es
Feedback
KUE Community / አዲስ ነገር መረጃ /

KUE Community / አዲስ ነገር መረጃ /

Ir al canal en Telegram

Kotebe University of Education Community / አዲስ ነገር መረጃ /

Mostrar más
4 241
Suscriptores
+324 horas
+17 días
+3330 días
Archivo de publicaciones
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2019 ዓ.ም በ11ኛ ክፍል ለሚጀመሩ አዳዲስ የሥራና ተግባር ትምህርት የሙያ ዓይነቶች የአተገባበር ማንዋል ይፋ አድርጓል። 👉 በመተግበሪያ ማንዋሉ መሰረት አንድ ተማሪ ከአቅሙና ከፍላጎቱ ጋር የተያያዘ አንድ የሙያ ዓይነት ብቻ መርጦ የሚማር ሲሆን፣ ትምህርት ቤቶች ሁሉንም 11 ዓይነት ሙያዎች በአንድ ጊዜ እንዲተገብሩ አይገደዱም። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመቅረፍ እና ተማሪዎችን ለሥራው ዓለም ለማዘጋጀት ያለመ አዲስ የአተገባበር ማንዋል አዘጋጅቷል። በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም ተዘጋጅቶ የቀረበው ይህ ማንዋል፣ በ2019 ዓ.ም በ11ኛ ክፍል ለሚጀመሩ አዳዲስ የሥራና ተግባር ትምህርት የሙያ ዓይነቶች ትግበራ የሚውል ሲሆን፤ የትምህርቱን አስፈላጊነት፣ ዓላማ፣ የአመራረጥ ሂደት እና የተግባርና ኃላፊነት ክፍፍልን በዝርዝር አካቷል። ቢሮው በመመሪያው መግቢያ ላይ እንደገለጸው፣ ትምህርት ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት ከፍተኛ ሚና ቢኖረውም፣ በተካሄደው የፍኖተ ካርታ ጥናት መሰረት የአጠቃላይ የትምህርት ስርዓቱ ከሥራና ተግባር ጋር ያልተሳሰረና የ21ኛው ክፍለ ዘመን ክህሎትን ያላካተተ ሆኖ ተገኝቷል። ይህ ችግር ተማሪዎችን በመሠረታዊ እውቀት ብቻ ያቆምና በሥራ ዓለም ተግባራዊ አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ የማያስችል ነው ይላል። ችግሩን ለመፍታትም በ2017 እና 2018 ዓ.ም በሁለተኛ ደረጃ ላይ በሚገኙ ተማሪዎች በስምንት የሙያ መስኮች ማለትም ፦ - በግብርና ፣ - መረጃ ቴክኖሎጂና ኮምፒውተር ሳይንስ ፣ - ጤና ሳይንስ፣ - ኮንስትራክሽን፣ - ማኑፋክቸሪንግ ፣ - ኮሙኒኬሽንና የማህበራዊ ሳይንስ ፣ - ቢዝነስ ሳይንስ እና ስነጥበባት ውስጥ ከሚገኙት የሥራ አይነቶች አንዱን መርጠው እንዲማሩ መደረጉን አስታውሷል። ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮም ከዕድሜ ጋር የተመጣጠነ የሥራና ተግባር ትምህርት እንደተሰጠ የአተገባበር መመሪያው ያስረዳል። አሁን ደግሞ በ2019 ዓ.ም በሁለተኛ ዙር ለ11ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚቀርቡ 11 አዳዲስ የሙያ ዓይነቶችን በትምህርት ቤቱ እና በተማሪው ምርጫ ተግባራዊ ለማድረግ የመተግበሪያ መመሪያ (Manual) መዘጋጀቱ አመልክቷል። በዚህ አዲስ የአተገባበር ሥርዓት ውስጥ የተካተቱት 11 የሙያ ዓይነቶች በስድስት ዋና ዋና የሙያ ዘርፎች (Career Clusters) የተከፋፈሉ ናቸው። ° በግንባታ ዘርፍ የሕንፃ ኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ እና የቧንቧ ስራ፤ ° በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የብረታ ብረት ቴክኖሎጂ፣ አውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ እና አልባሳት ቴክኖሎጂ ፤ ° በቢዝነስ ሳይንስ ዘርፍ የሆቴል አገልግሎት፣ የፀጉር ሥራና ውበት አገልግሎት እንዲሁም የምግብ ዝግጅት ተካተዋል። በተጨማሪም በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የሶፍትዌር ማበልጸግ፣ በግብርና ሳይንስ የሰብል አመራረት እና በጤና ሳይንስ የጤና ክብካቤ አገልግሎት የሙያ ዓይነቶች ለተማሪዎች እንዲቀርቡ ተለይተዋል። የሙያ ዓይነቶቹ የሚመረጡበት ሂደት ጥንቃቄ የተሞላበት እንዲሆን በመመሪያው ታዟል። ትምህርት ቤቶች የሙያ ዓይነቶችን ከመምረጣቸው በፊት የአካባቢውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ፣ ያሉትን የሰው ኃይልና የቁሳቁስ ግብዓቶች፣ እንዲሁም የተማሪዎችን ፍላጎት ግምት ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። በአተገባበር በመመሪያው መሠረት አንድ ትምህርት ቤት ሁሉንም 11 የሙያ ዓይነቶች ማቅረብ አይጠበቅበትም፤ ይልቁንም እንደ አቅሙና እንደ አካባቢው ሁኔታ የተወሰኑትን መርጦ ተግባራዊ ያደርጋል። ተማሪዎችም ከቀረቡት አማራጮች መካከል የአንዱ የሙያ ዓይነት ባለቤት እንዲሆኑ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ምርጫቸውም ከፍላጎታቸውና ከችሎታቸው ጋር የተገናኘ መሆን እንዳለበት ተደንግጓል። ለመመሪያው መሳካት የተለያዩ አካላት የየራሳቸው ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል። የከተማዋ ትምህርት ቢሮ የመሪ ዕቅድ የማዘጋጀትና ክትትል የማድረግ ኃላፊነት ሲኖርበት፣ የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽሕፈት ቤቶች ደግሞ ትምህርት ቤቶች የሙያ ዓይነቶችን እንዲለዩ ድጋፍ ያደርጋሉ፤ ሙያውን የሚከታተሉ ባለሙያዎችንም ይመድባሉ። ትምህርት ቤቶች በበኩላቸው ካሉ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመመካከር የሙያ ዓይነቶችን የመምረጥ፣ ለተማሪዎች ግንዛቤ የመፍጠርና ትግበራውን የመምራት ቀጥተኛ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ይህ የሥራና ተግባር ትምህርት ውጤታማ እንዲሆን ትምህርት ቤቶች ከአካባቢው ማህበረሰብ፣ ከመንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ከግል ባለሀብቶች ጋር በቅንጅት መሥራት እንደሚጠበቅባቸው መተግበሪያ መመሪያው ያሳስባል። ይህም ተማሪዎች ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ ሥራ ፈጣሪ ዜጎች እንዲሆኑና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዲደግፉ ለማስቻል ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ቢሮው ለትግበራው ምቾት ይረዳ ዘንድ ለትምህርት ቤቶችና ለተማሪዎች ምርጫ የሚሆኑ ቅጾችንም ከመመሪያው ጋር አያይዞ አቅርቧል። ሙሉ የአተገባበር ማንዋሉን በዚህ ያገኛሉ : አዲስ አበባ ነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ/ም

ትምህርት ሚኒስቴር በማስተማር ሥራ ላይ ያሉ መምህራንን ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ለመጀመር በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ገልጿል። በቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ጋር የተናበበ የሥልጠና ማዕቀፍ፣ ፕሮግራሙን ለመምራት የሚያስችሉ የትግበራ ሰነዶችን እና የሰልጣኝ መምህራንን ምልመላ፣ መረጣ እና ምደባ መከናወኑን አመልክቷል። ባለፉት አመታት በስልጠናው አሰጣጥ ጥራት ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የመምህራን የክረምት የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና በዚህ ክረምት ለማስጀመር 8 ዩኒቨርሲቲዎች ተለይተዋል። እነዚህም፦ - ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ - ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ - መቐለ ዩኒቨርሲቲ - ጅማ ዩኒቨርሲቲ - ሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ - ጎንደር ዩኒቨርሲቲ - አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሲሆኑ፣ በ2018 ዓ.ም. ክረምት 8,273 መምህራንን ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ወደ ስልጠና ለማስገባት ዝግጅት መጠናቀቁን ይፋ አድርጓል። የመግቢያ ምዘና ወስደው ያለፉና በየዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ ሰልጣኝ መምህራን፣ ምዝገባው ሐምሌ 24 እና 25/2018 ዓ.ም. የሚካሄድ መሆን ትምህርት ሚኒስቴር አመልክቷል።

ዩኒቨርሲቲው በለውጥ ላይ ነው! … - የካውንስል አባላት የግንባታ ፕሮጀክቶችን ጎበኝተዋል *** *** ***** (ኮትዩ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም) - የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የካውንስል አባላትና መምህራን በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የተገነቡ አዳዲስ እና እድሳት የተደረገላቸው ነባር ሕንጻዎችን ጎብኝተዋል፡፡ የግንባታ ፕሮጅክቶቹ ለቀጣዩ የትምህርት ዓመት ዝግጁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የተዘጋጀውን የአካላዊ ምልከታ መርሐግብር በንግግር ያስጀመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተሾመ ነቃጥበብ፣ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ዩኒቨርሲቲውን ወደ ተሟላ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለመቀየር የተካሄዱት የሪፎርም ስራዎች ሂደታቸውን ጠብቀው ውጤታማ በሆነ መልኩ እየተከናወኑ በመሆናቸው ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በተጨባጭ ለውጥ ላይ ነው ብለዋል፡፡ ከተከናወኑት የለውጥ ስራዎች መካከልም ከዩኒቨርሲቲው የአመራር ቦርድ እስከ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ድረስ የአመራር ለውጥ ማድረግ፣ አዲስ ካውንስል ማቋቋም፣ የሕግ ማዕቀፎች ይልቁንም የዩኒቨርሲቲውን የወደፊት አቅጣጫ የሚያሳይ ፍኖተ ካርታ፣ የሌጅስሌሽን፣ የአካዳሚክ ፕርግራሞች ማሻሻያ፣ ኢንተርናላይዜሽን፣ ስፔሻላይዜሽን እና የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ዋና ዋናዎቹ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ እነዚህም ተግባራት ዩኒቨርሲቲው ስርነቀል ለውጥ በማካሄድ እውቅና እንዲያገኝ የሚያስችሉ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በቀጣይም ልዩ ልዩ ፖሊሲዎችን ከማዘጋጀት እና መዋቅራዊ ለውጦችን በወረቀት ላይ ከማስፈር አንፃር ብዙ ይቀረናል ያሉት ፕሬዘዳንቱ ዶ/ር ተሾመ፣ ከሽግግር ወደ ተረጋጋ አሰራር ለመድረስም ከፊታችን ብርቱ ስራዎች ስለሚጠብቁን የካውንስል አባላትና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት ስራዎቻቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሽመልስ ዘውዴ በበኩላቸው፣ የጉብኝት መርሐግብሩ የተዘጋጀው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት እየተከናወኑ ያሉ ግንባታዎችን በቅርበት እንዲያውቁና የበኩላቸውን እንዲወጡ ለማስቻል መሆኑን ገልፀው፣ በእጃችን ላይ ከሚገኙት 10 የሚሆኑ ፕሮጀክቶች መካከል 98 በመቶ ያህል የተጠናቀቁት የተማሪዎች የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብሎክ ኤ እና ቢ ህንፃ፣ የተማሪዎች ክሊኒክ፣ ተጠናቆ አገልግሎት የጀመረው የአይሲቲ መሠረተ ልማት፣ የዩኒቨርሲቲው አጥርና የመግቢያ በሮች፣ የተማሪዎች መመገቢያና ኪችን ህንፃ፣ እንዲሁም የተማሪዎች መኝታ ቤት የሆኑ የሦስት ነባር ህንፃዎች እድሳት፣ የምድረ ግቢ ውበት መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም ከአንድ ወር በኋላ የሚጀመሩ የሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ፣ ለተማሪዎች መኝታ የሚሆኑ ሁለት መንታ ሕንጻዎች፣ የቋንቋዎች ትምህርት ኮሌጅ ግንባታ የዲዛይን ሥራ፣ የውኃ መሠረተ ልማት ግንባታ ዝርጋታ፣ የአስተዳደር ሕንፃ ግንባታ እና ሌሎች ተመሳሳይ የእድሳት ስራዎች የ2019 ዓ.ም ፕሮጀክቶች ከመሆናቸውም በተጨማሪ የዩኒቨርሲቲውን ገፅታዎች በተሻለ ሁኔታ እንደሚቀይሩም አብራርተዋል፡፡ ሕንፃዎቹም በዋናነት ለመማር ማስተማር፣ ለቢሮ፣ ለመዝናኛ ክበብ፣ ለማህበራዊ አገልግሎት፣ ለመኪና ማቆሚያ እና ለገቢ ማመንጫ አገልግሎት እንደሚውሉ ተናግረዋል፡፡ ለዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላትና መምህራን የቀረበውን ገለፀ ተከትሎ፣ ምድብ አንድ በአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዘዳንቱ በዶ/ር ሽመልስ ዘውዴ፣ ምድብ ሁለት በአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር አለባቸው ኬሚሶ እና በምርምር እና በማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ መሪነት የአካል ምልከታ ጉብኝቱ ተከናውኗል፡፡ በጉብኝት መርሐግብሩ ላይ የተሳተፉት የዩኒቨርሲቲው የካውንስል አባላትና መምህራን በሰጡት አስተያየት፣ በተመለከቱት ደረጃቸውን የጠበቁ ግንባታዎች በእጅጉ የተደሰቱ መሆናቸውን ተናግረው፥ የተጠናቀቁት እንዳሉ ሆነው በጅምር ላይ ያሉት ተጠናክረው እንዲቀጥሉና ግንባታዎቹም ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች ጨምሮ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ታሳቢ እንዲያደርጉ ሃሳብ የሰጡ ሲሆን፣ የማኔጅመንት አባላቱም ለተሰጡት አስተያየቶች ትኩረት እንደሚሰጡ በማስረዳት የጉብኝት መርሐግብሩ ተጠናቋል፡፡ - የህዝብ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት #Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education ለተጨማሪ መረጃ ይፋዊ ገጾቻችንን ይከታተሉ: Facebook፡ https://web.facebook.com/www.kue.edu.etቻ Website: https://www.kue.edu.et/ YouTube: https://youtube.com/@kueducation Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et) Log in or sign up to view See posts, photos and more on Facebook.

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በደብረብርሀን እና አሰላ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ያሰለጠናቸውን 2,349 የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራንን አስመረቀ። (ሰኔ 20/2018 ዓ.ም) በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው የምርቃት መርሀ ግብር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ስትራቴጂክ ካውንስል አባላትን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት አመራሮች፣የሁለቱ ኮሌጆች ዲኖችና መምህራን እንዲሁም የተመራቂ ቤተሰቦችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊና የመርሀግብሩ የክብር እንግዳ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ባስተላለፉት መልዕክት በከተማ አስተዳደሩ የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ተግባራዊ በማድረግ አዲስ አበባን ህጻናትን ለማሳደግ ምቹና ተመራጭ አፍሪካዊት ከተማ ለማድረግ እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በጫወታ የማስተማር ስነ ዘዴን ተግባራዊ በማድረግ በተማሪዎቹ ሁለንተናዊ እድገት ላይ መስራት መሆኑን አመላክተዋል። ኃላፊው አያይዘውም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ህጻናቱ ለቀጣዩ የትምህርት ደረጃዎች መሰረት የሚጥሉበት የትምህርት እርከን እንደመሆኑ በዛሬው እለት የተመረቁ መምህራን በኮሌጆቹ በነበራቸው ቆይታ ባገኙት ዕውቀትና ክህሎት መሰረት በጫወታ የማስተማር ስነዘዴን በአግባቡ በመተግበር ተማሪዎችን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባቸው በመግለጽ ሁለቱን ኮሌጆች ጨምሮ ለመርሀግብሩ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አበራ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ የቅድመ አንደኛ ትምህርትን ውጤታማ ለማድረግ መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ ለተቋማቱን ግብአት ከማቅረብ ጀምሮ ለመምህራን ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰው በደብረ ብርሀን አሰላ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ተምረው በዛሬው እለት የተመረቁ መምህራንም የዚሁ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን በመግለጽ ለተመራቂዎች መልካም እድል ተመኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ከትምህርት ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑን የማህበሩ ፕሬዘዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ ገልጸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከሁለቱ ኮሌጆች ጋር በጋራ በመሆን መምህራኑን አሰልጥኖ በማስመረቁ በማህበራቸውና በተመራቂ መምህራን ስም ምስጋና አቅርበዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

የሙአዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ልጅ ተመርቋል! #maleda :የእውቀትና የጥበብ ፍሬዎች ሲጎመሩ ማየት ለወላጅም ለሀገርም ትልቅ ደስታ ነው። ዛሬ በሀገራችን የኪነ-ጥበብና የማኅበራዊ ሕይወት ዘርፍ ጉልህ አሻራ ያኖሩት የሙአዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ልዩ የወላጅነት ኩራት ያጣጣሙበት ታሪካዊ ቀን ሆኗል። የዲ/ን ዳንኤል ክብረት ልጅ አቤሜሌክ ዳንኤል ረጅም የታማኝነትና የጥናት ዓመታትን በስኬት አጠናቆ፣ ዛሬ ከአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ተመርቋል። የአባት አደራ እና የራስ ጥረት ሲገናኙ ውጤቱ ሁልጊዜም ማማር ነው!" ይህ የምረቃ ቀን የወጣቱ አቤሜሌክ የልፋት ውጤት ብቻ ሳይሆን፣ ልጆቻቸውን በዕውቀትና በስነ-ምግባር ቀርጸው ለዚህ ማዕረግ ያበቁት የወላጆቹ የድካም ፍሬ መገለጫ ጭምር ነው። ለአቤሜሌክ ዳንኤል የወደፊት የሕይወትና የሥራ ዘመን ብሩህ እንዲሆንልህ እንመኛለን። ይህ የትምህርት መድረክ የትልቅ ጉዞ መጀመሪያ ይሁንህ! ከዩኒቨርሲቲው የቀሰምከው ዕውቀት ለራስህ የሚጠቅም፣ ለቤተሰብህ ኩራት የሚሆንና ለሀገርህም የሚተርፍ ፍሬ እንዲያፈራ ከልብ እንመኛለን። ለአቤሜሌክ፣ ለዲ/ን ዳንኤል ክብረት እና ለመላው ቤተሰብ፦ እንኳን ደስ አላችሁ::

የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የምረቃ ስነስርዓት እየተካሄደ ነው *** ** *** (ኮትዩ፣ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም) ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በዲፕሎማ፣ በቅድመ ምረቃ፣ በድህረ ምረቃ ማለትም በማስትሬት እና በዶክትሬት ዲግሪ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 2882 ተማሪዎች በአደዋ ድል መታሰቢያ የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ በደማቅ ስነ-ስርዓት እያስመረቀ ነው፡፡ የምረቃ ስነስርዓቱ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እና የተማሪ ወላጆች በተገኙበት እየተከናወነ ሲሆን የ2018 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ! - የህዝብ እና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት #Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education ለተጨማሪ መረጃ ይፋዊ ገጾቻችንን ይከታተሉ: Facebook፡ https://web.facebook.com/www.kue.edu.et Website: https://www.kue.edu.et/ YouTube: https://youtube.com/@kueducation Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et) Log in or sign up to view See posts, photos and more on Facebook.

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ2018ዓ.ም ለሁለተኛ ዙር ተማሪዎቹን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ፡፡ ***** (ባሌ-ሮቤ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ሕ.ዓ.ግ.ጽ) መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ለ18ኛ ጊዜ በተለያዩ ኮሌጆች ስር ያስተማራቸውን 1089/አንድ ሺ ሰማንያ ዘጠኝ /ተማሪዎቹን ነው በመጀመሪያ ድግሪ እና ማስተርስ ድግሪ በዛሬው እለት በደማቅ ሁኔታ ያስመረቀው፡፡ በምርቃቱ የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የአካደሚክ ፣ምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግር እና ማህበ/አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር በዛብህ ወንድሙ እንዳሉት መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ19 አመታት ቆይታው የዛሬዎቹን 1089 ተመራቂዎችን ጨምሮ ከሀምሳ ሺ በላይ /50,000/ በላይ ተማሪዎች አስተምሮ ማስመረቅ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እና የእለቱ የክብር እንግዳ የተከበሩ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ለተመራቂ ተማሪዎች እና ወላጆች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ካስተላለፉ በኋላ እንዳሉት ዛሬ እዚህ የተሰበሰብነው ለተራ ኩነት አይደለም፤ ህልም ወደ እውነት የተቀየረበትን ጉዞ ለማክበር ነው። ዛሬ የምናከብረው የትጋት ድል ነው፤ የጽናት ድል ነው፤ የወላጆች እንባ ወደ ደስታ የተለወጠበት ቀን ነው፤ የመምህራን ድካም ፍሬ ያፈራበት ቀን ነው።"የረጅም ጉዞ መጨረሻ የሌላ ጉዞ መጀመሪያ ነው። "ዛሬ አንድ ጉዞ ተጠናቋል፤ ነገር ግን ከዚህ በኋላ የምትጀምሩት ጉዞ ከዩኒቨርሲቲ ጉዞአችሁ የበለጠ ኃላፊነት፣ የበለጠ ፈተና እና የበለጠ እድል ያለው ነው ብለዋል፡፡ ክቡር ፐሬዝዳንቱ አክለውም ዛሬ የምትቀበሉት ዲግሪ በተለይ የጤና ባለሙያዎች ከሌሎች ሙያዎች የሚለየው አንድ ልዩ አደራ አለው። ከዛሬ ጀምሮ በእጃችሁ መሳሪያ ብቻ አይኖርም፤ የሰው ሕይወት አደራ ይኖራል።ታካሚ ወደ ሆስፒታል ሲመጣ ሁለት ነገሮችን ይዞ ይመጣል፤ ሕመሙን እና ተስፋውን። የምትሰጡት ሕክምና ሕመሙን ሊቀንስ ይችላል፤ ነገር ግን የምታሳዩት ርህራሄ፣ የምትናገሩት አጽናኝ ቃል እና የምትሰጡት ክብር ተስፋውን ያድሳል። የዛሬው ዓለም በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI)፣ በዲጂታል ጤና፣ በቴሌሜዲሲን እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እየተለወጠ ነው። ቴክኖሎጂ ብዙ ነገሮችን ልታደርግ ትችላለች፤ ግን ሰብዓዊ ርህራሄን፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባርን እና ሕሊናን ልትተካ አትችልም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በፕሮግሙ ማጠቃለያም ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተመራቂዎች ሜዳሊያ እና የዋንጫ ሽልማት ከክቡር ፕሬዝዳንቱ እጅ ተረክበዋል፡፡ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ጽ/ቤት

He thanked the organizers, facilitators, and participating teachers for their commitment and encouraged the graduates to apply the knowledge and skills they had acquired to enrich their professional practice and promote innovative, technology-enhanced education. - Public and International Relations Executive Office #Kotebe_University_ofEducation_committed_to_excellence_in_Education Follow us for more information: Facebook፡ https://web.facebook.com/www.kue.edu.et Website: https://www.kue.edu.et/ YouTube: https://youtube.com/@kueducation Facebook (https://web.facebook.com/www.kue.edu.et) Log in or sign up to view See posts, photos and more on Facebook

The AI-Enhanced Pedagogy Training Workshop is Concluded Successfully at KUE *** *** *** (KUE, June 18, 2026) – Kotebe University of Education (KUE), in collaboration with the United States Embassy in Addis Ababa, successfully concluded a nine-day professional development workshop titled "AI-Enhanced Pedagogy," held from June 8–18, 2026. According to the program coordinator, Dr. Dejen Chaka, the training focused on integrating artificial intelligence into education while emphasizing ethical principles, legal compliance, digital repositories, and the development of educational resources. The workshop empowered teachers to transition from being consumers of digital content to becoming creators of innovative learning materials. Participants gained practical experience in developing e-portfolios to showcase and store their digital work, creating e-books, designing interactive student worksheets using AI-powered tools like MagicSchool AI, enhancing language teaching skills, and exploring a wide range of other AI-supported educational applications. During the closing ceremony, three participant representatives shared testimonials highlighting the practical knowledge, professional growth, and transformative experiences they gained throughout the training. They emphasized that the workshop had strengthened their confidence and equipped them with valuable digital skills that they will apply in their classrooms. Delivering his closing remarks, the lead trainer, Professor Nega Worku Debela, reflected on the participants' inspiring journey of learning, discovery, and innovation over the past nine days. He noted that the workshop climaxed in remarkable achievements, with participants acquiring advanced digital competencies and AI-enhanced pedagogical skills that will significantly improve their professional practice. He explained that the teachers are now capable of developing and using their own AI-powered educational applications to teach English speaking, listening, reading, and writing more effectively, thereby creating engaging, innovative, and learner-centred classroom experiences. Representing the United States Embassy in Addis Ababa, Mr. George, the Regional English Language Officer, commended both the trainers and participants for their commitment and hard work throughout the program. He expressed confidence that the knowledge and practical skills acquired during the workshop would foster continuous educational innovation, strengthen teaching quality, and contribute to preparing the next generation with the knowledge and skills needed for the future. Speaking at the closing ceremony, Dr. Teshome Nekatibeb, President of Kotebe University of Education, stated that the training would make a significant contribution to improving the University's teaching and learning process. He highlighted that the AI applications developed during the workshop will enable teachers to explain complex concepts and difficult vocabulary in more practical, interactive, and engaging ways. He further noted that the creative projects presented by the participants clearly demonstrated the transformative potential of artificial intelligence in education. Dr. Teshome expressed his sincere appreciation to Professor Nega Worku Debela for leading the training with dedication and expertise, as well as to the United States Embassy in Addis Ababa for its generous support in making the program a success. At the conclusion of the workshop, certificates were awarded to participants who successfully completed the training. In his closing remarks, Dr. Alebachew Kemisso, Vice President for Academic Affairs, emphasized that the "AI-Enhanced Pedagogy" training had made a significant contributions to enhancing teaching and learning through the effective integration of artificial intelligence.