cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞ @orthodox1 ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye ማናገር ይችላሉ 🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹 Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝ @orthodox1

Ko'proq ko'rsatish
Advertising posts
37 875Obunachilar
-1324 soatlar
-1097 kunlar
-45630 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Обуначиларнинг ўсиш даражаси

Ma'lumot yuklanmoqda...

የሆሣዕና ዝማሬ በዘማሪት ህጻን ሳሮን የሆሣዕና ዝማሬ በዘማሪት ህጻን ሳሮን https://youtu.be/ffxoLx6o23g?si=s8_fd3DwK9rEcNu1 https://youtu.be/ffxoLx6o23g?si=s8_fd3DwK9rEcNu1
Hammasini ko'rsatish...
የሆሣዕና ዝማሬ በዘማሪት ህጻን ሳሮን // Ethiopian orthodox tewahedo hosaena song

. መፃጉዕ እና ኒቆዲሞስ 【 ዮሐ ፫ / ዮሐ ፭ 】 ✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥ የዐቢይ ጾም ሳምንታት ከ፶ ሚሊየን ሕዝብ በላይ ባላቸው ተዋህዶን በሚያምኑ በጽባሓውያኑ ኦርቶዶክሳውያት አብያተ ክርስቲያን ዘንድ [ Eastern Christian churches adhering to Miaphysite Christology; Oriental Orthodox Churches】እኛ ከዘወረደ እስከ ሆሳዕና እንደምንዘክረው ከሆሳዕና በቀር በስያሜ የተለያየት መታሰቢያ ተሠጥቶት ይዘከራል በብዙዎቹ ① ከብካበ ቃና ☞ ② ለምጻሙን ማዳኑ ☞ ③ ሽባውን ማዳኑ ☞ ④የከነናዊቷ ሴት እምነት ልጇን ማዳኑ ☞ ⑤ እኩለ ጾም/ በዓለ መስቀል ☞ ⑥ ደጉ ሳምራዊና ጀርባዋ የጎበጠች ሴት ☞ ⑦ ዘእውሩ ተወልደ ☞ ⑧ ሆሳእና ይታሰቡበታል። በዚህ ውሥጥ በየሳምንታቱ የእነዚህ ታሪኮች መጻፍና መዘከር ምክንያቱ ታሪክ ‘አዋቆች’ ብቻ እንድንሆን አይደለም። ለምሳሌ በቅዱስ መጽሐፍ የቅዱሳን እና የርኩሳን፣ የቡሩካንና የርጉማን ፣ የጻድቃንና የኃጥዓን ታሪክ ሁሉ ተዘግቧል ምክንያቱ ደግሞ በሁለት መንገድ መረዳት ይቻላል። እንድንታነጽና እንድንገሠጽ ፩) የመልካም ሰዎች ታሪክ ⇨ ለጽናት በተስፋ ለመጽናናት “በመጽናትና መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፎአልና።” 【ሮሜ ፲፭፥፬】 ፪) የአመጸኞች ታሪክ ⇨ ለተግሳጽ “ይህም ሁሉ እንደ ምሳሌ ሆነባቸው፥ እኛንም የዘመናት መጨረሻ የደረሰብንን ሊገሥጸን ተጻፈ።” 【፩ኛ ቆሮ ፲፥፲፩】 በዚሁ መንገድ ሊቃውንትና መና**ፍቃን ፣ የካዱና የጸኑ ፣ በጎ ሠሪዎችና ክፉ አድራጊዎች … ግለሰቦችም ታሪካቸው ተዘግቦ ተነግሯል። ዐላማው እንደቀድሞው ለሁለት ጥቅም ነው ፤ ፩) መልካም አድራጊዎች እንድናውቃቸው ምሳሌና አብነት እንድናደርጋቸው ☞ "ወአእምርዎሙ ለእለ ከመዝ ⇨ እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን እወቁአቸው” 【፩ኛ ቆሮ ፲፮፥፲፰】 ፪) ክፉ አድራጊዎችን ግን እንድናውቅባቸው ለመጠንቀቅ ☞ "ተዓቀቡ አንትሙሂ ወዑቅዎሙ ለከለባት ወዑቁዎሙ ለገበርተ እኪት ⇨ ከውሾች ተጠበቁ፥ ከክፉዎችም ሠራተኞች ተጠበቁ፥ ።” 【ፊል 3፥2】 መፃጉዕና ኒቆዲሞስም በ፫ ክፍል ታሪክ የዚህ መንገድ አስተማሪዎች እንዲሆኑ በዐቢይ ጾም ሰንበታት የሚታሰቡ ግለሰቦች ናቸው ✧ ክፍል 【፩】 በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፫ እና ምዕራፍ ፭ ኒቆዲሞስ ☞ ወሐሎ አሐዱ ብእሲ ዘስሙ ኒቆዲሞስ ወመልአኮሙ ለአይሁድ ወውእቱ መጽአ ኀበ እግዚእ ኢየሱስ ቀዲሞ ሌሊቱ መፃጉዕ ☞ ወሐሎ አሐዱ ብእሲ ዘሠላሳ ወሰመንቱ ክረምቱ እምዘደወየ ወኪያሁ ርእዮ እግዚእ እግዚእ ኢየሱስ ይሰክብ ውስተ ዐራቱ ልዩነት ኒቆዲሞስ ወደ ጌታው የመጣ መፃጉዕ ጌታው ወደ እርሱ የመጣ ኒቆዲሞስ ቀድሞ በሌሊት የሚገሰግሰው ከጌታው እግር ስር ሊማር (ለትምህርት) መፃጉዕ ቀድሞ ወደ መጠመቀቂያው ውኃ ለመውረድ ደጅ የሚጠና ምኞቱ ሊማር (ለምሕረት) ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት ፣ ባለ ሥልጣንና ባለሀብት መፃጉዕ ምሁረ ደዌ ፣ ሰው የሌለው ፣ ድኃ (ንብረቱ አልጋው ብቻ) ኒቆዲሞስ ስሙ የተጠቀሰ መፃጉዕ ግን በህመሙ ደረጃ መገለጫው እንጂ በስም ያልተጠቀሰ 【የመፃጉን ስም አልተጠቀሰም መፃጉዕነት የደዌ መጽናት እንጂ ስም አለመሆኑን ልብ ይሏል ፤ ልክ እንደ አልአዛርና ነዌ (ባለጠጋው) 】 ስሙ አለመጠቀሱ ባለመታመኑ ነው፤ የጻድቃን መንገድና የታመኑ ሰዎች ስም መታወቁ በመንግሥቱ እውቅና እንዳላቸው ያስገነዝባልና “ኄር እግዚአብሔር ለእለ ይትኤገስዎ በዕለተ ምንዳቤሆሙ ወያአምሮሙ ለእለ ይፈርህዎ ⇨ እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል።”።【 ናሆም 1፥7】 “እስመ እግዚአብሔር የአምር ፍኖቶሙ ለጻድቃን ወፍኖቶሙሰ ለኃጥኣን ትጠፍእ ⇨ እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና፥ የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።” 【 መዝሙር 1፥6】 ✧ ክፍል ፪ በአይሁድ ክስና ውንጀላ ውስጥ ☞ መፃጉዕ ወደ አይሁድ ሔዶ ክርስቶስን ከሰሰ ☞ ለክርስቶስ መገደል ምክንያትም ሆነ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፭ ከቁጥር ፻፫ ጀምሮ እንደተነገው «ዳሩ ግን በዚያ ስፍራ ሕዝብ ስለ ነበሩ ኢየሱስ ፈቀቅ ብሎ ነበርና የተፈወሰው ሰው ማን እንደ ሆነ አላወቀም። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ አለው። ሰውዬው ሄዶ ያዳነው ኢየሱስ እንደ ሆነ ለአይሁድ ነገረ። ስለዚህም በሰንበት ይህን ስላደረገ አይሁድ ኢየሱስን ያሳድዱት ነበር ሊገድሉትም ይፈልጉ ነበር። ☞ ኒቆዲሞስ ግን አይሁድ ወደእርሱ በመጡ ጊዜ ጥብቅና የቆመና እንዳይያዝ የሞገተ ሆኑ ተገኝቷል በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፯ ከቁጥር ፶ ጀምሮ « ከእነርሱ አንዱ በሌሊት ቀድሞ ወደ እርሱ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ፦ ⁵¹ ሕጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን? አላቸው።» ✧ ክፍል ፫ መጻጉዕ ፦ ጌታውን በዕለተ ዓርብ በጥፊ መትቶ የመታበት እጁ ሰሎ ቀርቶ ከደዌው የታረቀ ቀድሞ እንዲህ ሲል አስጠንቅቆት ነበር "ናሁኬ ሐየውከ ዑቅ ኢትአብስ ዳግመ እንከ ከመ ዘየአኪ ኢይርከብከ ⇨ ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ አለው።” 【ዮሐ ፭፥፲፬ 】 እርሱ ግን "በዚያ ቆሞ የነበረው ከሎሌዎች አንዱ፦ ለሊቀ ካህናቱ እንዲህ ትመልሳለህን? ብሎ ኢየሱስን በጥፊ መታው።” 【ዮሐ ፲፰፥፳፪】 ኒቆዲሞስ ፦ በከበረና ዋጋው ውድ የሆነ ሽቱ ገዝቶ ለአምላኩ የመግነዝ ሥርዓት ፈጸመ፤ ከስውሩ ደቀመዝሙር ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ሆኖ አምላኩን ሥጋ ከመቃብር አውርዶ አካሉን በአዲስ በፍታ ሸፍኖ ወደ አዲስ መቃብር ያኖረ 【 ዮሐ ፲፱፥፴፰ እስከ ፵】 «ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ። ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ። የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።» ኒቆዲሞስ በልሳነ ጽርእ ኒኮዴይሞስ "Νικόδημος" ይባላል በትርጉሙ ኒኮስ (νῖκος) እና ዴይሞስ (δῆμος) አገናኝቶ መዋዔ እም ሕዝቡ ይለዋል ከሕዝቡ ድል ያደረገ "victorious among his people" ይለዋል ቤተክርስቲያናችን ሦስት ጊዜ ትዘክረዋለች ፩) የዕረፍቱን መታሰቢያ ነሐሴ ፩ ቀን ሠይማ ፪) በዐቢይ ጾም ደግሞ የ፯ኛ ሳምንት መጠሪያን ሠጥታ ፫) ለሁልጊዜው ደግሞ የቤተመቅደሱን አጥር ቅጥር እንደመግነዙ በመቁጠር የመግቢያ በሩን አዕማድ ለዮሴፍና ኒቆዲሞስ መታሰቢያ እንዲሆናቸው በማውሳት የቅዱሱን የማታ ሰው የኒቆዲሞስን በረከት በሁላችን ላይ ያሳድርብን! መልእክቱን በድምጽና በምስል ለመከታተልና ለመስማት በተከታዩን ሊንክ ታግዘው ማግኘት ይችላሉ https://youtu.be/jkIgQ87W4Zw?si=LRACYvXhUAYJDQkp
Hammasini ko'rsatish...
MK TV || ዐውደ ስብከት || መፃጕዕ እና ኒቆዲሞስ || ዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ

Subscribe and share

https://www.youtube.com/user/EOTCMK?s......

https://www.youtube.com/user/EOTCMK?s......

#MKTV #MahibereKidusan #EOTCMK

👍 8 2👏 1
ቸሩ ሆይ ናና // የመሠንቆ ዝማሬ በ ዲያቆን ድርሻዬ አከለ
Hammasini ko'rsatish...
https://youtu.be/6EYyCyH4azs?si=KjEQF1NBsbUGtXnC ቸሩ ሆይ ናና // የመሠንቆ ዝማሬ በ ዲያቆን ድርሻዬ አከለ
Hammasini ko'rsatish...
ቸሩ ሆይ ናና ❤️ የመሰንቆ ዝማሬ በ ዲያቆን ድርሻዬ አከለ // ኅብር የበገና ምሽት

👍 4🙏 1
#ፈራሁ ቀኑ ከረፈደ ከመሸብኝ መጣሁ ደጃፍህ ላይ ቆምኩኝ እንዳልገባ ፈራሁ በደሌን ሳትመዝን ግቢ ብትለኝም ኃጢያቴ ከበደኝ አላራመደኝም የሰው ዕድሜው እኮ አጭር ነው ጥቂት ነው እንዴት ነው ሳላውቅህ ዘመኔ ያለቀው? ጉብዝናዬን ዓለም ስቃ ተጫውታበት እንዴት ብዬ ልርገጥ ደጅህን በድፍረት? ፈራሁ ልግባ ወይ አልግባ እንዴት ይመዘናል የአንተ ደም በእኔ እንባ ? እኔ ፈራሁ እንጂ አንተ እኮ አታስፈራም መምጣቴ ነው ደስታህ ፍቅርህ አይታማም ሽምቅቅ አለች ነፍሴ መስቀልህን ሳየው በደሌን አሰብኩት ደምህን እያየሁ ፈራሁ ልግባ ወይ አልግባ እንዴት ይመዘናል የአንተ ደም በእኔ እንባ ? በንጽህናህ ፊት እንዴት እቆማለሁ እንደ መላዕክቱ በምን እጋረዳለሁ ራሴን መሸፈኛ ክንፍ የለኝም እኔ ይታያል ኃጢያቴ የበደል ዕርቃኔ ፈራሁ ልግባ ወይ አልግባ እንዴት ይመዘናል የአንተ ደም በእኔ እንባ ? ጠዋት እና ማታ ለመጣው አንድ ነህ አምሽቶ ለገባም እኩል ትከፍላለህ አብርሃም ወይስሐቅ በድንኳንህ ቢያድሩም በአንተ መንግሥት ግን ከወንበዴ አይቀድሙም ፈራሁ ልግባ ወይ አልግባ እንዴት ይመዘናል የአንተ ደም በእኔ እንባ ? https://youtu.be/yZRhhLT74rY?si=TplnxdckbmIF7GG2
Hammasini ko'rsatish...
ፈራሁ | Ferahu | ዘማሪት በዛወርቅ አስፋው | Bezawork Asfaw | አዲስ መዝሙር New Orthodox Mezmur | 2024

"ፈራሁ | Ferahu | ዘማሪት በዛወርቅ አስፋው | Bezawork Asfaw | አዲስ መዝሙር New Orthodox Mezmur | 2024 is licensed under a Creative Commons Attribution Share Alike 4.0 International License. Based on a work at

https://www.youtube.com/watch?v=KdOwdsGMAfE."

Ethiopian Orthodox Tewahedo Song " ፈራሁ | Ferahu | ዘማሪት በዛወርቅ አስፋው | Bezawork Asfaw | አዲስ መዝሙር New Orthodox Mezmur | 2024 " New Ethiopian Orthodox Tewahedo Mezmur 2023 © Wreb Tube is the only Channel that has exclusive rights for all Lyrics produced by Zemarit Bezawork Asfaw #ይህ_ቪዲዮ_በFacebook_ኮፒ_ራይት_የተመዘገበ_ስለሆነ_አካውንትዎ_እንዳይዘጋ_በFacebook_አይልቀቁት:: " ፈራሁ | Ferahu | ዘማሪት በዛወርቅ አስፋው | Bezawork Asfaw | አዲስ መዝሙር New Orthodox Mezmur | 2024 " New Ethiopian Orthodox Tewahedo Mezmur 2023

👍 33🙏 3
ሸክም የሆነብንን ኃጢዓት አራግፈንና በደላችንን ከላያችን በማስወገድ ራስን አንጽቶ  ልብን አቅንቶ  ሕይወትን መምራት በዙፋኑ ቀኝ ሳያፍሩ ወደመክበር  ያደርሳል። “እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”【ዕብ ፲፪፥፩-፪】 በማያሳፍር ራቁትነት በፊቱ ለመክበር ያብቃን የአቡነ አዳም የእነ ሔዋን በረከታቸው በሁላችን ይደር! ትምህርቱን  ከታች ባለው "ሊንክ በድምጽ ማግኘት ይችላሉ    https://youtu.be/s0ipUnYfRkA?si=pDknHqI_wLvUBx_P
Hammasini ko'rsatish...
ዲ ን ዶ ር ቴዎድሮስ በለጠ የማያሳፍር ዕራቁትነት ዘፍ 2፥25

✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ / @mahiberetsion እግዚአብሔር ያክብርልን

👍 5 2
╔​✞═•┉✽✥⛪✥✽┉•═✞╗ ❀.  #የማያሳፍር_ራቁትነት . ╚✞═•┉✽✥⛪✥✽┉•═✞╝          ትናንት ሚያዝያ ፬ የመፈጠራቸው ነገ ሚያዝያ ፭ ደግሞ የዕረፍታቸውን መታሰቢያ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የምትዘክርላቸው አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን በረከታቸው ይደርብርብን። ★ "ሀለዉ አዳም ወብእሲቱ (ሔዋን) እራቃኒሆሙ ወኢይትኃፈሩ ☞ አዳምና ሚስቱ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ፥ አይተፋፈሩም ነበር።"  【ዘፍ ፪ ፥ ፳፭】 ሁለት ዐይነት እርቃን አለ  የሚያሳፍር እና የማያሳፍር  የማያሳፍረው ራቁትነት ደግሞ የተፈቀደ እና ያለተፈቀደ ሊሆን ይችላል ዛሬ ላይ ትውልዱ ባልተፈቀደ መንገድ መራቆቱን ሳያፍርበት እንደፋሽንም እንደ ክብርም ይቆጥረዋል በቀደመው ታሪክ የቃየል ልጆች ባልተፈቀደ መራቆት አምላካቸውን ሲያሳዝኑ እንደታዩ ቅዱስ ቀሌምንጦስ ገልጧል "ርእዩ አዋልዲሁ ለቃየል በዘይሴኒ ሥነ ራእይ እንዘ የሐውራ ዕራቆን ዘእንበለ ሐፍረት  ☞ የቃየን ሴቶች ልጆች ተውበው እርቃናቸውን በመሆን ሳያፍሩ ሲንቀሳቀሱ እዩዋቸው" 【ቀሌ. ፫፥፵፱】 ታዲያ እንዲህ ባለው መንገድ ነውርን እንደ ክብር መራቆትንም  እንደ መሰልጠን ገላ መግለጥ  እንደፋሽን እያዩ የሚኖሩ መጨረሻቸው ኩነኔ እንደሆነ መጽሐፋችን ይመሰክራል  “መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው።” 【ፊል ፫፥፲፱ 】        ለሰው ልጅ አካሉን ገልጦና ሰውነቱን አራቁቶ ለመታየት የታወቀ (በቂ) ምክንያት ያስፈልጋል፤ ሠለስቱ ምዕት ለመታከም «የሚተኮስ» «የሚታገም» አካል ቢኖር አልያም ከጸበል ሊነከሩና ሊታጠቡ እንጂ በሌላውስ መንገድ በማንም ፊት እርቃን መታየት ክልክል ነው ብለዋል። "ወዓዲ ተዐቀብ ከመ ኢትትዐረቅ እምልብስከ ቅድመ መኑሂ ዘእንበለ ዳዕሙ ሶበ ይረክበከ ምክንያት ለተዐርቆ።  ☞ ዳግመኛም በማንም ፊት ከልብስህ ራቁትህን እንዳትሆን ተጠበቅ፤ የምትራቆትበት ምክንያት ቢያገኝህ ነው እንጂ" 【 ሃይ አበው ፳፥፲፪ 】 መራቆት አለመዘጋጀት እፍረት ማሳየት የመዘናጋት በበጎ ምግባር ሳይተጉ የመኖር መገለጫ ነው።   “እነሆ፥ እንደ ሌባ ሆኜ እመጣለሁ፤ ራቁቱን እንዳይሄድ እፍረቱንም እንዳያዩ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ብፁዕ ነው።” 【ራእ  ፲፮፥፲፭】         አካልን ራቁቶ  መታየት ቀርቶ  የተራቆተ አካልም ማየት ራሱ   ሲያስነቅፍ ፣ ሲያስቀጣና ሲያስረግም እናያለን በዘፍጥረት መጽሐፍ ምዕራፍ ፱ እንደተገለጸው  በኖኅ ልጅ በካም  ላይ የደረሰው የዚህ ማሳያ ነው " ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይንም ተከለ። ከወይን ጠጁም ጠጣና ሰከረ፤ በድንኳኑም ውስጥ ዕራቁቱን ሆነ። የከነዓን አባት ካምም የአባቱን ዕራቁትነት አየ፥ ወደ ውጭም ወጥቶ ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው። ሴምና ያፌትም ሸማ ወስደው በጫንቃቸው ላይ አደረጉ፥ የኋሊትም ሄደው የአባታቸውን ዕራቁትነት አለበሱ፤ ፊታቸውም ወደ ኋላ ነበረ፥ የአባታቸውንም ዕራቁትነት አላዩም። ኖኅም ከወይን ጠጁ ስካር ነቃ፥ ታናሹ ልጁ ያደረገበትንም አወቀ። እንዲህም አለ፦ ከነዓን ርጉም ይሁን፤ ለወንድሞቹም የባሪያዎች ባሪያ ይሁን። እንዲህም አለ፦ የሴም አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ፥ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። እግዚአብሔርም ያፌትን ያስፋ፥ በሴምም ድንኳን ይደር፤ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። " 【ዘፍ ፱፥ ፳ - ፳፯】 እንግዲህ የተራቆተን ማየት በዚህ መጠን የሚያስነቅፍ ከሆነ ተራቁቶ የመታየት ቅጣቱ የከፋ ስለመሆኑ አያጠራጥርም መራቆት የዲያቢሎስ የክብር ልጅ መሆን ነውና ፤ ሰይጣን ማለት በትርጉሙ እሩቅ እም ስብሐተ እግዚአብሔር  【ከእግዚአብሔር ክብር የተራቆተ】ማለት ነውና። የተፈቀደ የማያሳፍርም  ዕርቃን የተባለውና በጥንተ ተፈጥሮ በአዳምና በሴቲቱ ኑሮ የተገለጠው የትኛው ራቁትነት ነው? ① ራቁትነታቸው ከዚህ ዓለም ልብስ ነው አለማፈራቸው ብርሃን ለብሰው ስለነበር ነው ዓለማችን የሚያለብሰን ምድራዊና ቁሳዊ ጊዜአዊና ኃላፊ ትጥቅ ነው መንፈሳዊ ትጥቃችን  ግን ኅልፈትና ውላጤ ከሌለው ሰማያዊ  አባታችን የምንቀበለው ነውና  “የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ።”  【ኤፌ ፮፥፲፩】 “እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ፤ … በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት ” 【ቆላ ፫፥፲፪- ፲፬】 የዓለሙ ልብስ ንፍገት ጭካኔ ቅሚያ ትዕቢት ብልጣብልጥነት ችኩልነትና ጸብእን ነው። ይህን ለብሰው የሚዋጉንን  ሥጋውያኑን በሥጋ ጦር ድል መንሳት እንዴት ይቻለናል?  የሳውልን የጦር ዕቃ የታጠቀ ካባ የለበሰና በአመጽ ወደተመላው እግዚአብሔርን ወደተገዳደረው ጎልያድ  በሥጋዊ መሳርያ ውጣ የተባለው  ብላቴናው ዳዊት መታመኛ ትምክህቱ መከታ ጉልበቱ እግዚአብሔር ስለበር በበትርና በኮሮጆው ጠጠር ዘምቶ  አመጸኛውን ሰልፈኛ ሰው ድል ነስቶታል።  “ዳዊትም ሰይፉን በልብሱ ላይ ታጠቀ፥ ገናም አልፈተነውምና መሄድ ሞከረ። ዳዊትም ሳኦልን፦ አልፈተንሁትምና እንዲህ ብዬ መሄድ አልችልም አለው። ዳዊትም አወለቀ።” 【፩ኛ ሳሙ. ፲፯፥ ፴፱】 ② አእምሮ ጠባያቸው ያላደፈ በተፈጥሮ እንደ ሕፃን  ስለነበሩ በዕርቃናቸው አይተፋፈሩም ሕጻናት በንጽሕና እንደ መላእክቱ ናቸው የእነርሱ አእምሮ ጠባይ ማደፍ ስላላገኘው ሊቁም «ንጽሖሙ ለሕፃናት በሥጋሆሙ ወነፍሶሙኒ ዘእንበለ ሕማም» ይላል። በዘመነ ሥጋዌው ክርስቶስ አምላካችንም እንደ ሕፃናት መሆን ለክብረ መንግሥቱ እንደሚያበቃ ነግሮናል “ እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” 【ማቴ ፲፰፥፫】 መልሶም እንደነርሱ ላሉቱ ስለምትሠጥነና እነርሱኑ ለመሰሉት ስለምትገባዋ ዘልዓለማዊ ርስት ይህን ደግሟል “ነገር ግን ኢየሱስ፦ ሕፃናትን ተዉአቸው፥ ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉ ናትና አለ፤”   【ማቴ ፲፱፥፲፬】  ያለቂም ያለበቀል የሚኖሩ ክፋትንና ተንኮልን አልመው አስበው ሌላው ይጎዳበት ብለው የማይፈጽሙ እንደወረቀት የሠጧቸውን የሚቀበሉ እንደውኃም ቅርጻቸው ያረፉበትን ሥፍራ የሚመስሉ ልጆች ሕጻናትን መስሎ መኖር የሚማሩትን መያዝ በበጎ አርያነት የሚመሩትን መምሰል በእጅጉ ይገባል ፤ “ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”【፩ኛ ጴጥ ፪፥፪-፫】 እንዲህ ያለው የሕጻናት ንጹሕ አይምሮ መያዝ አያሳፍርም። ③ ከልብሰ ኃጢዓት  ተራቁተው ኃፍረተ ነፍስ ሳይኖርባቸው ይኖሩ ነበር ሰው ኃጢዓትን ለብሶ በደል ደርቦ ከመኖር በንሰሐ ቢራቆት ተኮንና የምታፍር ነፍስ የለችውም፤  ይልቁንም የልብ ንጽሕና ማጣት የሕሊና ሞት እንደሚያመጣበት አውቆ በኃጢዓቱ ምክንያት ያገኘውን ቁስለት የልቡናው ሰንኮፍ በንሰሐ ከከከበረች ነፍሱ ቢያርቅ መንገዱን በጥንቃቄ ቢመራና በፍርሐትና በመንቀጥቀጥ ለአምላኩ ቢገዛ በግራ ከሚቆምና ተኮንነው ከሚያፍሩ በመለየት መክበር ይቻለዋል። “እናንተ ዓለመኞች ሴቶች ሆይ፥ ተጠንቀቁ፤ ተማምናችሁም የምትቀመጡ ሆይ፥ ተንቀጥቀጡ፤ ልብሳችሁን አውልቁ፥ ዕራቁታችሁን ሁኑ፥ ወገባችሁንም በማቅ ታጠቁ።”   【ኢሳ ፴፪፥፲፩】
Hammasini ko'rsatish...
ዲ ን ዶ ር ቴዎድሮስ በለጠ የማያሳፍር ዕራቁትነት ዘፍ 2፥25

✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ / @mahiberetsion እግዚአብሔር ያክብርልን

👍 7 4🙏 1
“እናንተ ዓለመኞች ሴቶች ሆይ፥ ተጠንቀቁ፤ ተማምናችሁም የምትቀመጡ ሆይ፥ ተንቀጥቀጡ፤ ልብሳችሁን አውልቁ፥ ዕራቁታችሁን ሁኑ፥ ወገባችሁንም በማቅ ታጠቁ።”   【ኢሳ ፴፪፥፲፩】 ሸክም የሆነብንን ኃጢዓት አራግፈንና በደላችንን ከላያችን በማስወገድ ራስን አንጽቶ  ልብን አቅንቶ  ሕይወትን መምራት በዙፋኑ ቀኝ ሳያፍሩ ወደመክበር  ያደርሳል። “እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”【ዕብ ፲፪፥፩-፪】 በማያሳፍር ራቁትነት በፊቱ ለመክበር ያብቃን የአቡነ አዳም የእነ ሔዋን በረከታቸው በሁላችን ይደር! ትምህርቱን  ከታች ባለው "ሊንክ በድምጽ ማግኘት ይችላሉ    https://youtu.be/s0ipUnYfRkA?si=pDknHqI_wLvUBx_P
Hammasini ko'rsatish...
ዲ ን ዶ ር ቴዎድሮስ በለጠ የማያሳፍር ዕራቁትነት ዘፍ 2፥25

✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ / @mahiberetsion እግዚአብሔር ያክብርልን

𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος): ╔​✞═•┉✽✥⛪✥✽┉•═✞╗ ❀.  #የማያሳፍር_ራቁትነት . ╚✞═•┉✽✥⛪✥✽┉•═✞╝          ትናንት ሚያዝያ ፬ የመፈጠራቸው ነገ ሚያዝያ ፭ ደግሞ የዕረፍታቸውን መታሰቢያ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የምትዘክርላቸው አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን በረከታቸው ይደርብርብን። ★ "ሀለዉ አዳም ወብእሲቱ (ሔዋን) እራቃኒሆሙ ወኢይትኃፈሩ ☞ አዳምና ሚስቱ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ፥ አይተፋፈሩም ነበር።"  【ዘፍ ፪ ፥ ፳፭】 ሁለት ዐይነት እርቃን አለ  የሚያሳፍር እና የማያሳፍር  የማያሳፍረው ራቁትነት ደግሞ የተፈቀደ እና ያለተፈቀደ ሊሆን ይችላል ዛሬ ላይ ትውልዱ ባልተፈቀደ መንገድ መራቆቱን ሳያፍርበት እንደፋሽንም እንደ ክብርም ይቆጥረዋል በቀደመው ታሪክ የቃየል ልጆች ባልተፈቀደ መራቆት አምላካቸውን ሲያሳዝኑ እንደታዩ ቅዱስ ቀሌምንጦስ ገልጧል "ርእዩ አዋልዲሁ ለቃየል በዘይሴኒ ሥነ ራእይ እንዘ የሐውራ ዕራቆን ዘእንበለ ሐፍረት  ☞ የቃየን ሴቶች ልጆች ተውበው እርቃናቸውን በመሆን ሳያፍሩ ሲንቀሳቀሱ እዩዋቸው" 【ቀሌ. ፫፥፵፱】 ታዲያ እንዲህ ባለው መንገድ ነውርን እንደ ክብር መራቆትንም  እንደ መሰልጠን ገላ መግለጥ  እንደፋሽን እያዩ የሚኖሩ መጨረሻቸው ኩነኔ እንደሆነ መጽሐፋችን ይመሰክራል  “መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው።” 【ፊል ፫፥፲፱ 】        ለሰው ልጅ አካሉን ገልጦና ሰውነቱን አራቁቶ ለመታየት የታወቀ (በቂ) ምክንያት ያስፈልጋል፤ ሠለስቱ ምዕት ለመታከም «የሚተኮስ» «የሚታገም» አካል ቢኖር አልያም ከጸበል ሊነከሩና ሊታጠቡ እንጂ በሌላውስ መንገድ በማንም ፊት እርቃን መታየት ክልክል ነው ብለዋል። "ወዓዲ ተዐቀብ ከመ ኢትትዐረቅ እምልብስከ ቅድመ መኑሂ ዘእንበለ ዳዕሙ ሶበ ይረክበከ ምክንያት ለተዐርቆ።  ☞ ዳግመኛም በማንም ፊት ከልብስህ ራቁትህን እንዳትሆን ተጠበቅ፤ የምትራቆትበት ምክንያት ቢያገኝህ ነው እንጂ" 【 ሃይ አበው ፳፥፲፪ 】 መራቆት አለመዘጋጀት እፍረት ማሳየት የመዘናጋት በበጎ ምግባር ሳይተጉ የመኖር መገለጫ ነው።   “እነሆ፥ እንደ ሌባ ሆኜ እመጣለሁ፤ ራቁቱን እንዳይሄድ እፍረቱንም እንዳያዩ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ብፁዕ ነው።” 【ራእ  ፲፮፥፲፭】         አካልን ራቁቶ  መታየት ቀርቶ  የተራቆተ አካልም ማየት ራሱ   ሲያስነቅፍ ፣ ሲያስቀጣና ሲያስረግም እናያለን በዘፍጥረት መጽሐፍ ምዕራፍ ፱ እንደተገለጸው  በኖኅ ልጅ በካም  ላይ የደረሰው የዚህ ማሳያ ነው " ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይንም ተከለ። ከወይን ጠጁም ጠጣና ሰከረ፤ በድንኳኑም ውስጥ ዕራቁቱን ሆነ። የከነዓን አባት ካምም የአባቱን ዕራቁትነት አየ፥ ወደ ውጭም ወጥቶ ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው። ሴምና ያፌትም ሸማ ወስደው በጫንቃቸው ላይ አደረጉ፥ የኋሊትም ሄደው የአባታቸውን ዕራቁትነት አለበሱ፤ ፊታቸውም ወደ ኋላ ነበረ፥ የአባታቸውንም ዕራቁትነት አላዩም። ኖኅም ከወይን ጠጁ ስካር ነቃ፥ ታናሹ ልጁ ያደረገበትንም አወቀ። እንዲህም አለ፦ ከነዓን ርጉም ይሁን፤ ለወንድሞቹም የባሪያዎች ባሪያ ይሁን። እንዲህም አለ፦ የሴም አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ፥ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። እግዚአብሔርም ያፌትን ያስፋ፥ በሴምም ድንኳን ይደር፤ ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ ይሁን። " 【ዘፍ ፱፥ ፳ - ፳፯】 እንግዲህ የተራቆተን ማየት በዚህ መጠን የሚያስነቅፍ ከሆነ ተራቁቶ የመታየት ቅጣቱ የከፋ ስለመሆኑ አያጠራጥርም መራቆት የዲያቢሎስ የክብር ልጅ መሆን ነውና ፤ ሰይጣን ማለት በትርጉሙ እሩቅ እም ስብሐተ እግዚአብሔር  【ከእግዚአብሔር ክብር የተራቆተ】ማለት ነውና። የተፈቀደ የማያሳፍርም  ዕርቃን የተባለውና በጥንተ ተፈጥሮ በአዳምና በሴቲቱ ኑሮ የተገለጠው የትኛው ራቁትነት ነው? ① ራቁትነታቸው ከዚህ ዓለም ልብስ ነው አለማፈራቸው ብርሃን ለብሰው ስለነበር ነው ዓለማችን የሚያለብሰን ምድራዊና ቁሳዊ ጊዜአዊና ኃላፊ ትጥቅ ነው መንፈሳዊ ትጥቃችን  ግን ኅልፈትና ውላጤ ከሌለው ሰማያዊ  አባታችን የምንቀበለው ነውና  “የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ።”  【ኤፌ ፮፥፲፩】 “እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ፤ … በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት ” 【ቆላ ፫፥፲፪- ፲፬】 የዓለሙ ልብስ ንፍገት ጭካኔ ቅሚያ ትዕቢት ብልጣብልጥነት ችኩልነትና ጸብእን ነው። ይህን ለብሰው የሚዋጉንን  ሥጋውያኑን በሥጋ ጦር ድል መንሳት እንዴት ይቻለናል?  የሳውልን የጦር ዕቃ የታጠቀ ካባ የለበሰና በአመጽ ወደተመላው እግዚአብሔርን ወደተገዳደረው ጎልያድ  በሥጋዊ መሳርያ ውጣ የተባለው  ብላቴናው ዳዊት መታመኛ ትምክህቱ መከታ ጉልበቱ እግዚአብሔር ስለበር በበትርና በኮሮጆው ጠጠር ዘምቶ  አመጸኛውን ሰልፈኛ ሰው ድል ነስቶታል።  “ዳዊትም ሰይፉን በልብሱ ላይ ታጠቀ፥ ገናም አልፈተነውምና መሄድ ሞከረ። ዳዊትም ሳኦልን፦ አልፈተንሁትምና እንዲህ ብዬ መሄድ አልችልም አለው። ዳዊትም አወለቀ።” 【፩ኛ ሳሙ. ፲፯፥ ፴፱】 ② አእምሮ ጠባያቸው ያላደፈ በተፈጥሮ እንደ ሕፃን  ስለነበሩ በዕርቃናቸው አይተፋፈሩም ሕጻናት በንጽሕና እንደ መላእክቱ ናቸው የእነርሱ አእምሮ ጠባይ ማደፍ ስላላገኘው ሊቁም «ንጽሖሙ ለሕፃናት በሥጋሆሙ ወነፍሶሙኒ ዘእንበለ ሕማም» ይላል። በዘመነ ሥጋዌው ክርስቶስ አምላካችንም እንደ ሕፃናት መሆን ለክብረ መንግሥቱ እንደሚያበቃ ነግሮናል “ እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” 【ማቴ ፲፰፥፫】 መልሶም እንደነርሱ ላሉቱ ስለምትሠጥነና እነርሱኑ ለመሰሉት ስለምትገባዋ ዘልዓለማዊ ርስት ይህን ደግሟል “ነገር ግን ኢየሱስ፦ ሕፃናትን ተዉአቸው፥ ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉ ናትና አለ፤”   【ማቴ ፲፱፥፲፬】  ያለቂም ያለበቀል የሚኖሩ ክፋትንና ተንኮልን አልመው አስበው ሌላው ይጎዳበት ብለው የማይፈጽሙ እንደወረቀት የሠጧቸውን የሚቀበሉ እንደውኃም ቅርጻቸው ያረፉበትን ሥፍራ የሚመስሉ ልጆች ሕጻናትን መስሎ መኖር የሚማሩትን መያዝ በበጎ አርያነት የሚመሩትን መምሰል በእጅጉ ይገባል ፤ “ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”【፩ኛ ጴጥ ፪፥፪-፫】 እንዲህ ያለው የሕጻናት ንጹሕ አይምሮ መያዝ አያሳፍርም። ③ ከልብሰ ኃጢዓት  ተራቁተው ኃፍረተ ነፍስ ሳይኖርባቸው ይኖሩ ነበር ሰው ኃጢዓትን ለብሶ በደል ደርቦ ከመኖር በንሰሐ ቢራቆት ተኮንና የምታፍር ነፍስ የለችውም፤  ይልቁንም የልብ ንጽሕና ማጣት የሕሊና ሞት እንደሚያመጣበት አውቆ በኃጢዓቱ ምክንያት ያገኘውን ቁስለት የልቡናው ሰንኮፍ በንሰሐ ከከከበረች ነፍሱ ቢያርቅ መንገዱን በጥንቃቄ ቢመራና በፍርሐትና በመንቀጥቀጥ ለአምላኩ ቢገዛ በግራ ከሚቆምና ተኮንነው ከሚያፍሩ በመለየት መክበር ይቻለዋል።
Hammasini ko'rsatish...
ዲ ን ዶ ር ቴዎድሮስ በለጠ የማያሳፍር ዕራቁትነት ዘፍ 2፥25

✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️አዲሱን የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን:: ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ / @mahiberetsion እግዚአብሔር ያክብርልን

#ያንን_ሰው_ባረገኝ  ፣ #ያቺንም_ሴት_በሆንኩ [፩] 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ~~~~~~~ ምነው እሱን በሆንኩ ያን የቀኝ ወንበዴ ብመስለው ላ’ንድቀን : ባየው መንገዴ ለመስረቅ አይደለም ንብረት ለመቀማት አልያም ለመዝረፍ ሕይወትን ለማጥፋት በዚያ መንገድማ ከሱስ ብበልጥ እንጂ መች ከእርሱ አንስና እኔን ታውቀኝ የለ …  የወንበዴ አለቃ ያ’ጢኣተኞች ዋና ያ … ጸጸት ያዘለ በዚያች የጭንቅ ሠዓት «አስበኝ» እያለ ከመስቀልህ ጥላ ከሥር ስለዋለ ካ’ዳም ቀድሞ ገባ ምሕረት ተቀበለ እኔም እንደ ጥጦስ : ማታዬ እንዲያምር ብትለኝ ምን አለ? … «ከገነት ተጠለል: ዛሬን ከእኔ እደር» 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ~~~~~~~ ደ’ሞ ይህን ተመኘሁ ለንጊኖስን በሆንኩ ያቺን ዕለተ ዓርብ : ቀራንዮ በዋልኩ ለአመጽ አይደለም : ከከአይሁድ ለማበር አልያም ለመውጋት : ያንተን ጎን በጦር በዚያ መንገድማ አንተን ለማሳመም:  ማን እኔን መሰለ ስንቴ እንዳቆሰልኩህ …  ስንቴ እንደወጋሁህ : እኔን ታወቀኝ የለ! ያ …የጲላጦስ ጭፍራ በመስቀል ላይ ሳለህ በሞት በመከራ በጦሩ ቢወጋህ ሳያዝን ሳይራራ  ከቀኝ ጎን አፍስሰህ  ውኃው ከደም ጋራ በፍቅርህ ስታስረው  ዐይኑን ስታበራ ትዕግስትህን ጎትቶት   ባንተ እንደ ተጠራ ምናለ እንደው ’ኔንም … ላንተ ብቻ እንዲያድር : ልቤን ብታበራ 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ~~~~~~~ የበገና መዝሙር ዲ/ን አቤል ተስፋዬ ላንዴ እስከወዲያኛዉ https://youtu.be/GjZf3fPaeDs
Hammasini ko'rsatish...
የበገና መዝሙር ዲ/ን አቤል ተስፋዬ ላንዴ እስከወዲያኛዉ

🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ~~~~~~~~~~~~~~~ ምነው እሱን በሆንኩ ያን የቀኝ ወንበዴ ብመስለው ላ’ንድቀን : ባየው መንገዴ ለመስረቅ አይደለም ንብረት ለመቀማት አልያም ለመዝረፍ ሕይወትን ለማጥፋት በዚያ መንገድማ ከሱስ ብበልጥ እንጂ መች ከእርሱ አንስና እኔን ታውቀኝ የለ …  የወንበዴ አለቃ ያ’ጢኣተኞች ዋና ያ … ጸጸት ያዘለ በዚያች የጭንቅ ሠዓት «አስበኝ» እያለ ከመስቀልህ ጥላ ከሥር ስለዋለ ካ’ዳም ቀድሞ ገባ ምሕረት ተቀበለ እኔም እንደ ጥጦስ : ማታዬ እንዲያምር ብትለኝ ምን አለ? … «ከገነት ተጠለል: ዛሬን ከእኔ እደር» 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ : ዛሬን ከእኔ እደር» ደ’ሞ ይህን ተመኘሁ ለንጊኖስን በሆንኩ ያቺን ዕለተ ዓርብ : ቀራንዮ በዋልኩ ለአመጽ አይደለም : ከከአይሁድ ለማበር አልያም ለመውጋት : ያንተን ጎን በጦር በዚያ መንገድማ አንተን ለማሳመም:  ማን እኔን መሰለ ስንቴ እንዳቆሰልኩህ …  ስንቴ እንደወጋሁህ : እኔን ታወቀኝ የለ! ያ …የጲላጦስ ጭፍራ በመስቀል ላይ ሳለህ በሞት በመከራ በጦሩ ቢወጋህ ሳያዝን ሳይራራ  ከቀኝ ጎን አፍስሰህ  ውኃው ከደም ጋራ በፍቅርህ ስታስረው  ዐይኑን ስታበራ ትዕግስትህን ጎትቶት   ባንተ እንደ ተጠራ ምናለ እንደው ’ኔንም … ላንተ ብቻ እንዲያድር : ልቤን ብታበራ 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ምነው በመሰልኳት የቺን አመንዝራ እንደርሷ ላንድ ቀን : ከፊትህ ብጠራ ለዝሙት አይደለም ነፍሴን ለማሳደፍ አልያም ለመርከስ መቅደስክን ለማጉደፍ በዚያ መንገድማ ነውርን በመሸከም : መች ከእርሷ አንሳለሁ ሕግህን በማፍረስ … እኔን ታውቀኝ የለ : ምን እነግርሃለው ያቺን … ድኩም ዘማ በኃጢአቷ ቆስላ በበደሏ ታ’ማ ዓለም ተሰብስቦ ሕይወቷን ሊቀማ እንዲወግሯት ሳትፈርድ ቸርነትህ ቀድማ መሬቱን ስትጭር ድምጽህ ሳይሰማ ነውሯን እንደቀበርክ በከሳሽ ፊት ቆማ ዳግም አትበድዪ : በፍቅር ሂጂ እንዳልካት እንደው የኔንም ነፍስ … ምናለ መልሰህ: እንዲያ በማረካት 🍁 ላንዴ እስከወዲያኛው ያንን ሰው ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት በሆንኩ ላልወጣ ገብቼ ፡ ላልመለስ በሔድኩ ባ’ረገኝ  ፣ ያቺንም ሴት ✍️๏ በአግናጥዮስ  🖊 ሕዳር ካህናተ ሰማይ ፳፻፲፫ ዓ.ም ተፃፈ ☞ ከምድር ጌጥ ታላቋ ደብረ ሊባኖስ

👍 10 8