KUE Community / አዲስ ነገር መረጃ /
前往频道在 Telegram
4 180
订阅者
无数据24 小时
-17 天
-5430 天
帖子存档
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የመምህራንና ሠራተኞች የእግር ኳስ ውድድር የፍጻሜ ጨዋታ ተካሄደ
*** *** ***
(ኮትዩ፣ ግንቦት 2018 ዓ.ም) - በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሰውነት ማጎልመሻና ስፖርት ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት በአምስት የሠራተኞችና መምህራን ወንዶች፣ እንዲሁም በሁለት የሴት ሠራተኞች ቡድን መካከል ላለፉት ሦስት ወራት ሲካሄድ የቆየው የእግር ኳስ ውድድር ዛሬ በተደረገው የፍጻሜ የዋንጫ ጨዋታ ተጠናቋል፡፡
በሴት ሠራተኞች መካከል በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ የአልማዝ ቡድን የአያል ቡድንን በመለያ ምት 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ በወንዶች እግር ኳስ የፍፃሜ ጨዋታ ደግሞ በአስተዳደር እና በተፈጥሮ ሳይንስ ቡድኖች መካከል በተደረገው ጨዋታ በተፈጥሮ ሳይንስ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
ለውድድሩ መሳካት ዳኝነቱን በሚገባ ለመሩት የምስጋና ሠርተፍኬት፣ ለአሸናፊ ቡድኖች የዋንጫ ሽልማት ተሰጥቷል፡፡ የስፖርት ሳይንስ ላብራቶሪን ላሳመሩ የአርት ስኩል ተማሪዎችም በዚሁ ወቅት የዕውቅና ሠርተፍኬት ተበርክቶ የፕሮግራሙ ፍፃሜ ሆኗል፡፡
በውድድሩ መዝጊያ ሥነስርዓት ላይ የዩኒቨርሲቲው የምርምርና የማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ፣ የፕሬዘዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር መሠረት ሀብታሙ፣ የሰውነት ማጎልመሻና ስፖርት ኢንስቲትዩት ዲን ዶ/ር ጥላሁን በረደድ እና የብቃትና ሰው ሀብት ጽ/ቤት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተሰማ መንግሥቱ ተገኝተዋል፡፡
- የህዝብ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት
#Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education
ለተጨማሪ መረጃ ይፋዊ ገጾቻችንን ይከታተሉ:
Facebook፡ https://web.facebook.com/www.kue.edu.et
Website: https://www.kue.edu.et/
YouTube: https://youtube.com/@kueducation
Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et)
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
በመጪው የትምህርት ዘመን በራስ ገዝነት ሽግግር መመሪያ መሰረት 60 በመቶና ከዚያም በላይ የሚያስመዘግቡ ዩኒቨርስቲዎች ወደ ራስገዝነት እንደሚሸጋገሩ ተገለጸ።
------------------------- // -------------------------
በዛሬው እለት ወደ ራሰ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሽግግር የሚገቡ ዩኒቨርስቲዎች የዝግጅት ግምገማ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ለገለልተኛ ገምጋሚ ቡድኑ ተሰጥቷል።
መድረኩ ላይ የተገኙት የከፍተኛ ትምህርት አስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) እንደገለጹት ዩኒቨርስቲዎች በአዋጅ ቁጥር1294/2015 መሠረት ወደ ራስገዝነት ሽግግር እንዲገቡ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አንስተዋል።
በተለይም በመጪው የትምህርት ዘመን ዘጠኝ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በተዘጋጀው መሥፈርት መሠረት የራሳቸውን ግለ ግምገማ በማድረግ ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፖርት ማቅረባቸውን ጠቁመዋል።
ተቋማቱ ያቀረቡትን ሪፖርት መሠረት በማድረግም የትምህርት ሚኒስቴር ዝግጅቶቻቸውን በሚመለከት ከዩኒቨርስቲዎች በተውጣጡ ፕሮፌሰሮችና ሌሎች ምሁራን ገለልተኛ ግምገማ ለማድረግ ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ስራ እየተገባ እንደሆነ ገልጸዋል።
ግምገማው ሲጠናቀቅም ግምገማው ከተካሄደባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ 60 በመቶና በላይ የግምገማ ውጤት የሚያስመዘግቡ ዩኒቨርስቲዎች ወደ ሽግግር ሂደቱ የሚገቡ እንደሆነ ዶክተር ሰለሞን ተናግ ረዋል።
በዚህም ዩኒቨርስቲዎቹ ያሉበትን ሁኔታ የግምገማ ቡድን ወደ ተቋማቱ የሚሰማራ ሲሆን
የግምገማው ስራውም ከነገ ጀምሮ እንደሚጀመርም በመድረኩ ተገልጿል።
ከመጪው 2019 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ወደ ራስ ገዝነት ሽግግር እንዲያደርጉ ከሚጠበቁ ዩኒቨርስቲዎች መካከልም መቀሌ ፣ ባህርዳር ፣ ጎንደር ፣ጅማ ፣ ሐዋሳ፣ አርባ ምንጭ ፣ ሐረማያ እንዲሁም የአዲስ አበባና የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/ http://twitter.com/fdremoe
ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/@minist
See les
The Rise of Digital Technologies Offers New Possibilities to Sustain Learning in Times of Crisis
- Dr. Teshome Nekatibeb
**** ** ****
(Haile Grand Hotel, April 29, 2026) – Kotebe University of Education is hosting the 4th International Research Conference, titled “Emergencies in the Digital Era: Opportunities, Pitfalls, and Prospects.” The conference officially opened today at the Haile Grand Hotel, bringing together scholars, policymakers, and education practitioners to address the future of higher education in times of crisis. The two-day event explores how digital technologies can sustain learning amidst disruptions caused by conflict, climate change, and public health emergencies.
Delivering the opening address, Dr. Teshome Nekatibeb emphasized that the rapid rise of digital technologies presents new opportunities to ensure the continuity of education during emergencies. He underscored the university’s long-standing role in teacher education and leadership, noting its commitment to advancing inclusive, equitable, and transformative learning. Education, he stressed, remains a critical pillar for stability, hope, and recovery, even in the face of severe disruptions.
Highlighting the broader context, Dr. Teshome noted that the global education system is under mounting pressure as crises increasingly interrupt schooling and displace communities. He remarked that Ethiopia and the wider region have witnessed these challenges firsthand, affecting both educators and learners. Despite these hurdles, he reaffirmed that education must not only continue but evolve, with digital innovation serving as a key driver of resilience and adaptability.
Participants at the conference pointed to the growing role of digital tools, including radio-based instruction, mobile learning platforms, and online education systems, in expanding access to learning. At the same time, discussions raised concerns regarding the persistent digital divide, warning that unequal access to technology risks deepening existing social and educational inequalities. Speakers called for solutions that are inclusive, context-driven, and accessible to marginalized communities.
Dr. Tewodros Mulugeta, Vice President for Research and Community Engagement, highlighted the strong interest the conference has generated, with more than 100 abstracts submitted and 24 papers selected for presentation. He also welcomed participants joining both in person and virtually from countries such as Kenya, Nigeria, Ghana, South Africa, Tanzania, India, Sweden, and Ukraine, reflecting the global significance of the discussions.
Keynote addresses by Professor Vinayagum Chinapah and Dr. Alebachew Kemiso, Vice President for Academic Affairs, explored the impacts of digitalization on education during crises, examining both its opportunities and technological challenges. Their presentations, alongside research discussions by various scholars, provided critical insights into education within emergency contexts.
The conference is set to continue tomorrow and conclude in the afternoon. It is expected to generate practical recommendations to strengthen digital learning systems and enhance international collaboration.
— Public and International Relations Executive Office
#Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education
For more information, follow our official pages:
Facebook: https://web.facebook.com/www.kue.edu.et
Website: https://www.kue.edu.et/
YouTube: https://youtube.com/@kueducation
Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et)
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርትን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመስጠት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ፡፡
(መጋቢት 25/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርትን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለማስፋፋትና ጥራቱን ለማረጋገጥ ከአዲስ አበባ እና ከኦሮሚያ ትምህርት ቢሮዎች ጋር የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራርማል።
ስምምነቱ በዋናነት የመምህራንን የማስተማር ብቃት በማሳደግ የሙያ ማረጋገጫ (Professional Certificate) አሰጣጥ ላይ የሚያተኩር ሲሆን ትምህርት ቢሮዎቹ ለስልጠናው ብቁ የሆኑ መምህራንን የመለየት ፣ አስተባባሪዎችን የመመደብ እና አስፈላጊውን የሎጂስቲክስ ድጋፍ የማመቻቸት ኃላፊነት እንደሚኖርባቸው ተጠቁሟል።
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ጋር በትብብር ለመሥራት ተፈራረመ
** ** ****
(ኮትዩ፣ መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም) - የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲን በመወከል የምርምርና የማኅበረሰብ ጉድኝት ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ፣ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣንን በመወከል የመንገድ ደህንነት ግንዛቤ ደንብ ማስከበርና መድን ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አማረ ታረቀኝ ስምምነቱን የፈረሙ ሲሆን፣ በስምምነቱ ዓላማ መሠረት ሁለቱ ተቋማት በርብብር ለመምህራንና ተማሪዎች፣ ለትምህርት ቤቶች እና ለማኅበረሰቡ ስለመንገድ ደህንነት ለማስተማርና ግንዛቤ ለማስጨበጥ፣ የአቅም ግንባታ እና የማማከር ሥራዎችን ለመሥራት፣ ባለሙያዎችን እና ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ እንደሚሠሩ ተገልጿል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ፣ የሰው ልጅ አእምሮ ላይ ቀጣይነት ያለው ለውጥ የሚያመጣው ትምህርት መሆኑን ጠቅሰው፣ የትራፊክ ሕግን ለማስከበር እና አደጋ ለመቀንስ የመጀመሪያው ተግባር ማወቅ በመሆኑ፣ የተሻለ ግንዛቤ ያለው መምህር፣ ተማሪ እና ትውልድ ለመፍጠር ከአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ጋር በትብብር ለመሥራት ዩኒቨርሲቲው ደስተኛ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ ከዚህ በፊትም አብረን የሠራናቸው ሥራዎች ስላሉ የስምምነት ፊርማው የተሻለ ውጤት እንደሚያመጣ በማመልከት የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ላሳየው ቀና ትብብር አመስግነዋል፡፡
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የመንገድ ደህንነት ግንዛቤ ደንብ ማስከበርና መድን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አማረ ታረቀኝ በበኩላቸው፣ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከሚሠራቸው አምስት ዋና ዋና ተግባራት አንዱ የመንገድ ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚያግዝ ትምህርት የሚሰጥ በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ የመንገድ ደህንነት ግንዛቤው ከፍ እንዲል ትልቁ ሥራ የህብረተሰቡን የአመለካከት አድማስ ማስፋት እና አደጋ መቀነስ ስለሆነ ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር በመሥራታችን ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡
የየዪኒቨርሲቲው ኢንዱስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር መልካሙ አፈታ፣ ስምምነቱ እዚህ ደረጃ እንዲደርስ የበኩላቸውን ጥረት ያደረጉትን የከተማ ትራንስፖርት ትምህርት ክፍል ኃላፊ የሆኑትን መምህርት ሩት ይትባረክን አመስግነው፣ ስምምነቱ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ጭምር ልዩ ትኩረት የተሰጠው በመሆኑ ከመፈራረም ባሻገር ተግባራዊ እንዲሆን በትብብር እንሠራለን ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል፡፡
- የህዝብ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት
#Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education
ለተጨማሪ መረጃ ይፋዊ ገጾችችንን ይከታተሉ:
Facebook፡ https://web.facebook.com/www.kue.edu.et
Website: https://www.kue.edu.et/
YouTube: https://youtube.com/@kueducation
Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et)
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
5.ሩሲያ Russia
ሩሲያ በጠፈር ምርምር Space Science በኑክሌር ፊዚክስ እና በምህንድስና ዓለምን ከሚመሩ አገራት አንዷ ናት። ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ከፍተኛው የሳይንስ ምርምር ድረስ ትምህርታቸው በሩሲያኛ ቋንቋ ነው። ሩሲያ የራሷን የጠፈር መንኮራኩሮች፣ የጦር መሣሪያዎችና ውስብስብ ማሽነሪዎችን የምታመርተው በገዛ ቋንቋዋ በሰለጠኑ ምሁራን ነው።
6. እስራኤል Israel
እስራኤል በቴክኖሎጂና በግብርና ምርምር Agro-Tech በዓለም እጅግ የረቀቀች አገር ናት ለብዙ ዘመናት በሥራ ላይ ያልነበረውን ዕብራይስጥ Hebrew ቋንቋን በማነቃቃት፣ ለዘመናዊ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲመጥን አድርገውታል። ዛሬ እስራኤል የስታርት-አፕ አገር Start-up Nation ተብላ የምትጠራው፣ ዜጎቿ በገዛ ቋንቋቸው የፈጠራ ሥራ ላይ ስለሚሰማሩ ነው።
7. ፈረንሳይ France
ፈረንሳይ በሳይንስና በሒሳብ ትምህርት ረጅም ታሪክ ያላት አገር ናት በፈረንሳይ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ሳይንስ፣ ሕክምና እና ምህንድስና የሚሰጠው በፈረንሳይኛ ነው። የራሳቸው የሳይንስ አካዳሚ French Academy of Sciences አዳዲስ ሳይንሳዊ ቃላትን ወደ ፈረንሳይኛ የመተርጎም ኃላፊነት አለበት በዓለም ላይ ከፍተኛውን የሒሳብ ሽልማት Fields Medal ካሸነፉ አገራት መካከል ፈረንሳይ ቀዳሚዋ ናት።
8. ቱርክ Turkey
ቱርክ በአሁኑ ወቅት በወታደራዊ ቴክኖሎጂ እና በግንባታ ምህንድስና በፍጥነት እያደገች ያለች አገር ናት ምንም እንኳን የእንግሊዝኛ ተጽዕኖ ቢኖርም፣ አብዛኞቹ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ሳይንስን በቱርክኛ ያስተምራሉ ቱርክ የራሷን ሰው አልባ አውሮፕላኖች Drones እና ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ማምረት የቻለችው በዚህ መንገድ ነው።
9.ስካንዲኔቪያን አገራት ኖርዌይ፣ ስዊድን፣ ዴንማርክ
እነዚህ አገሮች ምንም እንኳን እንግሊዝኛን በሚገባ ቢናገሩም፣ መሰረታዊ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ትምህርታቸውን የሚሰጡት በገዛ ቋንቋቸው ነው በዓለም የኑሮ ደረጃ እና በፈጠራ ሥራ Innovation ሁልጊዜም ቀዳሚዎቹ ናቸው።
ልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲም ይህንን ተሞክሮ ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት
የኢትዮጵያን የትምህርት ሥርዓት ከውጭ ጥገኝነት ነፃ በማውጣት በራሷ ዕውቀትና ጥበብ የምትመራ የበለጸገች ሀገር ለመመሰረት ነዉ።
የልጅ ኤልያሰ ዩኒቨርሲቲ መቋቋም ለአገራችን ኢትዩዸያ ያለዉ ጠቀሜታ።
የልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ መቋቋም ለሚመጣው ትውልድ ከትምህርት ባለፈ የአስተሳሰብ የማንነት ኩራት በራስ መተማመን እንዲያዳብር ያደርጋል።
ለረጅም ዘመናት ሳይንስና ቴክኖሎጂ የውጭ አገር ዜጎች ብቻ የሚሰሩት ተደርጎ ሲታሰብ ቆይቷል። ትውልዱ የኳንተም ፊዚክስን ወይም የሶፍትዌር ምህንድስናን በገዛ ቋንቋው ሲማር እኛም መስራት እንችላለን የሚል የሥነ-ልቦና ጥንካሬን ያገኛል። ቋንቋን ከዕውቀት ጋር ማዋሃድ ለትውልዱ ትልቅ ኩራትን ይፈጥራል።
የፈጠራ አቅምን (Creativity) ያሳድጋል አንድ ተማሪ በትምህርት ገበታ ላይ ግማሽ ጊዜውን ቃላትን ለመተርጎም ካሳለፈ ለፈጠራ የሚሆን ጊዜ ይሻማዋል ትውልዱ በገዛ ቋንቋው ሲማር ግን ትኩረቱ ይህ ነገር እንዴት ይሰራል? እና "አዲስ ነገር ምን ልፍጠር? በሚለው ላይ ይሆናል። አገራችን ኢትዮጵያን ወደፊት የራሷን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለዓለም እንድታበረክት በር ይከፍትላታል። ትዉልዳችን በተግባር ላይ የተመሰረተ Practical ትምህርት ስለሚማር ከዩኒቨርሲቲ ሲወጣ ሥራ ፈላጊ ሳይሆን ሥራ ፈጣሪ ይሆናል። በአገር ውስጥ በሚገኙ ቁሳቁሶች ማሽኖችንና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን መስራት መቻሉ ለትውልዱ የኢኮኖሚ ነፃነትን ያጎናጽፈዋል።
ልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ ለትውልዱ የሚሰጠው ትልቁ ስጦታ "የዕውቀት ቁልፍ" ነው።
ይህ ቁልፍ ደግሞ በውጭ ቋንቋ መቆለፊያ የታሰረ ሳይሆን፣ በማንኛውም ኢትዮጵያዊ እጅ የሚከፈት በቀላሉ የሚገባና የሥልጣኔን በር የሚከፍት ነው።
ይህ ተቋም በተለይ ሳይንስና ቴክኖሎጂን በአፍ መፍቻ ቋንቋ በአማርኛ ለማስተማር የያዘው ራዕይ ከሀገራችን አልፎ እንዲሁም ለአፍሬካዉያን የትምህርት ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው።
ኢትዮጵያ ካሏት በርካታ ጥንታዊ ዕውቀቶች መካከል አብዛኞቹ ከዘመናዊው ሳይንስ ጋር ጥልቅ ቁርኝት አላቸው።
እነዚህን ዕውቀቶች ከዘመናዊው ሳይንስ Physics, Chemistry, Engineering, Medicine አንጻር ስንመዝናቸው አባቶቻችን ምን ያህል የረቀቀ ጥበብ እንደነበራቸው እንረዳለን።
ዋና ዋናዎቹን ትስስሮች እንዲህ ማየት ይቻላል የሕንፃ ምህንድስና Civil Engineering & Architecture የአክሱም ሐውልቶች ግዙፍ ድንጋዮችን ከአለት ፈልፍሎ ማውጣት ማጓጓዝ እና ቀጥ አድርጎ መትከል ከፍተኛ የፊዚክስ Statics and Dynamics እና የሜካኒካል ምህንድስና ዕውቀትን ይጠይቃል። በተለይ የስበት ማዕከልን Center of Gravity ጠብቆ ማቆም መቻላቸው የሚደነቅ ነው ። የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት፦ ከአንድ ወጥ ድንጋይ ተፈልፍለው መሰራታቸው የጂኦሎጂ Geology እና የከፍተኛ መዋቅራዊ ምህንድስና Structural Engineering ውጤቶች ናቸው። የውኃ መውረጃ መስመሮቻቸውና የድጋፍ ምሶሶቻቸው ስሌት ዛሬም ድረስ መሐንዲሶችን ያስደምማል።
የሕክምና ሳይንስ Medical Science & Pharmacology ባህላዊ መድኃኒቶች ጥንታውያን ኢትዮጵያውያን ከተለያዩ ዕፅዋት፣ ማዕድናትና የእንስሳት ተዋጽኦዎች መድኃኒት የመቀመም ጥበብ ነበራቸው። ይህም ከዘመናዊው የፋርማሲ Pharmacognosy ሳይንስ ጋር ይያያዛል። ለምሳሌ እንቆቆ እና ኮሶ ለሆድ ትል መድኃኒትነት መጠቀማቸው በዘመናዊ ሳይንስ የተረጋገጠ ውጤት አለው ቀዶ ሕክምና በጥንታዊ የቤተክህነት መጻሕፍት ውስጥ ስለ ዓይን ሞራ ማውጣት እና ስለ ተሰበሩ አጥንቶች ጥገና ውጋት የሚገልጹ መረጃዎች አሉ። ይህ ከዘመናዊው Surgery እና Orthopedics ጋር ይመሳሰላል ። የሥነ-ከዋክብት ጥናት Astronomy & Mathematics የአቡሻህር ስሌት የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር በከዋክብት፣ በጨረቃና በፀሐይ ዑደት ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ ስሌት ከፍተኛ የሒሳብ Mathematics እና የሥነ-ከዋክብት Astronomy ዕውቀትን ይጠይቃል። የፀሐይና የጨረቃ ግርዶሽን ቀድሞ መተንበይ መቻላቸው የጥበቡን ጥልቅነት ያሳያል የብረታ ብረትና የኬሚስትሪ ጥበብ Metallurgy & Chemistry የቀለጣ ጥበብ ጥንታውያን ኢትዮጵያውያን ብረትን አቅልጠው ለጦር መሣሪያ፣ ለቤት መገልገያና ለጌጣጌጥ ይጠቀሙ ነበር። ይህ የኬሚስትሪንና የሜታለርጂን Metallurgy ሳይንስ በተግባር መረዳታቸውን ያሳያል የቀለም ቅመማ በጥንታውያን መጻሕፍት ብራናዎች ላይ የሚታዩትና ለዘመናት የማይለቁ ቀለሞች ከዕፅዋትና ከማዕድናት የተቀመሙ የኬሚስትሪ ውጤቶች ናቸው።
የግብርና ሳይንስ Agricultural Science የእርከን ስራ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ለሺህ ዓመታት የቆዩ የእርከን ስራዎች የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የተሰሩ የኒያክ ኢንጂነሪንግ Hydraulic Engineering ስራዎች ናቸው የሰብል ዝርያዎችን ማላመድ እንደ ጤፍ እና እንሰት ያሉ ሰብሎችን ለይቶ ማልማትና ለምግብነት ማዋል ከዘመናዊው የዕፅዋት ዘረ-መል Genetics እና ባዮቴክኖሎጂ ጋር የተያያዘ ነው።
እነዚህ ጥንታዊ ዕውቀቶች በዘመናዊ ሳይንሳዊ ስም ባይጠሩም፣ በተግባር ግን ሳይንሳዊ ሕጎችን የተከተሉ ነበሩ። ልጅ ኤልያስ ዩኒቨርሲቲ እነዚህን ጥበቦች በምርምር አግኝቶ ከዘመናዊው ቴክኖሎጂ ጋር በማገናኘት ለትውልዱ በማሰተላለፍ ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ የሳይንስ ማንነት እንዲኖራት ያደርጋል።
ትዉልዳችዉን በገዛ ቋንቋቸው ሳይንስና ቴክኖሎጂን በማሰተማር በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ዓለም አቀፍ የሥልጣኔ ማማ ላይ የደረሱ በርካታ አገሮች አሉ እነዚህ አገሮች የቋንቋን መሰናክል በመስበር ዕውቀትን ለሕዝባቸው ተደራሽ በማድረጋቸው ውጤታማ ለመሆን በቅተዋል።
ለምሳሌ እነዚህ ዋናዎቹን አገሮችና ተሞክሯቸውን እንደሚከተለው መመልከት ይቻላል።
1.ጃፓን (Japan) ከምዕራባውያን አገራት ውጭ በቴክኖሎጂ ቀዳሚ መሆን የቻለችው በቋንቋዋ በመጠቀሟ ነው የተከተሉት መንገድ፦ በ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን በሜይጂ ዘመን የነበሩ የጃፓን ምሁራን የዓለምን የሳይንስና የቴክኖሎጂ መጻሕፍት ወደ ጃፓንኛ ተረጉመዉ ዛሬ ጃፓን በሮቦቲክስ፣ በአውቶሞቢል እና በኤሌክትሮኒክስ ዘርፍ የዓለም መሪ መሆን የቻለችው ልጆቿ በገዛ ቋንቋቸው የሳይንስን ጥልቀት ስለሚረዱ ነው።
2.ደቡብ ኮሪያ South Korea
ከ፶ ዓመታት በፊት ከኢትዮጵያ በታች በኢኮኖሚ ደካማ የነበረችው ደቡብ ኮሪያ አሁን ካለችበት የዕድገት ደረጃ ላይ የደረሰችው በትምህርት ሥርዓቷ ነው። ሳይንስን፣ ሒሳብንና ምህንድስናን በኮሪያኛ Hangul ቋንቋቸው ብቻ ነው የሚማሩት። ውጤቱ እንደ ሳምሰንግ Samsung እና ሂዩንዳይ Hyundai ያሉ የዓለም ግዙፍ የቴክኖሎጂ ተቋማትን ማፍራት ችለዋል።
3. ጀርመን Germany
ጀርመን በአውሮፓ የምህንድስና እና የኢንዱስትሪ ማዕከል ናት። በጀርመን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አብዛኛው የምህንድስና እና የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት የሚሰጠው በጀርመንኛ ቋንቋ ነው። ጀርመን በዓለም ላይ ጥራት ያለው የማሽነሪና የሕክምና መሣሪያዎችን በማምረት የታወቀችው፣ ዜጎቿ ሳይንሱን በገዛ ቋንቋቸው ጠልቀው ስለሚመራመሩበት ነው።
4. ቻይና China
ቻይና በአሁኑ ወቅት በጠፈር ምርምር እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዓለምን እየመራች ነው። ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ከፍተኛ ፒ.ኤች.ዲ (PhD) ድረስ ትምህርታቸው በማንዳሪን ቻይንኛ ቋንቋ ነው። ውጤቱ፦ የቋንቋ እንቅፋት ስለሌለባቸው በቢሊዮን የሚቆጠረው ሕዝባቸው በፈጠራ ስራ ላይ በቀላሉ እንዲሰማራ አድርገዋል።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
