Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)
Kanalga Telegram’da o‘tish
9 383
Obunachilar
+1224 soatlar
+137 kunlar
+7430 kunlar
Postlar arxiv
+8
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ 11 ወራት እቅድ አፈጻጸምና በሌሎች ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ
EED ሰኔ 2/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ ያለፉት 11 ወራት እቅድ አፈጻጸም፣ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 አፈጻጸም፣ የቀጣይ በጀት ዓመት መነሻ እቅድ እና ሌሎች የዘርፉ ስራዎች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡
በተቋሙ የማኔጅመንት አዳራሽ በተካሄደው ውይይት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ የበጀት ዓመቱ 11 ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን የቀጣይ አቅጣጫም ተቀምጧል፡፡ ለኢንሺየቲቩ ስኬት ሁሉም የበኩሉን አስተዋጾ እንዲያደርግም ተጠይቋል፡፡
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 አፈጻጸም ሪፖርት፣ የዋና ዋና ስራዎች በጀት አጠቃቀም ሪፖርት፣ የዘርፉ ቀጣይ ወራት እቅድና የስራ አካባቢን ምቹ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ላይ ውይይትና የጋራ መግባባት ተደርሷል፡፡
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://youtu.be/_82DFVufJCA?si=bEoDjLFUnGiueodL
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
‹‹መሰረተ ሰፊ የኢንዱስትሪ ልማት ለመገንባት ለአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች በቂ ትኩረት መስጠት ይገባል!››
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://www.youtube.com/watch?v=3A5F3LsrBKY
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://www.youtube.com/watch?v=G_CyA8XBaww
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት
#የገጠር_ኢንዱስትራላይዜሽን
#ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
+6
እንቶት የፈሳሽ ሳሙና
========/////==========
EED ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
ለምሳሌ እንቶት ፈሳሽ ሳሙና አምራች ማህበር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን እነር መገር ወረዳ ሚቄ ከተማ የሚገኝ አነስተኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ነው።
ኢንተርፕራይዙ በ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር መነሻ ካፒታል በ2018 ዓ.ም በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ በተፈጠረው ንቅናቄ በ5 ወጣቶች የተመሠረተና ለ27 ወጣቶች የስራ እድል የፈጠረ የተለያዩ መጠን ያላቸውን ፈሳሽ ሳሙና የሚያመርት ኢንተርፕራይዝ ነው።
‹‹እንቶት›› የጉራጌኛ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ተባብረን በሀገር እንስራ የሚል እንደሆነ የሚናገሩት የማህበሩ ሰብሳቢ ፈትለወርቅ ጸጋ በግብርና ስራ ያገኙትን ሀብት መነሻ በማድረግ እና ያለውን የገበያ ፍላጎት በመመስረት ስራውን እንደጀመሩ ይገልጻሉ፡፡
በቅርቡም የደረቅ ሳሙና ምርቶችን በማምረት ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ በዝግጅት ላይ እንደሆኑና የኤሌክትሪክ ሐይል አቅርቦት እንዲመቻችላቸው ጠይቀዋል፡፡
ለአካባቢው ከተሞችና የገጠር ቀበሌዎች ምርቶቻቸውን በስፋት እያቀረቡ መሆኑንና ከተጠቃሚዎችና ከባለሙያዎች የሚሰጣቸውን አስተያየትም እንደግብዓት በመጠቀም የምርቱን ጥራት ለመጠበቅ በትኩረት እየሰሩ መሆኑን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል፡፡
#አድራሻ፡
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን እነር መገር ወረዳ ሚቄ ከተማ
☎️ስልክ፡ 09 97 48 79 80/ 09 98 16 79 80
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት
#የገጠር_ኢንዱስትራላይዜሽን
#ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
+6
አንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ
=======/////========
EED ግንቦት 27 ቀን 20178 ዓ.ም
አንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ ‹እናት ዱቄት› በሚል ስያሜ የተለያየ መጠን ያላቸውን የስንዴ ዱቄት እያመረተ የሚገኝና በሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀቤላ ቲላ ወረዳ የሚገኝ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ነው።
ኢንተርፕራይዙ በ4 ሚሊዮን ብር መነሻ ካፒታል በ2018 ዓ.ም በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ በተፈጠረው ንቅናቄ ስራ ጀምሯል።
የእናት ዱቄት መስራች አንዋር ነስሮ እንደሚናገረው በአካባቢው ያለውን ክፍተትና የገበያ ፍላጎት መሰረት በማድረግ ወደስራ መግባታቸውንና የተለያየ መጠን ያላቸውን የስንዴ ዱቄት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ሰአት አጠቃላይ ሀብቱን ወደ 40 ሚልየን ብር ማሳደጉን የሚገልጸው አንዋር ለ9 ቋሚና 20 ለሚሆኑ ሰራተኞች ጊዚያዊ የስራ እድል መፍጠሩንም ይናገራል፡፡
በአካባቢው ለሚገኙ ከተሞች ምርታቸውን በስፋት እያቀረቡና በተጠቃሚዎች ዘንድ ተቀባይነታቸውንና የማምረት አቅማቸውን ለማሳደግ እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግሯል፡፡
በሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት አማካኝነት ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ የወሰዷቸው ማሽኖቹ የማምረት አቅም በቀን 24 ቶን መሆኑን የሚገልጸው አንዋር የስራ ማስኬጃ እጥረትና የኤሌክትሪክ ሐይል መቆራረጥ በሚፈልጉት ደረጃ እንዳይሰሩ እንቅፋት እንደሆነባቸውና የአቅማቸውን 20 በመቶ ብቻ እየተጠቀሙ እንደሚገኝ ይገልጻል፡፡
#አድራሻ፡
ሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀቤላ ቲላ ወረዳ
☎️ስልክ፡ 0918999843
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት
#የገጠር_ኢንዱስትራላይዜሽን
#ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://www.youtube.com/watch?v=9uOEiSL5mF0
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
ስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክቸሪንግ፡- ከወዳደቁ ነገሮች ጭስ አልባ ከሰል የሚያመርት ኢንተርፕራይዝ
========/////==========
EED ግንቦት 26 ቀን 20178 ዓ.ም
ስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክቸሪንግ ከወዳደቁ ቆሻሻዎች ጭስና ሽታ አልባ ኮኮ የተሰኘ ከሰል የሚያመርት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ የሚገኝ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ነው።
ኢንተርፕራይዙ በ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር መነሻ ካፒታል በ2018 ዓ.ም ህዳር ወር በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ በተፈጠረው ንቅናቄ በ2 ጓደኛሞች የተመሠረተ አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ነው።
ስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክቸሪንግ ምክትል ስራ አስኪያጅና መስራች ወጣት አብዱልካፍ ሽኩር እንደሚናገረው ሽታና ጭስ አልባ የሆነውን ኮኮ ከሰል ለማምረት እንደ ጫት ገረባ፣ ቡና ገለባ፣ ሰጋቱራና ደቃቅ ከሰል ከመሳሰሉ በአካባቢው የሚገኙና የሚጣሉ ግብአቶችን ይጠቀማል።
ለከሰል ምርት የሚቆረጡ ዛፎችን መጠን በመቀነስ የአየር ንብረትን በጠበቀ ሁኔታ ከሰል እያመረቱ መሆኑን የሚገልጸው ም/ስራ አስኪያጁ የፈርነስ/ካራቦናይዜሽን ማሽንን በመጠቀም ካርቦን ሞኖ ኦክሳይድ የሌለው ከሰል እያመረቱና የከሰል ጭስን 95 በመቶ እየቀነሱ በመሆናቸው የህብረተሰቡን ጤናን እየጠበቁ መሆኑን ይስረዳል፡፡
ስራው ሲጀመር ዝቅ ብሎ መስራትና መቆሸሽ ይኖረዋል የሚለው አብዱልካፍ አሁን ወደከፍታ እየተሸጋገሩና በሶስት ፈረቃ እያሰሩ በመሆናቸው በአሁኑ ሰአት 2 ነጥብ 5 ሚልየን ብር ጠቅላላ ሀብት በማንቀሳቀሰ ለ25 ቋሚና 12 ጊዚያዊ/ኮሚሽን ሰራተኞች የስራ እድል መፍጠራቸውን ይናገራል፡፡
ከኬራቲ ጀምሮ እስከ አዲስ አበባ ገበያ ምርቶቻቸውን በስፋት እያቀረቡ መሆኑን የሚገልጸው አብዱልካፍ ቆሻሻ ሀብት መሆኑን በመረዳት ወደሀብት እየቀየሩና ማህበረሰቡ ይህንን እንዲረዳም እየሰሩ መሆኑን ይናገራል፡፡
ምርቶቻቸው ጥራት ያለው፣ ጭስና ሽታ አልባ እንዲሁም ለረዥም ጊዜ የሚቆይ በመሆኑ ተመራጭ መሆናውንና ትላልቅ ሱፐር ማርኬቶች፣ ሆቴሎች በተለይም ኮንዶሚኒየምና አፓርታማ አካባቢ የሚገኙ የማህረሰብ ክፍሎች ምርቶችቸውን በስፋት እየተጠቀሙ መሆኑን ይገልጻል፡፡
ስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክቸሪንግ ከኮኮ ከሰል በተጨማሪ የተፈጥሮ ሽታ ያላቸውን አበባዎች በመጠቀም ብሑሮችና እጣኖችን እንዲሁም ደረቅ ሳሙናዎችን በማምረት ለተጠቃሚዎች በማቅረብም ላይ ይገኛል፡፡
ያለባቸውን የአቅም ውስንነት በመቅረፍም በስፋት ወደ ገበያ የመግባት እቅድ እንዳላቸው የገለጸው አብዱልካፍ ተጨማሪ ማሽኖች የሚያገኙባቸው ሆኔታዎች እንዲመቻችላቸውና ያለባቸው የኤሌክትሪክ ሐይል አቅርቦት ችግር እንዲፈታላቸውም ጥሪ አቅርቧል፡፡
#አድራሻ፡
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ ኬራቲ ከተማ
☎️ስልክ፡ 09 11 57 31 71/ 09 75 73 33 33
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት
#የገጠር_ኢንዱስትራላይዜሽን
#ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
በስደት ያጠራቀሙትን እውቀትና ገንዘብ ለሀገር ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፡ አቶ ስምኦን እና የ“ጭቶ ቡና” የስኬት ጉዞ
EED ግንቦት 25/2018 ዓ.ም
ቡና ለኢትዮጵያዊያን መጠጥ ብቻ አይደለም፤ ባህል፣ ታሪክ፣ የማህበራዊ ህይወት መስተጋብርና የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ጭምር ነው። በዚህ ሰፊ የቡና ባህልና ብዝሃ-ህይወት ውስጥ ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመናዊ ማኑፋክቸሪንግና እሴት በመጨመር (Value Addition) ረገድ የብዙዎችን ትኩረት እየሳበና የኢንዱስትሪው አዲስ ተስፋ እየሆነ የመጣ አንድ ስኬታማ የሀገር በቀል ኢንተርፕራይዝ አለ:- ጭቶ ቡና።
ይህ ኢንተርፕራይዝ በልዩ ጣዕሙና በጥራቱ የሚታወቀውን የኢትዮጵያን ቡና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ፣ የሀገራችንን የቡና ገበያ ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሸጋግር የሚችል ትልቅ አቅም ይዞ ብቅ ብሏል።
የኢንተርፕራይዙ መስራች አቶ ስምኦን ሰርፁ ይባላሉ። አቶ ስምኦን ለረጅም ዓመታት ኑሯቸውን በውጭ ሀገር አድርገው የነበረ ቢሆንም፣ የሀገራቸውን ጥሪ ሰምተው በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። ወደ ሀገር ቤት ሲመለሱም ዝም ብለው አልነበረም፤ በማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ በመሰማራት ከፍተኛ ጥራት ያለውና እሴት የተጨመረበትን የኢትዮጵያ ቡና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ትልቅ ራዕይ ሰንቀው እንጂ።
አቶ ስምኦንና ጭቶ ቡና ጥሬ ቡናን ዝም ብሎ ከመላክ ይልቅ በዘመናዊ ማሽኖች የተቆላ፣ የተፈጨና የታሸገ ከፍተኛ ጥራት ያለው ምርት በማዘጋጀት ወደ ውጭ ሀገር በመላክ ላይ ይገኛሉ። ይህ ጉዟቸው ደግሞ በቅርቡ እጅግ አስደሳች ወደሆነ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል፤ ድርጅቱ በቅርብ ጊዜ በትልቁ የዓለም የገበያ መዳረሻ በሆነችው ቻይና ላይ አዲስ ቅርንጫፍ መክፈት ችሏል።
የጭቶ ቡና የዛሬ ስኬት በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ጉዞው የጀመረው ከ4 ዓመታት በፊት ነበር። በወቅቱ በነበረው የፍራንኮ ቫሉታ ዕድል በመጠቀም ዘመናዊ የቡና ማቀነባበሪያ ማሽኖችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት፣ ስራቸውን በኪራይ ቤት ውስጥ በጠበበ ቦታ ጀመሩ። ስራ ሲጀምሩም በ5 ሰዎች ብቻ ነበር። ዛሬ ላይ ግን ጭቶ ቡና ያንን የፈተና ጊዜ አልፎ በመስፋፋት ላይ ይገኛል። በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ለገጣፎ የሚገኘውና በጥራትና በዘመናዊ አሰራር ላይ ባደረገው ትኩረት አሁን ላይ ከ40 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተረጋጋና ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠር ችሏል።
አቶ ስምኦን ስለ ጉዟቸውና ስላጋጠሟቸው እክሎች ሲናገሩ “ችግር የማደግ ምልክት ነው። እኛ ችግሮችን እንደ ፈተና በመውሰድ፣ ፈተናውን እንዴት ማለፍ እንደሚቻል ብቻ ትኩረት አድርገን እንሰራለን” በማለት የጠንካራ ስራና የዕድገት አስተሳሰብ (Growth Mindset) መርሆቸውን ይገልጻሉ።
ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና የወደፊት ተስፋ
ጭቶ ቡና በአሁኑ ወቅት የቡናውን ተፈጥሯዊ ጣዕምና መዓዛ ሳይለቅ፣ የዓለም አቀፍ ገበያን የጥራት መመዘኛ በሚያሟላ መልኩ እጅግ ዘመናዊ ማሽኖችን በመጠቀም ምርቱን እያዘጋጀ ይገኛል። ይህ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደግሞ ምርቱ በዓለም መድረክ ተወዳዳሪ እንዲሆን አድርጎታል።
ኢንተርፕራይዙ አሁን ካለበት ተስፋ ሰጪ ደረጃ ተነስቶ ይበልጥ እንዲያድግና የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ ግን የመስሪያ ቦታ አቅርቦት ወሳኝ መሆኑን መስራቹ ሳይጠቅሱ አላለፉም። በቀጣይም የተሻለና ሰፊ የመስሪያ ቦታ ቢመቻችላቸው፣ ይበልጥ ሰፊ የስራ ዕድል በመፍጠርና ምርትን በማሳደግ ረገድ ከዚህ የተሻለ የላቀ ውጤት ለማምጣት በትጋት እንደሚሰሩ አቶ ስምኦን ሰርፁ ገልጸዋል።
የጭቶ ቡና ጉዞ ለሌሎች ተመላሽ ዳያስፖራዎችና የሀገር ውስጥ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች ትልቅ ማሳያና አምሳያ ነው። በችግሮች ሳይበገሩ፣ ቴክኖሎጂን ከሀገር ምርት ጋር በማቀናጀት የተጀመረው ይህ ጉዞ፣ የኢትዮጵያን ቡና ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ ይበልጥ ከፍ እንደሚያደርገው ጥርጥር የለውም። ለመሰል ጠንካራ አምራች ኢንተርፕራይዞች የሚደረግ ማንኛውም ድጋፍ ደግሞ የሀገርን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት የመገንባት ያህል ዋጋ አለው።
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!
ግንቦት 25 2018 ዓ.ም
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡
ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
መልካም የእሁድ እረፍት ለኢኮኖሚያችን ፈርጦች! ☕🏠
==============//=========
ማኑፋክቸሪንግ ማለት ማሽንና ጥሬ ዕቃ ብቻ አይደለም፤ ከጀርባው የቤተሰብ ኃላፊነት፣ የልጆች ተስፋ እና የሀገር ኩራት ያለበት ታላቅ ጥበብ እንጂ።
ሳምንቱን ሙሉ ስታመርቱ የነበራችሁ አምራቾቻችን ዛሬ ከቤተሰቦቻችሁ ጋር መልካም የደስታ ጊዜ እንድታሳልፉ እንመኛለን!
የተሳካ ሳምንት የሚጀምረው በታደሰ አእምሮና በእሁድ ዕቅድ ነው። ውድ የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ባለቤቶች፤ ነገ አዲስ የሥራ ሳምንት እና ትልቅ ሀገራዊ ጉዳይ አለብን! ሳምንቱን ስንጀምር በታደሰ ተነሳሽነት፣ በጥራትና በፈጠራ ወደፊት ለመራመድ ዛሬ እሁድን በሚገባ እረፍት እናድርግ!
💡 ትናንሽ እርምጃዎች ወደ ታላላቅ ፋብሪካዎች ይመራሉ። እኛም በዕውቀትና በቴክኖሎጂ ከጎናችሁ ነን!
🇪🇹 የእሁድ ማሳሰቢያ፡ ዛሬ ለቤተሰብዎ የሚሸምቱት ማንኛውም ዕቃ የሀገር ውስጥ ምርት መሆኑን በማረጋገጥ አምራቾቻችንን ይደግፉ!
#የኢትዮጵያ_ኢንተርፕራይዝ_ልማት #እሁድ #ቤተሰብ #ኢትዮጵያ_ታምርት #SMEs
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopmen
የሳምንቱ መጨረሻ ቀናት መልዕክት! 🛠️🇪🇹
======////=====
ስኬት በአንድ ጀምበር አይገነባም፤ በየቀኑ በሚደረጉ ጥቃቅን ጥረቶች እንጂ። በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የተሰማራችሁ አምራቾች በሙሉ፣ በየቀኑ ለምታሳዩት ጽናት ትልቅ ክብር አለን።
ዛሬ ቅዳሜ ቢሆንም፣ የሀገር ውስጥ ምርትን የመደገፍና የመሸመት ጉዟችን አይቆምም! የሀገራችንን ምርት እንሸምት፣ አምራቾቻችንን እናበረታታ!
በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማራችሁ ኢንተርፕራይዞች፣ ሳምንቱን በምን ዓይነት ትልቅ ስኬት ወይም መልካም ተሞክሮ አጠናቀቃችሁ?
1️⃣ አዲስ የገበያ ትስስር ፈጠርን?
2️⃣ የምርት ጥራታችንን አሻሻልን?
3️⃣ አዳዲስ ሠራተኞችን ቀጠርን?
ከነዚህ ውጪም የሆነ ስኬት ካላችሁ ኮሜንት ላይ አጋሩን፤ እርስ በርስ እንማማር፣ እንነቃቃ!
#WeekendMotivation
#EthiopiaTamrit #MadeInEthiopia
#የኢትዮጵያ_ኢንተርፕራይዝ_ልማት
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopmen
“የፀና ቃል፤ የላቀ እምርታ!"
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopmen
የፋሲካ ባልትናና ቅመማ ቅመም የጥራትና የስኬት ጉዞ ፦ ከባልትና ምርት ወደ ምርምር ማዕከል የግንባታ ራዕይ ጉዞ
EED ግንቦት 20/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ የምግብ ባህል በደመቁና ልዩ ጣዕም ባላቸው ቅመማ ቅመሞች የታወቀ ነው። ይህንን ባህላዊ ጣዕም ጠብቆ፣ በጥራትና በከፍተኛ ደረጃ አዘጋጅቶ ለገበያ ማቅረብ ደግሞ ከፍተኛ ጥንቃቄና ዘመናዊ አሰራርን ይጠይቃል። በተለይም በሀገራችን የሆቴልና የቱሪዝም ኢንዱስትሪ እያደገ በመጣበት በአሁኑ ወቅት፣ ለትልልቅ ሆቴሎችና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን ለጠበቁ መስተንግዶዎች አስተማማኝና ጥራት ያለው የባልትና ምርት ማቅረብ የገበያው ወሳኝ ፍላጎት ሆኗል። ይህንን ክፍተት በከፍተኛ ብቃት በመሙላት በዘርፉ ግንባር ቀደም ስም መሆን የቻለው ፋሲካ ባልትናና ቅመማ ቅመም ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ማዕከል በሆነው ሳሪስ አካባቢ ዋና የምርት ማዕከሉን አድርጎ የሚንቀሳቀሰው ፋሲካ ባልትና በ5 ወንድምና እህቶች እና በ50 ሺህ ብር ካፒታል በ2006 ዓ.ም ስራ የጀመረው ስራ ዛሬ ላይ 90 ሚልየን ብር በማንቀሳቀስ ለ108 ሰራተኞች የስራ እድል መፍጠር ችሏል።
ፋሲካ ባልትናና ቅመማቅመም ጠንካራ መሠረት ያለው የቤተሰብ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ነው። ኢንተርፕራይዙ እንደ አንድ የቤተሰብ ስራ ከመጀመሩ ባሻገር የቤተሰብ አባላት ለስራው ያላቸው ትጋት፣ ሙያዊ ክህሎትና ትውፊታዊ እውቀት ዛሬ ለደረሰበት ከፍተኛ ደረጃና አስተማማኝነት ዋነኛ ምሰሶ ሆኗል።
የፋሲካ ባልትና ልዩ መለያው የወቅታዊ በዓላት ገበያን ጠብቆ የሚንቀሳቀስ ሳይሆን፣ ዓመቱን ሙሉ ከፍተኛ ጥራትና ቀጣይነት ያለው አቅርቦት ለሚፈልጉ ከትልልቅ ሆቴሎችና ሬስቶራንቶችጋር በቋሚነት መስራቱ ነው። ትልልቅ ሆቴሎች በምግብ ጥራትና በንፅህና አጠባበቅ ላይ ያላቸው መመዘኛ በጣም ጥብቅ በመሆኑ፣ ፋሲካ ባልትና ይህንን መስፈርት አሟልቶ የብዙዎቹ ቀዳሚ ምርጫ መሆን ችሏል።
ፋሲካ ባልትና እና ቅመማ ቅመም ዛሬ ላይ ካለው የአቅርቦትና የገበያ መሪነት ባሻገር ወደፊት የዘርፉን ዕድገት ወደ ላቀ ሳይንሳዊ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅና አርቆ አሳቢ ራዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። ኢንተርፕራይዙ በምርት ጥራት፣ ደህንነትና አዳዲስ ምርቶች ልማት ላይ በስፋት ለመስራት ትልቅ የቅመማቅመም ምርምርና ስርፀት (R&D) ማዕከል የማቋቋም ራዕይ ሰንቆ እየሠራ ይገኛል።
ይህ ማዕከል ሲቋቋም የኢትዮጵያን ባህላዊ ቅመማቅመሞች ሳይንሳዊ ይዘትና የጤና ጥቅሞች በጥናት በመደገፍ፣ ለሆቴል ኢንዱስትሪው የሚቀርቡ ምርቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና ይበልጥ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማድረግ ሰፊ ፋይዳ ይኖረዋል።
ባልትናን በሻማ አሽጎ ከመሸጥ የተነሳው ይህ የባልትናና ቅመማቅመም ማቀነባበሪያ ኢንተርፕራይዝ፣ የረጅም ጊዜ ልምዱንና ዘመናዊ አሰራርን በማጣመር በኢትዮጵያ የሆቴል አቅርቦት ዘርፍ ላይ ትልቅ አሻራ ማሳረፍ ችሏል። ምርትን ወቅታዊ በዓላት ላይ ብቻ ሳይገድብ፣ የትልልቅ ሆቴሎችን ከፍተኛ መመዘኛ አሟልቶ በቋሚነት ማቅረቡ ለሌሎች ኢንተርፕራይዞችም ትልቅ ምሳሌ ነው። ወደፊት የሚገነባው የምርምር ማዕከልም ለሀገር ውስጥ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ትልቅ ኩራትና ተስፋ እንደሚሆን ይጠበቃል።
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopmen
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
