uz
Feedback
Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ethiopian Enterprise Developmen (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Ko'proq ko'rsatish
9 803
Obunachilar
+624 soatlar
+247 kun
+12230 kun
Postlar arxiv
ለአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ አመራርና ባለሙያዎች መሰጠት የጀመረው ሀገራዊ የአቅም ግንባታ ስልጠና
+9
ለአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ አመራርና ባለሙያዎች መሰጠት የጀመረው ሀገራዊ የአቅም ግንባታ ስልጠና

በ2018 በጀት ዓመት በአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች 270 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል!   ለአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ አመራርና ባለሙያዎች ሀገራዊ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ EED መስከረም 9/2019 ዓ.ም  (አዳማ) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት አዲስ በተቋቋሙና በተጠናከሩ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች 270 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን አስታወቀ::   ይህ የተገለጸው ከመላው ኢትዮጵያ ለተወጣጡ 160 ለሚሆኑ የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ አመራርና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት በተጀመረበት ወቀት ነው። የልማት መስሪያ ቤቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታህ የሱፍ በስልጠናው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ተቋሙ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 526/2015 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ተወዳዳሪ ሆነው በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ሽግግር፣ በተኪ ምርት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራና በኤክስፖርት እድገት ላይ ጉልህ ሚና እንዲጫወቱ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 4 ሺህ 233 አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች መቋቋማቸውንና በዚህም ለ270,546 ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን ገልጸዋል::   ከዚህም በተጨማሪ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት በተሰራው ስራ 1 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር የሚያወጡ ምርቶችን መተካት መቻሉንና ወደውጭ በተላኩ ምርቶች 36 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ዶላር መገኘቱን ተናግረዋል::   ም/ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም  የዘርፉን ምርታማነትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚሰጡ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፣ የእድገት ሽግግር፣ የቴክኖሎጂ ልማት፣ የጥራት አስተዳደርና የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ስራዎችና ድጋፎች የተሳለጡና ወጥ መሆን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። ሰልጣኞች ከስልጠናው የሚያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ በየአካባቢያቸው ለሚገኙ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች አቅም የሚገነባና ውጤታማ ድጋፍ እንዲሰጡ ም/ዋና ዳይሬክተሩ አደራ ብለዋል:: #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት!   ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡   https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

https://www.youtube.com/@ethiopiaenterprise ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን እና ስራ ፈጠራን ይደግፋሉ? በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ተሰማርተዋል? ወይንስ ለመሰማራት አስበዋል? የ
https://www.youtube.com/@ethiopiaenterprise ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን እና ስራ ፈጠራን ይደግፋሉ? በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ተሰማርተዋል? ወይንስ ለመሰማራት አስበዋል? የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የዩቲዩብ ቻናልን በመቀላቀል የሀገራችንን አነስተኛ እና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች የስኬት ጉዞ ይከታተሉ! 📌 ቻናላችንን Subscribe በማድረግ፡ ·         «የአምራች ሥነ-ልቦና» ፕሮግራሞችን እና የኢንተርፕራይዞችን የልምድ ልውውጥ ያገኛሉ! ·         አዳዲስ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ እና የሙያ ዕውቀቶችን ይሸምታሉ! ·         የሀገር ውስጥ አምራቾችን የስኬት ታሪክ በመመልከት ለራስዎ ተነሳሽነት ይፈጥራሉ! ·         የሀገር ውስጥ ምርቶችን ያስተዋውቃሉ፤ አዳዲስ የገበያ እና የንግድ ትስስሮችን ይፈጥራሉ! 🔗 አሁኑኑ የዩቲዩብ ገጻችንን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ! https://www.youtube.com/@ethiopiaenterprise #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት!   ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡   https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

https://www.youtube.com/watch?v=CkfShJ_Q3Ww #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት! ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡ https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

የተስፋና የትጋት ፍሬ፦ የቱምሃ ሳሙና አርአያነት ያለው የስኬት ማዕበል EED መስከረም 5/2019 ዓ.ም ​ቱምሃ ሳሙና በ5 አባላት (አቶ ዘመኑ፣ ታከለና ጓደኞቻቸው) ሽርክና ማህበር በ2010 ዓ.ም ፈሳሽ ሳሙና በማምረት ወደ ስራ የገባ መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ነው፡፡ ​የኢንተርፕራይዙ መስራች አባልና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘመኑ መለሠ "ቱምሃ ሳሙና" ስራውን ለመጀመር በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በኩል የተገኘው የሙያ ስልጠናና ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደነበረው ገልፀዋል፡፡ ​በተለይም በተቋሙ የተገኘው የሙያ ክህሎት ስልጠና አባላቱ ከተለያየ የስራ ዘርፍ የመጡ በመሆናቸው ስራውን ለመጀመር መሰረት እንደሆናቸው የገለፁት አቶ ዘመኑ፤ ከሙያ ስልጠና በተጨማሪ ከምርት አመራረት እስከ ገበያ አጠቃቀምና ተወዳዳሪነት ድረስ በተቋሙ የተደረገላቸው ድጋፍ ትልቅ አቅም እንደሆናቸው ተናግረዋል፡፡ ይህም ኢንተርፕራይዙ ጥራት ያላቸውን የጽዳትና የዲተርጀንት ምርቶች በስፋት እንዲያመርትና በዘርፉ ውጤታማ እንዲሆን ያስቻለው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ​ያለ ቴክኖሎጂ ድጋፍ በአባላቱ ከፍተኛ ትጋት፣ የሰው ኃይል ጉልበትና ጥንካሬ በተለይም ፈሳሽ ሳሙና በማምረት ስራውን የጀመረው ቱምሃ ሳሙና፤ አሁን ላይ በመንግስት በተመቻቸለት የማምረቻ ቦታ ዘመናዊ ማሽኖችን በመጠቀም 16 አይነት የጽዳት፣ የዲተርጀንትና የውበት መጠበቂያ ዕቃዎችን በብዛትና በጥራት እያመረተ ይገኛል፡፡ በ1,000 ብር መነሻ ካፒታል የተጀመረው ቱምሃ ሳሙና፤ በአባላቱ የማያወላውል ስራ ወዳድነትና ጥንካሬ አሁን ላይ ከ40 ሚሊዩን ብር በላይ ካፒታል በማስመዝገብ ለ110 ዜጎችም የስራ ዕድል መፍጠር ችሏል፡፡ ​ኢንተርፕራይዙ የተለያዩ የዲተርጀንትና የጽዳት አገልግሎት ያላቸውን ምርቶች በስፋት በማምረት ለግለሰቦች፣ ለሆቴሎች፣ ለኢንዱስትሪዎች፣ የጽዳት አገልግሎት ለሚሰጡ ተቋማትና ለአከፋፋዮች በማቅረብ የገበያ ተደራሽነቱን ማስፋፋት ችሏል፡፡ ቱምሃ ሳሙና ስታንዳርዱን የጠበቀ ጥራት ያለው ምርት እንዲያመርት በየ3 ወሩ በደረጃዎችና ተስማሚነት ተቋማት በኩል የጥራት ፍተሻ እየተደረገለት እንደሚገኝና በዚህም ሰርቲፋይ መሆኑን የሚገልፁት አቶ ዘመኑ፤ ከዚህ በተጨማሪም ኢንተርፕራይዙ የራሱ የጥራት ፍተሻ ሚኒ ላብራቶሪ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ​በአሁኑ ወቅት በሃገራችን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚወጣባቸውን የጽዳትና የዲተርጀንት ምርቶች በሃገር ውስጥ በጥራትና በስፋት በማምረት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ኢንተርፕራይዙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡ ቱምሃ ሳሙና ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችን በስፋት በማምረት የሃገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሸፈንም ባለፈ ወደ ውጭ ሀገር ኤክስፖርት የማድረግ ሰፊ እቅድ እንዳለው የሚገልፁት አቶ ዘመኑ፤ ለዚህም በተለይም የጥሬ ዕቃ አቅርቦት፣ የፋይናንስ፣ የውጪ የገበያ ትስስርና መሰል ድጋፎች እንደሚያስፈልጉት ገልፀዋል፡፡ ​ኢንተርፕራይዙ በስራ ሂደት የሚያጋጥሙትን ችግሮች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት እየሰራ በመሆኑ ችግሮቹን በመፍታት በስኬት እንዲጓዝ እንዳስቻለውም አብራርተዋል፡፡ ​የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ብዙ ፈተናዎች ያሉበት ቢሆንም በከፍተኛ ጥንካሬና በትጋት ከተሰራ ውጤታማ መሆን የሚቻልበት ሰፊ ዕድል ያለው በመሆኑ፤ በተለይም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሚተኩ የጽዳትና የዲተርጀንት ምርቶች ላይ ለሚሰማሩ አምራቾች መንግስት በልዩነት ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚገባ አቶ ዘመኑ አሳስበዋል፡፡ ወጣቶችም በዘርፉ በመሰማራትና ጠንክረው በመስራት የራሳቸውን ሀብትና ንብረት ማፍራት እንዲሁም ሀገርን መጥቀም እንዳለባቸው መክረዋል፡፡ ​#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት!   ​ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡   https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

በግጭት ጉዳት የደረሰባቸው አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች እና ባለሙያዎችን ለመደገፍ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ይፋዊ የማስጀመሪያ ፕሮግራም እየተካሄደ ነው ​EED መስከረም 5/2019 ዓ.ም ​የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በአማራ ክልል 5 ከተሞች የሚገኙና በግጭት ጉዳት የደረሰባቸው አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች እና ባለሙያዎችን መልሶ ለማቋቋምና ለመደገፍ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ይፋዊ የማስጀመሪያ ፕሮግራም እያካሄደ ነው። ​መድረኩን የከፈቱት የልማት መ/ቤቱ የዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግርማው ፈረደ እንደተናገሩት፣ ፕሮግራሙ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች እና ዘርፉን የሚደግፉ ባለሙያዎች በስነ-ልቦና እንዲዘጋጁ ከመደገፉም በላይ በዘላቂነት ወደ ሙሉ ምርትና አገልግሎት እንዲመለሱ የሚያስችል  ስራዎችን ያካተተ ነው። ከዚህ በፊት በግጭት ጉዳት የደረሰባቸው አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች እና የዘርፉ ባለሙያዎች ወደነበሩበት የስራ መንፈስ እንዲመለሱና እንዲነቃቁ የስነ ልቦና ማነቃቂያ መርሃ ግብር መካሄዱን አውስተዋል:: ​ከጀርመን አለም አቀፍ የልማት ድርጅት (GIZ) እና አጋር ተቋማት በተገኘው ድጋፍ የሚተገበረው ይህ  የአቅም ግንባታ ፕሮግራም በደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር እና ደብረ ብርሃን የሚገኙ 75 አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን እንዲሁም 25 ባለሙያዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል። ​በዚህ ይፋዊ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት፣ ከአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ፣ ከስራና ክህሎት ቢሮ እና ፕሮጀክቱ ከሚተገበርባቸው 5 ከተሞች የመጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል። ​#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት!   ​ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡   https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች ወደ ኢትዮጵያ ገጠር፡ የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ጉዞ! 🚀🌾🏭 ############////####### የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ በገጠር ያለውን ሃብት በተለይም ጥሬ እቃ እሴት በመጨመርና የበለጠ ዋጋ ሊያወጣ በሚችል መንገድ በመጠቀም ማቀነባበርና ማምረት የሚያስችል ሲሆን ይህም ተጨማሪ አምራች ኢንተርፕራይዞችን ለማቋቋምና የስራ እድል ለመፍጠር ያስችላል፡፡ ​ግብርናን ከማዘመን ባለፈ የሀገርን ኢኮኖሚ መዋቅራዊ እሴት የሚቀይር አገራዊ ንቅናቄ ነው። በገጠር አካባቢዎች የማኑፋክቸሪንግ እንቅስቃሴዎችን ማስፋፋት የሥራ ዕድል ይፈጥራል፣ የከተሞችን ጥግግት ይቀንሳል፣ እንዲሁም ሀገራዊ ምርታማነትን ያፋጥናል። ​ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች፡ ሀገራት እንዴት ተለወጡ? 🌍✨ ⚙️​ጃፓን (One Village One Product - OVOP) 🇯🇵፦ እያንዳንዱ መንደር ወይም አካባቢ ባለው ልዩ የግብርና ወይም የባህላዊ ሀብት ላይ ትኩረት አድርጎ ጥራት ያለው አንድ ዋና ምርት እንዲያመርት በማድረግ የገጠር ኢኮኖሚዋን አንሰራራች። ⚙️​ቻይና (Township and Village Enterprises - TVEs) 🇨🇳፦ በገጠር መንደሮች የተከፈቱ አነስተኛ ማኑፋክቸሪንግና ማቀነባበሪያዎች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ከድህነት ያወጡ ሲሆን፣ ለዛሬው ግዙፍ የአለም ኤክስፖርት አቅሟ መሠረት ጥለዋል። ⚙️​ሕንድ (One District One Product - ODOP) 🇮🇳፦ እያንዳንዱ ወረዳ በያዘው ልዩ ሀብት (በግብርና፣ በቆዳ ወይም በእጅ ጥበብ) ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ ምርቱን ወደ ዓለም ገበያ እንዲያወጣ በማድረግ ሰፊ የኢኮኖሚ ንቅናቄ ፈጥራለች። ⚙️​የኢትዮጵያ መንገድ፡ ፕሮግራሙ ከተጀመረ የተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶች 🇪🇹 ​ኢትዮጵያ እነዚህን ስኬታማ ተሞክሮዎች ከሀገራዊ እውነታ ጋር በማጣጣም የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭን መተግበር ጀምራለች። ​የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ፕሮግራሙን በበላይነት እያስተባበረ የሚገኝ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ ከተጀመረ ወዲህ 1 ሺህ የሚሆኑ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች በገጠር ወረዳዎች እንዲቋቋሙ ተደርጓል! ​📘 ተግባራዊ የማንዋል ዝግጅት፦ የአተገባበር ሂደቱ ሳይንሳዊና ወጥ ይሆን ዘንድ ማስፈጸሚያ ማንዋል ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል። ​💡 የአቅም ግንባታ፦ ለፈፃሚዎችና ለኢንተርፕራይዞች ተደጋጋሚ ስልጠናዎች ተሰጥቷል። ​🔍 ቀጣይነት ያለው ድጋፍ፦ ኢንተርፕራይዞቹ ውጤታማ እንዲሆኑ የቅርብ ክትትልና የቴክኒክ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል። ​የዚህ በጀት ዓመት ግቦችና የቀጣይ ትኩረት 🎯 ​በተገኙ ጅምር ውጤቶች ላይ በመመሥረት፣ በያዝነው በጀት ዓመት፦ ​1,578 አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በገጠር ወረዳዎች ለማቋቋም ታቅዷል። ​ከተለያዩ ባለድርሻ ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት የትኩረት አቅጣጫ ተደርጎ የተያዘ ሲሆን፣ ይህም የፋይናንስ፣ የመሰረተ ልማትና የገበያ ትስስር ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ያስችላል። ​ይህ እንቅስቃሴ የገጠር ሀብታችንን ወደ ተመረተ እሴት በመቀየር የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄን ግብ ለማሳካት ትልቅ ሚና ይጫወታል። ​👉 ለእርስዎ፦ በገጠር ወረዳዎች በሚቋቋሙ ኢንተርፕራይዞች ውስጥ የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ድጋፍ የትኛውን ክፍተት በይበልጥ ይቀርፋል ብለው ያስባሉ? ሃሳብዎን በኮሜንት ያካፍሉን! 👇 ​#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት!   ​ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡   https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች ወደ ኢትዮጵያ ገጠር፡ የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ጉዞ! 🚀🌾🏭
+6
ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች ወደ ኢትዮጵያ ገጠር፡ የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ጉዞ! 🚀🌾🏭

እንኳን ለ2019 ዓ.ም በሠላም አደረሳችሁ! ​የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች በበቂ የፋይናንስ፣ የማማረቻ ማዕከላት፣ የግብዓት፣ የቴክኖሎጂ፣ የክህሎትና የገበያ ትስስር አቅማቸው ጎልብቶ ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲሸጋገሩ፣ ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉና የተኪና የወጪ ምርት አቅማቸውን እንዲገነቡ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል፤ በዚህም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ​በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርምን መነሻ በማድረግ ዘርፉን ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል። በተለይም የዘርፉን ተወዳዳሪነት የሚያረጋግጠውን የአምራች ኢንዱስትሪ አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎችን በስኬት አጠናቀን ወደ ትግበራ ምዕራፍ ተሸጋግረናል። የአገልግሎት አሰጣጣችንን ለማዘመን፣ የሥራ አካባቢያችንን ይበልጥ ምቹና ሳቢ ለማድረግ እንዲሁም ለተቋማዊ ስኬታችን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አጋሮቻችንና የሥራ ባልደረቦቻችን እውቅና ለመስጠት ሰፊ ተግባራት ተከናውነዋል። በተጨማሪም የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሼቲቭን ወደ ትግበራ በማስገባት የአካባቢን ፀጋ ወደ ምርት የመቀየርና ሰፊ የሥራ ዕድል የመፍጠር ሥራ የተሠራ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም አምራቾቻችን ምርቶቻቸውን የሚያስተዋውቁበትና ሰፊ የገበያ ዕድል የሚያገኙበት መድረክ ተፈጥሯል። ​በአዲሱ የበጀት ዓመትም የተጀመረውን የሪፎርም ትግበራ አጠናክረን በመቀጠል፣ የኢንተርፕራይዞቻችንን የምርት ጥራትና ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ሁለንተናዊ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን እንሰራለን። የሀገራችንን የኢኮኖሚ ጥገኝነት ለመቀነስና የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ የሚደረገውን የሀገር ውስጥ ምርት የመተካትና የወጪ ምርት ድጋፍም አጠናክረን እንቀጥላለን። ​ለእቅዶቻችን ስኬትና ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ እድገት ለምትተጉ የተቋማችን መላው ሠራተኞችና አመራሮች፣ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም ከጎናችን ለሆናችሁ ባለድርሻ አካላትና የልማት አጋሮቻችን በሙሉ የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ​አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የፍቅር፣ የምርታማነትና የታላቅ ስኬት እንዲሆንልን እመኛለሁ! ​በድጋሚ መልካም አዲስ ዓመት! ​አለባቸው ንጉሴ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር

የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ «የእመርታ ቀን»ን አስመልክቶ በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ «ተኪ ምርትን» አስመልክቶ የሰጡትን ጠቃሚ ማብራሪያና ምላሽ እንድትከታተሉ ጋበዝን!   🎬 ቪዲዮውን ይመልከቱ! ​#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት!   ​ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡   https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ «የእመርታ ቀን»ን አስመልክቶ በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ «ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ»ን አስመልክቶ የሰጡትን ጠቃሚ ማብራሪያና ምላሽ እንድትከታተሉ ጋበዝን!   🎬 ቪዲዮውን ይመልከቱ! ​#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት!   ​ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡   https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት የነገው ቀን ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር ከወረቀት ወደ ዲጂታል፤ ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባ
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት የነገው ቀን ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር ከወረቀት ወደ ዲጂታል፤ ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ ነው። ንግድና አገልግሎትን ያቀላጥፋል፣ መረጃዎችን ተደራሽ ያደርጋል፣ ዘርፎችንም ያዘምናል! የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያ ኮደሮች ንቅናቄ ወጣቶችን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣሪ በማድረግ ወደ 7 ሚሊዮን ግባችን እያመራ ሲሆን የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን አረጋግጧል። በሀገር በቀል አቅም የበለጸገው የሳይበር ሉዓላዊነታችን ደግሞ የማንቆጣጠራቸው ቴክኖሎጂዎችን ጥገኝነት አላቆ በዲጂታል ኢኮኖሚ በራስ አቅሟ የምትቆም አዲሷ ኢትዮጵያ በታላቅ ምዕራፍ ላይ መሆኗን በኩራት ያበስራል!

የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ለተቋሙ ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት እና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ ​EED ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም ​የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የ2019 አዲስ ዓመትን ምክንያ
+9
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ለተቋሙ ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት እና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ ​EED ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም ​የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የ2019 አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለተቋሙ ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ያካሄደ ሲሆን፣ ለተማሪዎችም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍም አድርጓል፡፡ ​ተቋሙ ከአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም ከተለያዩ ድጋፍ አድራጊ አካላት ያሰባሰበውን ሀብት በመጠቀም በተቋሙ አነስተኛ ደመወዝ ለሚከፈላቸው ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት ድጋፍ አድርጓል። በተጨማሪም ተማሪ ልጆች ላላቸው ሰራተኞች የሚሆኑ የትምህርት መርጃ ቁሳቁሶችን (ደብተር፣ ቦርሳ እና እስክርቢቶ) አበርክቷል፡፡ ​የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ከመደበኛ ተግባሩ ጎን ለጎን መሰል የማህበራዊ ኃላፊነት ስራዎችን አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። ​#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ማህበራዊ_ኃላፊነት #የሥራ_ዕድል_ፈጠራ ​ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡ https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

የተቋሙ የልህቀት እና የኢንኩቤሽን ማዕከል ግንባታ እና የሰራተኞች አብሮነት ፕሮግራም የተሳካ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጠ ​EED ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም ​የኢትዮጵያ
+9
የተቋሙ የልህቀት እና የኢንኩቤሽን ማዕከል ግንባታ እና የሰራተኞች አብሮነት ፕሮግራም የተሳካ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጠ ​EED ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም ​የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አዲስ እያስገነባ ለሚገኘው የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ የልህቀት እና የኢንኩቤሽን ማዕከል እና የአብሮነት መርሃ ግብር እንዲሳካ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የተለያዩ  ተቋማትና ግለሰቦች የእውቅናና የምስጋና መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡ ​በግንባታ ላይ በሚገኘው የልህቀትና ኢንኩቤሽን ማዕከል ግቢ ውስጥ በተካሄደው በዚህ ፕሮግራም ማዕከሉ ሲጠናቀቅ ለአነስተኛና  መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የክህሎት ማሳደጊያና የኢንኩቤሽን አገልግሎት በመስጠት ለሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተገልጻል፡፡ ለማዕከሉ ግንባታ መሳካትና ለተቋሙ የአመራርና ሠራተኞች የአብሮነት መርሃ-ግብር ስኬት የላቀ ድጋፍ ላደረጉ አካላት የምስክር ወረቀት በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተበርክተዋል፡፡ ​#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት! #ማህበራዊ_ኃላፊነት  #የልህቀት_ማዕከል ​ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡ https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛ ገቢ ላላቸው የተማሪ ወላጆች የትምህርት ቁሳቁስና ለአዲስ በዓል መዋያ ልዩ ልዩ ድጋፍ አደረገ EED ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አ
+7
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛ ገቢ ላላቸው የተማሪ ወላጆች የትምህርት ቁሳቁስና ለአዲስ በዓል መዋያ ልዩ ልዩ ድጋፍ አደረገ EED ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አነስተኛ ገቢ ላላቸው ወላጅ ተማሪዎች ለትምህርት አገልግሎት የሚያስፈልጉ ቦርሳ፤ ደብተርና እስክርቢቶ ድጋፍ አድርጓል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታም ተቋሙ በቋሚነት ለሚደግፋቸው ልጆች የትምህርት ቁሳቁስና ለአዲስ በዓል መዋያ የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ድጋፉ የተደረገው የአመራርና ሠራተኞች የአብሮነት መርሃ-ግብር በተካሄደበት አዲስ እየተገነባ በሚገኘው የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ የልህቀትና ኢንኩቤሽን ማዕከል አካባቢ ለሚገኙ ሕፃናትና ተቋሙ በቋሚነት ለሚደግፋቸው ልጆች ነው፡፡ በስነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ፤ "የአዲስ ዓመት መባቻን ስናከብር አቅም የሌላቸውን ወገኖቻችንን ማሰብና ማገዝ ይገባናል፤ ተቋማችን የጀመረው ይህ የመተሳሰብና የመረዳዳት የበጎ አድራጎት ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል" ብለዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፤ ድጋፉ ማዕከሉ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር አዎንታዊና ጠንካራ ግንኙነት ለመፍጠር የሚያስችል ከመሆኑ ባሻገር፣ ማዕከሉ ግንባታው ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባ ለአካባቢው ነዋሪዎችና ወጣቶች የክህሎት ሥልጠና ለመስጠትና የሥራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ መሠረት እንደሚጥል አስገንዝበዋል። #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት! #ማህበራዊ_ኃላፊነት ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡ https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment