uz
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Kanalga Telegram’da o‘tish

📈 Telegram kanali የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU analitikasi

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 376 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 6 129-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 349-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 376 obunachiga ega bo‘ldi.

24 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 522 ga, so‘nggi 24 soatda esa 23 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 27.03% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining N/A% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 880 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 0 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 33 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Kanal uchun tavsif kiritilmagan.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 25 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

14 376
Obunachilar
+2324 soatlar
+1087 kunlar
+52230 kunlar
Postlar arxiv
ሰሙነ ሕማማት ዕለተ ሰኑይ መርገመ በለስ "በማለዳም ወደ ከተማ ሲመለስ ተራበ። በመንገድም አጠገብ በለስ አይቶ ወደ እርስዋ መጣ፤ ከቅጠልም ብቻ በቀር ምንም አላገኘባትምና፦ ለዘላለሙ ፍሬ አይገኝብሽ
ሰሙነ ሕማማት ዕለተ ሰኑይ መርገመ በለስ "በማለዳም ወደ ከተማ ሲመለስ ተራበ። በመንገድም አጠገብ በለስ አይቶ ወደ እርስዋ መጣ፤ ከቅጠልም ብቻ በቀር ምንም አላገኘባትምና፦ ለዘላለሙ ፍሬ አይገኝብሽ አላት። በለሲቱም ያንጊዜውን ደረቀች። ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው፦ በለሲቱ ያንጊዜውን እንዴት ደረቀች? ብለው ተደነቁ።" ማቴ 21፡18-20 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የ2016 ዓ.ም የሆሣዕና በዓል በርካታ ሕፃናት በተገኙበት በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ተከበረ ሚያዚያ 20/08/2016 ዓ.ም (የሰንበት /ት/ቤቶች አን
+9
የ2016 ዓ.ም የሆሣዕና በዓል በርካታ ሕፃናት በተገኙበት በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ተከበረ ሚያዚያ 20/08/2016 ዓ.ም (የሰንበት /ት/ቤቶች አንድነት) የ2016 ዓ.ም የሆሣዕና በዓል በአዲስ አበባ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለምና ወደብረ ትጉኃን ቅዱስ ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አዘጋጅነት 50 ከሚሆኑ ደብራት የተወጣጡ ቁጥራቸው ከ2000 በላይ የሆኑ ሕፃናት በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተከብሯል። በበዓሉ ላይ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ሐላፊ ተገኝተዋል። በተለያዩ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ሕፃናቱ የተዘጋጁ የልዩ ልዩ የመዝሙርና የኪነ ጥበብ መርሐ ግብር ፣ የጥያቄ እና መልስ ውድድር ፣ የስዕል አውደ ርዕይ እና ሌሎችም መርሐ ግብሮች ቀርበዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ሆሣዕና "የሚቀድሙትም ሕዝብ የሚከተሉትም፦ ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።" ማቴ 21፡9 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻና
ሆሣዕና "የሚቀድሙትም ሕዝብ የሚከተሉትም፦ ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።" ማቴ 21፡9 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️ Youtube

ሆሣዕና “ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ።” መዝ 8፡2 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️ Youtube
ሆሣዕና “ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ።” መዝ 8፡2 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️ Youtube

ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለበዓለ ትንሣኤ የነድያን ማስፈሰኪያ መርሐ ግብርን በሚመለከት የተሰጠ መግለጫ። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን "ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል።" ምሳሌ 19፦17 የሰንበት ት/ቤቶች ላለፉት ረጅም ዓመታት ዋነኛ የሆነውን ህጻናት እና ወጣቶች የተምሮ ማስተማር ሥራ በተጨማሪ ህጻናት ወጣቶች እና ጎልማሶች የተማሩትን በሕይወት እንዲተገብሩ የተለያዩ ክፍላትን በማደራጀት ወንጌልን በተግባር እንዲተረጉሙ እያደረጉ ይገኛሉ። ይህን አገልግሎት ከሚያከናውኑባቸው አበይት ክፍሎች አንድ የበጎ አድራጎት ክፍል ተጠቃሽ ነው። ዛሬ ይህን መግለጫ ለመስጠት ያነሳሳን በአዲስ አበባ ብቻ የሚገኙ ከ250 በላይ ሰንበት ት/ቤቶች በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እና ትንሳኤ በዓል ሰንበት ት/ቤቶች በተናጠል በየ አጥቢያቸው ከ 200 እስከ 3000 ነደያንን በአንድ ቀን በመመገብ በድምር በአንድ በዓል በአማካይ 125,000 በላይ ነደያንን እና አቅመ ደካሞችን የመመገብ አገልግሎት ላለፉት አሥርት ዓመታት ሲተገብሩ ቆይተዋል ከዚህም በተጨማሪ አገልግሎታቸውን በማስፋት የአበይት በዓላት የነበረውን አገልገሎት ወደ nሚነት በመቀየር ላይ ይገኛሉ ከአገልገሎቶቹም መሃል ምሳሌ ለመጥቀስ 1. የነደያን የሳምንታዊ እና ወርሃዊ ምገባ እና ቃለ እግዚአብሔር እንዲማሩ ማድረግ እና ለስጋ ወደሙ እነዲበቁ ማድረግ 2. የነደያን ልጆችን ከመዋዕለ ህጻናት ከፍቶ ከማስተማር ጀምሮ ዘላቂ ድጋፍ በመስጠት እስከ ከፍተኛ ደረጃ ትምህርት እንዲማሩ ማድረግ እና በዘላቂ ፕሮጀቸቶች ራስን የማስቻል ተግባራት 3. መድኃኒት መግዣ ያጡ ህሙማንን የመድኃኒት መግዣ በመደገፍ ከሥጋዊ መከራ በመታደግ 4. የጎዳና ተዳዳሪ ወንድሞች እና እኅቶችን በምገባ እና ቃለ እግዚአብሔርን በማስተማር 5. ደጋፊ የሌላቸውን ጸበልተኞች በመደገፍ 6. ለአለአስፈላጊ ሥራ የተደረጉ እህቶችን ካሉበት ሕይወት በማውጣት ቃለ እግዚአብሔር በማስተማር እና በመደገፍ 7. በቤታቸው ሆነው ዝቅተኛ ገቢ ኖሯቸው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ለሚገኙ ቤተሰቦች እና ጧሪ ቀባሪ ለሌላቸው ቤተሰቦች ከወር የቤት ወጪ ጀምሮ እስከ በዓላት ማስፈሰክ እነዚህ እና እነዚህን የመሰሉ አያሌ ሥራዎች በሰንበት ት/ቤቶች እየተሠሩ ይገኛሉ። በመሆኑም ዛሬ ከፊታችን በሚከበረው የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ሰንበት ት/ቤቶች ምዕመናንን ከቀድሞ በበለጠ ደረጃ በማስተባበር እና በማሳተፍ ከዚህ ቀድሞ ከምታደርጉት የበጎ አድራጎት አገልግሎት በስፋት በማስተባበር የድርሻችንን እንድንወጣ እያሳሰብን ተርቤ አብልታችሁኛል ፤ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛል ታርዤ አልብሳችሁኛል ታምሜ ጠይቃችሁኛል የሚለውን የጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ጥያቄ ሁላችንም ለመፈጸም እንችል ዘንድ ሀ- ምእመናን በጉልበታችሁ በገንዘባችሁ በእውቀታችሁ በቅርባችሁ በሚገኙ አድባራት እና ገዳማት ሰንበት ት/ቤቶች ጋር በመገኘት ከበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ እና የዘላቂ በጎ አድራጎት ስራቸውንም በመረዳት ከጎናችው በመሆን እነድትደግፉ፡፡ ለ- የዚህን በጎ አድራጎት ስራ ለመደገፍ ፈቃደኛ የሆናችው የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች በቀሪዎቹ ቀናት ውስጥ ሀሳቡ ብዙሃን ጋር እንዲደረስ የበኩላችሁን በቅስቀሳ እነድታግዙን ሐ- የሰንበት ት/ቤትን ፍሬ በህይወታችሁ የቀመሳችሁ ቀደምት አባላት እንዲሁም አሁንም በማገልገል ላይ የምትገኙ ካህናት ፤ መምህራነ ወንጌል ፤የኪነ ጥብብ ባለሙያዎች፤ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ፤ በየሙያ ዘርፉ የምትገኙ ሁላችሁም ምእመናን የበጎ አድራጎቱ በረከት ተሳታፊ እንዲሆኑ እግዚአብሔር የሰጣችውን ፀጋ በመጠቀም በቅስቀሳ እንድታግዙ፡፡ እናንተም በጉለበታችሁ ፤በገንዘባችሁ እና በእውቀታችሁ ያሳደገቻችሁ ሰንበት ት/ቤት በመገኘት በአገልገሎት ላይ ያሉ ወንዲሞች እና እህቶችን በማገዝ እንድታበረቱ ሰንበት ት/ቤታችሁ ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡ መ- የገዳማት እና አድባራት አስተዳደር አካላት የሰበካ ጉባኤ እንዲሁም የምግባረ ሠናይ ክፍሎች ይህን የተቀደሰ የቤተክርስቲያን አገልግሎት ሰንበት ት/ቤቶቹ በተሻለ እንዲፈጽሙ በማገዝ እና በመርዳት ሥራቸው እንዲቀላጠፍ የበኩላችሁን እንድትወጡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጥሪውን ያቀርባል። ሠ- በዚህ የበጎ አድራጎት ስራ በዘላቂነት በየሰንበት ት/ቤቱ ያለውን የተደራሽነት አቅም በመጠቀም በበጎ አድራጎት ስራው በመላው ወይም በከፊል አዲስ አበባ የሰንበት ት/ቤቶችን አገልግሎት መደገፍ የምትፈልጉ ድርጅቶች እና ግለሰቦች በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ልማት እና በጎ አድራጎት ክፍል ጋር በመገኘት የበጎ አድራጎት ስራውን በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች መፈጸም የምትችሉ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ መግለጽ እንወዳለን። "ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል እንደ ስጦታውም መልሶ ይከፍለዋል።" ምሳሌ 19፡17 በሚለው አምላካዊ ቃል መሠረት ብድራችንን ብል እና ነቀዝ በማያበላሹት ሌቦችም ቆፍረው በማይሰርቁት በሰማይ ለናንተ መዝገብ ሰብስቡ ማቴ 6፡20 እንደተባለ እኛም ኑ በሰማያዊ መዝገባችንን እንጻፍ ብለን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

''ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል'' ምሳ 19÷17 የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በበዓለ ትንሣኤ የነድያን ማስፈሰኪያ መርሐ ግብርን በሚመለከት መግለጫ ሰጠ። ሚያዚያ 18/08/2016 ዓ.ም (የሰንበት /ት/ቤቶች አንድነት) የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ የአ.አ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፤ መምህር ደምስ የአ/አ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ክፍል ኃላፊ በተገኙበት በበዓለ ትንሣኤ የነድያን ማስፈሰኪያ መርሐ ግብርን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥቷል። በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት በሁሉም አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ከ500,000 በላይ ነደያንን በበዓለ ትንሣኤ የማስፈሰክ መርሐ ግብር ላይ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የበኩሉን አስተዎጽኦ እንዲያደርግ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአ.አ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥሪ አድርገዋል። ''ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል።'' መዝ 40÷1 አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ ሰንበት ት/ቤቶች ከዚህ ቀደም ስያከናውኑ የነበረውን የበጎ አድራጎት ሥራ በተለይም በበዓላት ነዳያንን የመመገብ ሥራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ በዚህ እግዚአብሔር አምላክ እንደሚያድን እና እንደሚጠብቅ በማስገንዘብ በዚህ ዓመትም በአ/አ በሚገኙ ከ231 በላይ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ላይ ሊደረግ የታሰበውን የነዳያን ምገባ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ምዕመናን ፤ የሚዲያ አካላትና አንቂዎች፤ የሰንበት ት/ቤት ፍሬዎች፤ የኪነ ጥበብ ሰዎች፤ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ሁሉ በየ አካባቢያቸው በሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች በመሔድ በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በልዩ ልዩ ቁሳቁስና ዕውቀት ድጋፍ ማድረግ እንደሚችሉ ተገልጿል። ''ብድራችንን ብል እና ነቀዝ በማይበላሹት ሌቦችም ቆፍረው በማይሰርቁት በሰማይ ለናንተ መዝገብ ሰብስቡ'' ማቴ 6÷20 እንደተባለ እኛም ኑ በሰማያዊ መዝገባችንን እንጻፍ ብለን ጥሪያችንን እናስተላልፍለን ። በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ሆሣዕና “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው።” ማቴ 21፡9 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️ Youtube
ሆሣዕና “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው።” ማቴ 21፡9 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️ Youtube

#በዓለ_ሆሣዕናን_ከሕፃናት_ጋር በዕለተ ሆሣዕና ሚያዚያ 20 2016 ዓ.ም ከቀኑ 6፡30 ጀምሮ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና ደብረ ትጉኀን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አዘጋጅነት የሚከናወነው የዘንድሮ የሆሣዕና በዓል የሕፃናት መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ከሚገኙ ከ50 በላይ ሰንበት ት/ቤቶች እና ከ2000 በላይ ሕፃናት ይሳተፉበታል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

#በዓለ_ሆሣዕናን_ከሕፃናት_ጋር በዕለተ ሆሣዕና ሚያዚያ 20 2016 ዓ.ም ከቀኑ 6፡30 ጀምሮ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና ደብረ ትጉኀን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት
#በዓለ_ሆሣዕናን_ከሕፃናት_ጋር በዕለተ ሆሣዕና ሚያዚያ 20 2016 ዓ.ም ከቀኑ 6፡30 ጀምሮ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና ደብረ ትጉኀን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አዘጋጅነት የሚከናወነው የዘንድሮ የሆሣዕና በዓል የሕፃናት መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ከሚገኙ ከ50 በላይ ሰንበት ት/ቤቶች እና ከ2000 በላይ ሕፃናት ይሳተፉበታል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok