills that will significantly improve their professional practice. He explained that the teachers are now capable of developing and using their own AI-powered educational applications to teach English speaking, listening, reading, and writing more effectively, thereby creating engaging, innovative, and learner-centred classroom experiences.
Representing the United States Embassy in Addis Ababa, Mr. George, the Regional English Language Officer, commended both the trainers and participants for their commitment and hard work throughout the program. He expressed confidence that the knowledge and practical skills acquired during the workshop would foster continuous educational innovation, strengthen teaching quality, and contribute to preparing the next generation with the knowledge and skills needed for the future.
Speaking at the closing ceremony, Dr. Teshome Nekatibeb, President of Kotebe University of Education, stated that the training would make a significant contribution to improving the University's teaching and learning process. He highlighted that the AI applications developed during the workshop will enable teachers to explain complex concepts and difficult vocabulary in more practical, interactive, and engaging ways. He further noted that the creative projects presented by the participants clearly demonstrated the transformative potential of artificial intelligence in education. Dr. Teshome expressed his sincere appreciation to Professor Nega Worku Debela for leading the training with dedication and expertise, as well as to the United States Embassy in Addis Ababa for its generous support in making the program a success.
At the conclusion of the workshop, certificates were awarded to participants who successfully completed the training. In his closing remarks, Dr. Alebachew Kemisso, Vice President for Academic Affairs, emphasized that the "AI-Enhanced Pedagogy" training had made a significant contributions to enhancing teaching and learning through the effective integration of artificial intelligence.
የቋንቋዎች ትምህርት ኮሌጅ ከገጣሚና ጸሐፌ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ ጋር የስነ-ጽሑፍ ውይይት አካሄደ
** ** ****
(ኮትዩ፣ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም) – የቋንቋዎች ትምህርት ኮሌጅ በኢትዮጵያ የቴአትር እና የሥነጽሑፍ ዘርፍ የረጅም ዘመን አስተዋፅኦ ካበረከተው ገጣሚና ጸሐፌ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ ጋር የሥነጽሑፍ ውይይት ያካሄደ ሲሆን፣ ደራሲውም በሥነጽሑፍ መስክ ያሳለፈውን የረጅም ዓመታት ጉዞ እና ያጋጠሙትን ተሞክሮዎች ለተሳታፊዎች አካፍሏል።
በውይይቱ ወቅት ደራሲው ወደ ሥነጽሑፍ ዓለም እንዲገባ ያነሳሱትን ምክንያቶች፣ የልጅነት ትዝታዎቹን፣ የዩኒቨርሲቲ መምህርነት ቆይታውን እና የደራሲነት ህይወቱን በተመለከተ ከኮሌጁ መምህራን ለቀረቡለት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል።
የሥነጽሑፍ ፍቅሩ እንዲያድግ ትልቅ ሚና የተጫወቱት አባቱ መሆናቸውን የገለጸው ገጣሚና ጸሐፌ ተውኔት አያልነህ፣ ከዩኒቨርሲቲ መምህርነት እስከ ባህል ማዕከል ዳይሬክተርነት እንዲሁም በተለያዩ የመንግስት ኃላፊነቶች ሀገሩን ከማገልገል በተጨማሪ ለመድረክና ለሕትመት የበቁ ሙሉ ጊዜ ተውኔቶቹን፣ የታተሙ ግጥሞቹን እና ሙዚቃዊ ድራማዎቹን እንዲሁም ከውጭ ቋንቋዎች ወደ አማርኛ የተረጎማቸውን ሥነጽሑፋዊ ሥራዎቹን በዝርዝር አብራርቷል።
ለህትመት በበቁ እና መድረክ ላይ በቀረቡ የተውኔት ሥራዎቹም ምክንያት የደረሰበትን የእስርና የመጉላላት አጋጣሚ፣ ሀገር በቀል እውቀት እና በዚሁ እሴት ላይ የተመሠረተ ሥርዓተ ትምህርት ለሀገራችን ዕድገት እንዲሁም ለትውልዱ መቀጠል አስፈላጊ መሆናቸውን በመግለፅም ከመምህራኑ ጋር ሰፊ ውይይት አድርጓል።
ውይይቱም የሀገሪቱን ሥነጽሑፍ ታሪክ ለመረዳት፣ የፈጠራ ሥራዎችን ለማሳደግ፣ ተተኪ ትውልድን ለማፍራት እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የሚካሄደውን የመማር ማስተማር ሂደት የሚያግዝ ጠቃሚ ግንዛቤ እንዲገኝ ማስቻሉም በውይይቱ ወቅት ተገልጿል።
ከዚሁ ጠቀሜታ በመነሳት ገጣሚና ጸሐፌ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ ሰፋ ባለ መድረክ ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ገለፃ እንደሚያቀርብ ሌላ የውይይት መድረክ እንደሚዘጋጅም የቋንቋዎች ትምህርት ኮሌጅ ዲን ዶ/ር በቃሉ አጥናፉ በውይይቱ መድረክ መዝጊያ ላይ ባሰሙት ንግግር አመልክተዋል፡፡
- የህዝብ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት
#Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education
ለተጨማሪ መረጃ ይፋዊ ገጾቻችንን ይከታተሉ:
Facebook፡ https://web.facebook.com/www.kue.edu.et
Website: https://www.kue.edu.et/
YouTube: https://youtube.com/@kueducation
Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et)
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የመምህራንና ሠራተኞች የእግር ኳስ ውድድር የፍጻሜ ጨዋታ ተካሄደ
*** *** ***
(ኮትዩ፣ ግንቦት 2018 ዓ.ም) - በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሰውነት ማጎልመሻና ስፖርት ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት በአምስት የሠራተኞችና መምህራን ወንዶች፣ እንዲሁም በሁለት የሴት ሠራተኞች ቡድን መካከል ላለፉት ሦስት ወራት ሲካሄድ የቆየው የእግር ኳስ ውድድር ዛሬ በተደረገው የፍጻሜ የዋንጫ ጨዋታ ተጠናቋል፡፡
በሴት ሠራተኞች መካከል በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ የአልማዝ ቡድን የአያል ቡድንን በመለያ ምት 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ በወንዶች እግር ኳስ የፍፃሜ ጨዋታ ደግሞ በአስተዳደር እና በተፈጥሮ ሳይንስ ቡድኖች መካከል በተደረገው ጨዋታ በተፈጥሮ ሳይንስ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
ለውድድሩ መሳካት ዳኝነቱን በሚገባ ለመሩት የምስጋና ሠርተፍኬት፣ ለአሸናፊ ቡድኖች የዋንጫ ሽልማት ተሰጥቷል፡፡ የስፖርት ሳይንስ ላብራቶሪን ላሳመሩ የአርት ስኩል ተማሪዎችም በዚሁ ወቅት የዕውቅና ሠርተፍኬት ተበርክቶ የፕሮግራሙ ፍፃሜ ሆኗል፡፡
በውድድሩ መዝጊያ ሥነስርዓት ላይ የዩኒቨርሲቲው የምርምርና የማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ፣ የፕሬዘዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር መሠረት ሀብታሙ፣ የሰውነት ማጎልመሻና ስፖርት ኢንስቲትዩት ዲን ዶ/ር ጥላሁን በረደድ እና የብቃትና ሰው ሀብት ጽ/ቤት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተሰማ መንግሥቱ ተገኝተዋል፡፡
- የህዝብ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት
#Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education
ለተጨማሪ መረጃ ይፋዊ ገጾቻችንን ይከታተሉ:
Facebook፡ https://web.facebook.com/www.kue.edu.et
Website: https://www.kue.edu.et/
YouTube: https://youtube.com/@kueducation
Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et)
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
በመጪው የትምህርት ዘመን በራስ ገዝነት ሽግግር መመሪያ መሰረት 60 በመቶና ከዚያም በላይ የሚያስመዘግቡ ዩኒቨርስቲዎች ወደ ራስገዝነት እንደሚሸጋገሩ ተገለጸ።
------------------------- // -------------------------
በዛሬው እለት ወደ ራሰ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሽግግር የሚገቡ ዩኒቨርስቲዎች የዝግጅት ግምገማ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ለገለልተኛ ገምጋሚ ቡድኑ ተሰጥቷል።
መድረኩ ላይ የተገኙት የከፍተኛ ትምህርት አስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) እንደገለጹት ዩኒቨርስቲዎች በአዋጅ ቁጥር1294/2015 መሠረት ወደ ራስገዝነት ሽግግር እንዲገቡ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አንስተዋል።
በተለይም በመጪው የትምህርት ዘመን ዘጠኝ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በተዘጋጀው መሥፈርት መሠረት የራሳቸውን ግለ ግምገማ በማድረግ ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፖርት ማቅረባቸውን ጠቁመዋል።
ተቋማቱ ያቀረቡትን ሪፖርት መሠረት በማድረግም የትምህርት ሚኒስቴር ዝግጅቶቻቸውን በሚመለከት ከዩኒቨርስቲዎች በተውጣጡ ፕሮፌሰሮችና ሌሎች ምሁራን ገለልተኛ ግምገማ ለማድረግ ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ስራ እየተገባ እንደሆነ ገልጸዋል።
ግምገማው ሲጠናቀቅም ግምገማው ከተካሄደባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ 60 በመቶና በላይ የግምገማ ውጤት የሚያስመዘግቡ ዩኒቨርስቲዎች ወደ ሽግግር ሂደቱ የሚገቡ እንደሆነ ዶክተር ሰለሞን ተናግ ረዋል።
በዚህም ዩኒቨርስቲዎቹ ያሉበትን ሁኔታ የግምገማ ቡድን ወደ ተቋማቱ የሚሰማራ ሲሆን
የግምገማው ስራውም ከነገ ጀምሮ እንደሚጀመርም በመድረኩ ተገልጿል።
ከመጪው 2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ወደ ራስ ገዝነት ሽግግር እንዲያደርጉ ከሚጠበቁ ዩኒቨርስቲዎች መካከልም መቀሌ ፣ ባህርዳር ፣ ጎንደር ፣ጅማ ፣ ሐዋሳ፣ አርባ ምንጭ ፣ ሐረማያ እንዲሁም የአዲስ አበባና የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/ http://twitter.com/fdremoe
ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/@minist
See les
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
