Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)
رفتن به کانال در Telegram
9 712
مشترکین
+824 ساعت
+347 روز
+11330 روز
آرشیو پست ها
https://www.youtube.com/watch?v=5shLca9wqiA
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1501ኛው የነብዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በዓሉ የሰላም እና የጤና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://youtu.be/Evc3KqAWleQ
#የአምራች_ስነ_ልቦና (ክፍል አስራ_ስምንት) - #ጭቶ_ቡና
========////=======
የ“ጭቶ ቡና” የስኬት ጉዞ
በውጭ ሀገር የነበራቸውን ኑሮ በመተው ወደ ሀገራቸው የተመለሱት አቶ ስምኦን ሰርፁ፣ ጥሬ ቡናን ዝም ብሎ ከመላክ ይልቅ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እሴት በመጨመር (Value Addition) የኢትዮጵያን ቡና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ “ጭቶ ቡና” የተሰኘ ኢንተርፕራይዝ መሥርተዋል።
ከ4 ዓመታት በፊት በኪራይ ቤትና በ5 ሰራተኞች ስራ የጀመረው ይህ ኢንተርፕራይዝ፣ በአሁኑ ወቅት በሸገር ከተማ ለገጣፎ አካባቢ ተስፋፍቶ ከ40 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ በቅርቡም በትልቋ የዓለም የገበያ መዳረሻ ቻይና አዲስ ቅርንጫፍ መክፈት ችሏል።
አቶ ስምኦን “ችግር የማደግ ምልክት ነው” በሚል የዕድገት አስተሳሰብ ፈተናዎችን አልፈው የቡናውን ተፈጥሯዊ ጣዕምና መዓዛ የሚጠብቁ ዘመናዊ ማሽኖችን በመጠቀም ምርታቸውን ለዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ አድርገዋል።
በቀጣይም ምርታቸውን በማሳደግ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰሩ የገለፁ ሲሆን፣ የጭቶ ቡና ጉዞ ለተመላሽ ዳያስፖራዎችና ለአገር ውስጥ ስራ ፈጣሪዎች ትልቅ ማሳያ ሆኗል።
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://www.youtube.com/watch?v=NfofgXMK0aQ
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://www.youtube.com/watch?v=FuaKijradHU
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
✨ "ኢትዮጵያ ታምርት፤ እኛም እንሸምት!"
#የሀገር ውስጥ ምርት አጠቃቀም ባህላችን ወዴት እያመራ ነው?
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በህብረተሰባችን ዘንድ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በኩራት የመጠቀም አስደሳች ባህል በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ይገኛል!
🌟 የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞቻችን ምርቶች በጥራት፣ በጥንካሬና በዘመናዊ ዲዛይን እያደጉ መምጣታቸው በገበያው ውስጥ የጎላ ተወዳዳሪነትን ፈጥሮላቸዋል።
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት (EED) ኢንተርፕራይዞች ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን እንዲያመርቱና ህብረተሰቡ የሀገሩን ምርት በስፋት እንዲጠቀም የሚያደርገውን ሁለገብ ድጋፍ አጠናክሮ ቀጥሏል።
💥 ተደራሽነትን ለማስፋት የተከናወኑ አበራች ስራዎች፦
አምራችና ተጠቃሚን በቀጥታ የሚያገናኙ ደማቅ የኤግዚቢሽንና ባዛር የገበያ መድረኮች የተዘጋጁ ሲሆን፣ በልዩ ልዩ የመገናኛ ብዙሃንና ማህበራዊ ሚዲያዎች ሰፊ የማስተዋወቅና የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች ተከናውነዋል፤ አምራች ኢንተርፕራይዞችም ከቀን ወደ ቀን ደረጃቸውንና ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችን ለአገር ውስጥና ለውጭ ገበያ እንዲያቀርቡ አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል!
ይህ ሀገራዊ እንቅስቃሴ ሙሉ ስኬት የሚያገኘው ግን የሁላችንም የጋራ ጥረት ሲታከልበት ሲሆን በተለይም፦
🏭 አምራቾች፦ የምርት ጥራትና ደረጃን ዘወትር የማስጠበቅ፣
🏛 መንግስትና ባለድርሻ አካላት፦ የድጋፍና የገበያ ትስስር ስርዓቱን የማጠናከር፣
🛒 ህብረተሰቡ፦ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በመግዛትና በማበረታታት አጋርነቱን የማሳየት!
💭 የእርስዎ አስተያየት ለውይይት፦
በቅርብ ጊዜ ገዝተዋቸው በጥራታቸውና በጥንካሬያቸው የወደዷቸው የሀገር ውስጥ ምርቶች የትኞቹ ናቸው? 🤔
የሀገር ውስጥ ምርት አጠቃቀም ባህላችን የበለጠ እንዲያድግ ከማህበረሰቡ እና ከአምራቾች ምን ይጠበቃል ይላሉ?
ሀሳብዎን ያካፍሉን!
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
✨ "ኢትዮጵያ ታምርት፤ እኛም እንሸምት!"
#የሀገር ውስጥ ምርት አጠቃቀም ባህላችን ወዴት እያመራ ነው?
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
"ተክተን እናመርታለን፤ ሀገርን እናበለጽጋለን!"
EED ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም
ገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ጥራት ባላቸው የሀገር ውስጥ ምርቶች ለመተካት የተያዘውን ሀገራዊ ራዕይ በግንባር ቀደምትነት እየመራ ይገኛል።
ፓርኩ የሀገርን የምርት አቅም በማሳደግ፣ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ራስን ለመቻልና የሀገር ውስጥ ኢኮኖሚን ለማጠናከር የሚደረገውን ጥረት በከፍተኛ ደረጃ በማፋጠን ላይ ነው::
ይህ እንቅስቃሴ ከውጭ የሚገቡ ዕቃዎች ላይ ያለውን ጥገኝነት በመቀነስ ረገድ የሚከተሉትን ዋና ዋና ውጤቶች እያረጋገጠ ይገኛል፡
የውጭ ምንዛሬን ማዳንና ኢኮኖሚን ማጠናከር፡ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ውጭ እንዳይወጣ በማስቀረት ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት አስተዋጽኦ እያደረገ ነው።
የጥራትና የውድድር አቅምን ማሳደግ፡ የሀገር ውስጥ አምራቾች የጥራት ደረጃቸውን እንዲያሳድጉ፣ የምርት ሂደታቸውን እንዲያዘምኑና በሀገር ውስጥም ሆነ በክልላዊ ገበያዎች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ትልቅ ዕድል ፈጥሯል።
የሥራ ዕድል ፈጠራና የቴክኖሎጂ ሽግግር፡ በፓርኩ ውስጥ የሚከናወኑ አምራች ኢንዱስትሪዎች ለአካባቢው ወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል ከ መፍጠራቸው ባሻገር የቴክኖሎጂና የክህሎት ሽግግርን እያፋጠኑ ይገኛሉ።
የአቅርቦት ሰንሰለትን ማረጋጋት፡ የሀገር ውስጥ ገበያን አስተማማኝና ጥራት ባላቸው ምርቶች በማቅረብ የሸቀጦችን ዋጋ ማረጋጋትና የገበያ ክፍተቶችን መሙላት ተችሏል።
"ተክተን እናመርታለን፤ ሀገርን እናበለጽጋለን!" በሚል መሪ ቃል የሚንቀሳቀሰው ገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ፣ የኢንዱስትሪ መሠረቱን በማጠናከር የሀገር ውስጥ አምራቾች የልማቱ ዋና ተፎካካሪ እንዲሆኑ እያደረገ ይገኛል::
በመሆኑም የሀገር ውስጥ ምርትን በመደገፍ፣ በመጠቀምና በማበረታታት የነገዋን የበለፀገችና ራስዋን የቻለች ኢትዮጵያ አብሮ መገንባት የሁሉም ዜጋ፣ የባለሀብቱና የባለድርሻ አካላት ሀገራዊ ኃላፊነት መሆኑ ተመላክቷል።
ምንጭ: አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (AMN)
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
+2
የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ እየተገመገመ ነው
=========================
ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት፣ ክልልና ከተማ አስተዳደር የኢንዱሰትሪ ቢሮ ስራ ኃላፊዎች ጋር የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም፣ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት እያካሄደ ነው፡፡
በውይይቱ በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ወቅት የታዩ ጠንካራና መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮችን በጥልቀት በመገምገም ለ2019 በጀት ዓመት አዲስ የተቀመጡ ግቦችና የትኩረት መስኮችን በመለየት የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ መግባባት ላይ በመድረስ የስራ አቅጣጫዎች የሚሰጡ ይሆናል፡፡
በ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም የተሻላ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ተጠሪ ተቋማት፣ ክልልና ከተማ አስተዳደር የኢንዱስትሪ ቢሮዎች እውቅናና ሽልማት መርሐ ግብር ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://youtu.be/MYOS1lvE88g?si=ZudYfDenzsJOPqRL
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://youtu.be/UHF0nqh_lhU?si=yycHZrGx1crnjif5
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
https://youtu.be/4_yI1xBQBMk
#የአምራች_ስነ_ልቦና (ክፍል አስራ_ስምንት) - #ጭቶ_ቡና
========////=======
የ“ጭቶ ቡና” የስኬት ጉዞ
በውጭ ሀገር የነበራቸውን ኑሮ በመተው ወደ ሀገራቸው የተመለሱት አቶ ስምኦን ሰርፁ፣ ጥሬ ቡናን ዝም ብሎ ከመላክ ይልቅ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እሴት በመጨመር (Value Addition) የኢትዮጵያን ቡና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ “ጭቶ ቡና” የተሰኘ ኢንተርፕራይዝ መሥርተዋል።
ከ4 ዓመታት በፊት በኪራይ ቤትና በ5 ሰራተኞች ስራ የጀመረው ይህ ኢንተርፕራይዝ፣ በአሁኑ ወቅት በሸገር ከተማ ለገጣፎ አካባቢ ተስፋፍቶ ከ40 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ በቅርቡም በትልቋ የዓለም የገበያ መዳረሻ ቻይና አዲስ ቅርንጫፍ መክፈት ችሏል።
አቶ ስምኦን “ችግር የማደግ ምልክት ነው” በሚል የዕድገት አስተሳሰብ ፈተናዎችን አልፈው የቡናውን ተፈጥሯዊ ጣዕምና መዓዛ የሚጠብቁ ዘመናዊ ማሽኖችን በመጠቀም ምርታቸውን ለዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ አድርገዋል።
በቀጣይም ምርታቸውን በማሳደግ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰሩ የገለፁ ሲሆን፣ የጭቶ ቡና ጉዞ ለተመላሽ ዳያስፖራዎችና ለአገር ውስጥ ስራ ፈጣሪዎች ትልቅ ማሳያ ሆኗል።
ሙሉ መረጃውን በቅርብ ቀናት ይጠብቁን!
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
+9
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና ከአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በጋምቤላ ከተማ የችግኝ ተከላ፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እና የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀምሯል። በመርሃ ግብሩ የተቋማቱ እና የጋምቤላ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ችግኝ የተከሉ ሲሆን፣ ለ1 ሺህ 500 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት ግንባታንም በይፋ አስጀምረዋል።
+9
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት በጋምቤላ ከተማ የችግኝ ተከላ፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እና የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀመሩ
EED ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም (ጋምቤላ)
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማቱ- ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እና ከአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በጋምቤላ ከተማ የችግኝ ተከላ፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እና የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሄዱ።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እና የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት እንዲሁም የጋምቤላ ክልልና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተቋማቱና የአስተዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተው ችግኝ የተከሉ ሲሆን፣ ለ1 ሺህ 500 ተማሪዎች የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አበርክተዋል። በተጨማሪም ለአቅመ ደካሞች የሚገነቡ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ በይፋ ተጀምሯል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት አመራሮች እንደገለጹት፣ ተቋማቱ አምራች ኢንዱስትሪውን ከመደገፍና ኢኮኖሚያዊ እድገትን ከማፋጠን ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን የመወጣት እና ህብረተሰቡን የማገልገል ተግባራቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ።
#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት
ለተጨማሪ መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ፡
https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
