የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览
频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 376 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 129,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 349 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 376 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 522,过去 24 小时变化为 23,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 27.03%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 880 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
14 376
订阅者
+2324 小时
+1087 天
+52230 天
帖子存档
ሰሙነ ሕማማት ዕለተ ሰኑይ መርገመ በለስ
"በማለዳም ወደ ከተማ ሲመለስ ተራበ። በመንገድም አጠገብ በለስ አይቶ ወደ እርስዋ መጣ፤ ከቅጠልም ብቻ በቀር ምንም አላገኘባትምና፦ ለዘላለሙ ፍሬ አይገኝብሽ አላት። በለሲቱም ያንጊዜውን ደረቀች። ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው፦ በለሲቱ ያንጊዜውን እንዴት ደረቀች? ብለው ተደነቁ።" ማቴ 21፡18-20
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+9
የ2016 ዓ.ም የሆሣዕና በዓል በርካታ ሕፃናት በተገኙበት በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ተከበረ
ሚያዚያ 20/08/2016 ዓ.ም (የሰንበት /ት/ቤቶች አንድነት)
የ2016 ዓ.ም የሆሣዕና በዓል በአዲስ አበባ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለምና ወደብረ ትጉኃን ቅዱስ ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አዘጋጅነት 50 ከሚሆኑ ደብራት የተወጣጡ ቁጥራቸው ከ2000 በላይ የሆኑ ሕፃናት በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተከብሯል። በበዓሉ ላይ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ሐላፊ ተገኝተዋል። በተለያዩ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ሕፃናቱ የተዘጋጁ የልዩ ልዩ የመዝሙርና የኪነ ጥበብ መርሐ ግብር ፣ የጥያቄ እና መልስ ውድድር ፣ የስዕል አውደ ርዕይ እና ሌሎችም መርሐ ግብሮች ቀርበዋል።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ሆሣዕና
"የሚቀድሙትም ሕዝብ የሚከተሉትም፦ ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።" ማቴ 21፡9
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት!
✍️ Youtube
ሆሣዕና
“ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ።” መዝ 8፡2
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት!
✍️ Youtube
ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለበዓለ ትንሣኤ የነድያን ማስፈሰኪያ መርሐ ግብርን በሚመለከት የተሰጠ መግለጫ።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
"ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል።" ምሳሌ 19፦17
የሰንበት ት/ቤቶች ላለፉት ረጅም ዓመታት ዋነኛ የሆነውን ህጻናት እና ወጣቶች የተምሮ ማስተማር ሥራ በተጨማሪ ህጻናት ወጣቶች እና ጎልማሶች የተማሩትን በሕይወት እንዲተገብሩ የተለያዩ ክፍላትን በማደራጀት ወንጌልን በተግባር እንዲተረጉሙ እያደረጉ ይገኛሉ። ይህን አገልግሎት ከሚያከናውኑባቸው አበይት ክፍሎች አንድ የበጎ አድራጎት ክፍል ተጠቃሽ ነው።
ዛሬ ይህን መግለጫ ለመስጠት ያነሳሳን በአዲስ አበባ ብቻ የሚገኙ ከ250 በላይ ሰንበት ት/ቤቶች በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እና ትንሳኤ በዓል ሰንበት ት/ቤቶች በተናጠል በየ አጥቢያቸው ከ 200 እስከ 3000 ነደያንን በአንድ ቀን በመመገብ በድምር በአንድ በዓል በአማካይ 125,000 በላይ ነደያንን እና አቅመ ደካሞችን የመመገብ አገልግሎት ላለፉት አሥርት ዓመታት ሲተገብሩ ቆይተዋል ከዚህም በተጨማሪ አገልግሎታቸውን በማስፋት የአበይት በዓላት የነበረውን አገልገሎት ወደ nሚነት በመቀየር ላይ ይገኛሉ ከአገልገሎቶቹም መሃል ምሳሌ ለመጥቀስ
1. የነደያን የሳምንታዊ እና ወርሃዊ ምገባ እና ቃለ እግዚአብሔር እንዲማሩ ማድረግ እና ለስጋ ወደሙ እነዲበቁ ማድረግ
2. የነደያን ልጆችን ከመዋዕለ ህጻናት ከፍቶ ከማስተማር ጀምሮ ዘላቂ ድጋፍ በመስጠት እስከ ከፍተኛ ደረጃ ትምህርት እንዲማሩ ማድረግ እና በዘላቂ ፕሮጀቸቶች ራስን የማስቻል ተግባራት
3. መድኃኒት መግዣ ያጡ ህሙማንን የመድኃኒት መግዣ በመደገፍ ከሥጋዊ መከራ በመታደግ
4. የጎዳና ተዳዳሪ ወንድሞች እና እኅቶችን በምገባ እና ቃለ እግዚአብሔርን በማስተማር
5. ደጋፊ የሌላቸውን ጸበልተኞች በመደገፍ
6. ለአለአስፈላጊ ሥራ የተደረጉ እህቶችን ካሉበት ሕይወት በማውጣት ቃለ እግዚአብሔር በማስተማር እና በመደገፍ
7. በቤታቸው ሆነው ዝቅተኛ ገቢ ኖሯቸው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ለሚገኙ ቤተሰቦች እና ጧሪ ቀባሪ ለሌላቸው ቤተሰቦች ከወር የቤት ወጪ ጀምሮ እስከ በዓላት ማስፈሰክ እነዚህ እና እነዚህን የመሰሉ አያሌ ሥራዎች በሰንበት ት/ቤቶች እየተሠሩ ይገኛሉ።
በመሆኑም ዛሬ ከፊታችን በሚከበረው የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ሰንበት ት/ቤቶች ምዕመናንን ከቀድሞ በበለጠ ደረጃ በማስተባበር እና በማሳተፍ ከዚህ ቀድሞ ከምታደርጉት የበጎ አድራጎት አገልግሎት በስፋት በማስተባበር የድርሻችንን እንድንወጣ እያሳሰብን
ተርቤ አብልታችሁኛል ፤
ተጠምቼ አጠጥታችሁኛል
ታርዤ አልብሳችሁኛል
ታምሜ ጠይቃችሁኛል የሚለውን የጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ጥያቄ ሁላችንም ለመፈጸም እንችል ዘንድ
ሀ- ምእመናን በጉልበታችሁ በገንዘባችሁ በእውቀታችሁ በቅርባችሁ በሚገኙ አድባራት እና ገዳማት ሰንበት ት/ቤቶች ጋር በመገኘት ከበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ እና የዘላቂ በጎ አድራጎት ስራቸውንም በመረዳት ከጎናችው በመሆን እነድትደግፉ፡፡
ለ- የዚህን በጎ አድራጎት ስራ ለመደገፍ ፈቃደኛ የሆናችው የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች በቀሪዎቹ ቀናት ውስጥ ሀሳቡ ብዙሃን ጋር እንዲደረስ የበኩላችሁን በቅስቀሳ እነድታግዙን
ሐ- የሰንበት ት/ቤትን ፍሬ በህይወታችሁ የቀመሳችሁ ቀደምት አባላት እንዲሁም አሁንም በማገልገል ላይ የምትገኙ ካህናት ፤ መምህራነ ወንጌል ፤የኪነ ጥብብ ባለሙያዎች፤ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ፤ በየሙያ ዘርፉ የምትገኙ ሁላችሁም ምእመናን የበጎ አድራጎቱ በረከት ተሳታፊ እንዲሆኑ እግዚአብሔር የሰጣችውን ፀጋ በመጠቀም በቅስቀሳ እንድታግዙ፡፡ እናንተም በጉለበታችሁ ፤በገንዘባችሁ እና በእውቀታችሁ ያሳደገቻችሁ ሰንበት ት/ቤት በመገኘት በአገልገሎት ላይ ያሉ ወንዲሞች እና እህቶችን በማገዝ እንድታበረቱ ሰንበት ት/ቤታችሁ ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡
መ- የገዳማት እና አድባራት አስተዳደር አካላት የሰበካ ጉባኤ እንዲሁም የምግባረ ሠናይ ክፍሎች ይህን የተቀደሰ የቤተክርስቲያን አገልግሎት ሰንበት ት/ቤቶቹ በተሻለ እንዲፈጽሙ በማገዝ እና በመርዳት ሥራቸው እንዲቀላጠፍ የበኩላችሁን እንድትወጡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጥሪውን ያቀርባል።
ሠ- በዚህ የበጎ አድራጎት ስራ በዘላቂነት በየሰንበት ት/ቤቱ ያለውን የተደራሽነት አቅም በመጠቀም በበጎ አድራጎት ስራው በመላው ወይም በከፊል አዲስ አበባ የሰንበት ት/ቤቶችን አገልግሎት መደገፍ የምትፈልጉ ድርጅቶች እና ግለሰቦች በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ልማት እና በጎ አድራጎት ክፍል ጋር በመገኘት የበጎ አድራጎት ስራውን በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች መፈጸም የምትችሉ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ መግለጽ እንወዳለን። "ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል እንደ ስጦታውም መልሶ ይከፍለዋል።" ምሳሌ 19፡17 በሚለው አምላካዊ ቃል መሠረት ብድራችንን ብል እና ነቀዝ በማያበላሹት ሌቦችም ቆፍረው በማይሰርቁት በሰማይ ለናንተ መዝገብ ሰብስቡ ማቴ 6፡20 እንደተባለ እኛም ኑ በሰማያዊ መዝገባችንን እንጻፍ ብለን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
''ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል'' ምሳ 19÷17
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በበዓለ ትንሣኤ የነድያን ማስፈሰኪያ መርሐ ግብርን በሚመለከት መግለጫ ሰጠ።
ሚያዚያ 18/08/2016 ዓ.ም (የሰንበት /ት/ቤቶች አንድነት)
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ የአ.አ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፤ መምህር ደምስ የአ/አ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ክፍል ኃላፊ በተገኙበት በበዓለ ትንሣኤ የነድያን ማስፈሰኪያ መርሐ ግብርን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥቷል።
በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት በሁሉም አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ከ500,000 በላይ ነደያንን በበዓለ ትንሣኤ የማስፈሰክ መርሐ ግብር ላይ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የበኩሉን አስተዎጽኦ እንዲያደርግ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአ.አ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥሪ አድርገዋል።
''ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል።'' መዝ 40÷1 አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ ሰንበት ት/ቤቶች ከዚህ ቀደም ስያከናውኑ የነበረውን የበጎ አድራጎት ሥራ በተለይም በበዓላት ነዳያንን የመመገብ ሥራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ በዚህ እግዚአብሔር አምላክ እንደሚያድን እና እንደሚጠብቅ በማስገንዘብ በዚህ ዓመትም በአ/አ በሚገኙ ከ231 በላይ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ላይ ሊደረግ የታሰበውን የነዳያን ምገባ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ምዕመናን ፤ የሚዲያ አካላትና አንቂዎች፤ የሰንበት ት/ቤት ፍሬዎች፤ የኪነ ጥበብ ሰዎች፤ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ሁሉ በየ አካባቢያቸው በሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች በመሔድ በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በልዩ ልዩ ቁሳቁስና ዕውቀት ድጋፍ ማድረግ እንደሚችሉ ተገልጿል።
''ብድራችንን ብል እና ነቀዝ በማይበላሹት ሌቦችም ቆፍረው በማይሰርቁት በሰማይ ለናንተ መዝገብ ሰብስቡ'' ማቴ 6÷20 እንደተባለ እኛም ኑ በሰማያዊ መዝገባችንን እንጻፍ ብለን ጥሪያችንን እናስተላልፍለን ። በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ሆሣዕና
“ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው።” ማቴ 21፡9
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት!
✍️ Youtube
ዕረፍቱ ለቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ
https://www.tiktok.com/@eotc_gssu/video/7361815304537771294
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
