uk
Feedback
ወግ ብቻ

ወግ ብቻ

Відкрити в Telegram

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13@wegoch @Words19@seiloch@zefenbicha Creator @leul_mekonnen1

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ወግ ብቻ

Канал ወግ ብቻ (@wegoch) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 17 128 підписників, посідаючи 4 941 місце в категорії Релігія і духовність та 1 957 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 17 128 підписників.

За останніми даними від 10 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -117, а за останні 24 години на 0, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 19.71%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 7.27% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 376 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 246 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 67.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch ✔ @zefenbicha Creator @leul_mekonnen1

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 11 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

17 128
Підписники
Немає даних24 години
+147 днів
-11730 день
Архів дописів
እየመጡ ነው! (አሌክስ አብርሃም) ቦሌና መገናኛ ጫማ ልትገዙ ስትሄዱ ድንገት አግኝታችሁት እንዳትደነግጡ ከወዲሁ ልንገራችሁ። የቻይናው ብሔራዊ የሕክምና ምርቶች አስተዳደር NEO (Neural Electronic Opportunity) ጭንቅላት ውስጥ የሚቀበር ቺፕ ለገበያ እንዲውል በይፋ ፈቅዷል። በዓለም ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የጭንቅላት ውስጥ ቺፕ የንግድ ፈቃድ ተሰጠ ማለት ነው። (እንደፈራነው) ጦቢያዊያን ለአመታት ችብስ 666 ...ስንለው የነበረው ጉዳይ ያው እየመጣ ነው። ነገ እንደጥርስ ማስታወቂያ በተወሳሰቡ የህክምና ቃላት ታጅቦ "አስመጥተናል" የሚል ማስታወቂያ መነገሩ አይቀሬ ነው። ለጊዜው ለአካል ጉዳተኞች ረዳትነት ብቻ ይውላል ብለዋል። ያው አንድ ነገር ከተመረተ በኋላ የቴክኖሎጅውን ፍጥነት በስልክ ማየት ነው። ዝርዝሩ ይቅርብን ግን ኤሎን ማስክ 'Neuralink' ብሎ የጀመረውን ፕሮጀክት ቻይናወቹ ቀድመው ለገበያ አውለውታል።የሆነ ቀን ቱርክ ፀጉር ከቱርክ አንጎል ከቻይና አሰገጥመን ሸገር ላይ እንግሊዝኛውን ልናዶለዱለው እንችላለን። ችግሩ ሀክ ሊደረግም ይችላል የሚል ስጋት መኖሩ ነው። አስበሽዋል እናት የሰርግሽ ቀን የባልሽ አንጎል ሃክ ቢደረግ? ወጩ ጋር ተዳምሮ... @wegoch @wegoch @paappii

የጠቋር ሚስት ጓደኛዬ አዲስ ሙሽራ ነው። ገና ስድስት ወሩ ነው ካገባ። የሆነ እሁድ ጠዋት ልጠይቃቸው ቤታቸው ስሄድ ይሄን ገንገበት ጓደኛዬን ባለቤቱ “ዳዲ” እያለች ስትጠራው ሰማሁ። ተወልዳ እስክታድግ በአንድ የአምበሳ ቆዳ ጫማ እየዳከረ ያሳደጋትን የአባቷን ስም እንደቀልድ ለስድስት ወር ባሏ መስጠቷ ግርም አለኝ። አጎቴ "ሴትና የቀበሌ ቤት የኔ ነው አይባልም" የሚለው እውነት ሳይሆን አይቀርም። ቤታቸው የሄድኩት እሁድ ጠኋት ስለነበር “ቸርች ልንሄድ ስንል መጣህ” ብለው አብረን ካልሄድን አሉኝ። ላለመሄድ ብሞክርም ባለቤቱ ቆጣ ብላ “ኖህ! ወደድራፍት ቤት እንሂድ ቢሉህ መች እምቢ ትላለህ? በል ተነስ” አለችኝ። ይሄ ግምብ ራስ ባሏ ድራፍት እንደምወድ ነግሯታል ማለት ነው። ሰነድ መሻሻጥ ተጀመረ? ብዬ እያመነታሁ አብሬያቸው ሄድኩ። የወሰዱኝ ቸርች አንድ ነብይ የሚያገለግልበት አዲስ የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን ነው። ጓደኛዬ ባለቤቱ በቅርቡ ጌታን እንደተቀበለች ነግሮኛል። ገና ውስጥ ገብተን አረፍ እንዳልን በከፍተኛ ድምፅ እየጮኸች ትፀልይ ጀመር። “ጌታ ሆይ ለዚህ አብሮን ለመጣው፣ ነፍሱ በሃጢአት ለታሰረችው ጎስቋላ ወንድሜ ዛሬ ድረስለት” ስትል ደነገጥኩ። ጭራሽ ስለኔ ነው ፀሎቱ? “ጌታ ሆይ” አለች ጭራሽ ተንጠራርታ እጇን ትከሻዬ ላይ ጭና። ድምጿ እየጨመረ ነው “ጌታ ሆይ፥ ዛሬ ስለዚች ነፍስ እፀልያለሁ ...” አለች። {እቺ ነፍስ የተባልኩት እኔው ነኝ} “ዛሬ እቺ ነፍስ ከስካርና ከሃጢአት ቀምበር እንድትላቀቅ እፀልያለሁ፥ እቺ ነፍስ ዛሬ ከዝሙትና ጌታ ከማይከብርበት የሃጢአት ልምምድ እንድትፈታ እፀልያለሁ” ስትል ቀና ብዬ ምእመኑን አየሁ። እኛ አጠገብ ያሉ ምእመናን ሁሉም ወደኔ እጃቸውን ዘርግተው ይፀልዩልኛል። የት ልግባ? ጭራሽ በሰው ሁሉ ፊት ሰካራም ነው። ያመነዝራል። ትበለኝ? ለምን አንደኛዋን የቲክቶክ ቪዲዮ አትሰራብኝም? ዞር ብዬ ጓደኛዬን ሳየው ሳቁን አፍኖ በቆረጣ ያየኛል። በስጋ ብገለጥበት ደስ ባለኝ። እሱ ነው አብረን በነበርን ግዜ ምንሰራውን ነገር ሁሉ ዘክዝኮ ነግሯት የሰው መሳቂያ ያረገኝ። የተወሰነ ቆይቶ ነብዩ ወደመድረክ ወጥቶ ፀሎት ማድረግ ጀመረ። ቤቱ ፀጥ አለ። አንዳንድ ሰዎች ብቻ በየመሃሉ አሜን ይላሉ። እሱም ትንሽ ከፀለየ በኋላ ... “የጌታ መንፈስ ጅብ ጋላቢ መንፈስ ያሳየኛል” አለ። የዚህ ግዜ የጓደኛዬ ሚስት ዞር ብላ አታየኝም መሰላችሁ? ምናባሽ ላርግሽ? ብላት ደስ ባለኝ። አንተ ነህ ለማለት ፈልጋ ነው? ይሄ የተረገመ ልጅ ጅብም ይጋልባል ብሏት ይሆን እንዴ? ነብዩ ቀጠለ። “በጉባኤ ውስጥ አንድ ሰው ይታየኛል። ቤተሰቦቹ ቃልቻ ነው ሚያመልኩት። እሱንም በልጅነቱ በአጋዘን ደም ያጥቡት ነበር። ዋናው የአጋንንቶች አለቃ ይጠቀምበታል” ሲል በሃዘኔታ እንደገና ዞራ አየችኝ። አረ እቺ ሴትዮ ለምን አትፋታኝም? እያልኩ ፀሎቱን መከታተል ጀመርኩ። ነብዩ ወደኔ አካባቢ ፍጥጥ ብሎ ካየ በኋላ ከመድረክ ወርዶ ቀጥ ብሎ መጣ ..... አሁንስ እኔም ፈራሁ። ስለኔ ነው እንዴ ሚያወራው? የሚል ሃሳብ ውልብ አለብኝ። ምናልባት ነፍስ ሳላውቅ ቤተሰቦቼ እንዳለው በአጋዘን ደም አጥበውኝ ይሆን እንዴ? መቸስ ሰው ማመን ከባድ ነው በዚህ ዘመን ምናምን እያልኩ ሳስብ ነብዩ አይኑን አፍጥጦ ቀጥ ብሎ እኛ ወዳለንበት መጣና እጁን አንስቶ....... የጓደኛዬ ሚስት ላይ ሲጭን ከተቀመጠችበት ወምበር ሁለት ሜትር ወደላይ ነጥራ መሬት ላይ ተነጠፈች። እግዚኦ ማህረነ ክርስቶስ። ምን ጉድ ነው? በኔ ሲስቅ የነበረው ጓደኛዬ ሚስቱ እንደዚያ ስትሆን ሲያያት ክፉኛ ደነገጠ። እኔም ምን መጣ ብዬ አንዴ ነብዩን አንዴ እሷን ማየት ጀመርኩ ነብዩ “ዋናው መንፈስ ተያዘ!” ሲል ጉባኤው በጩኸትና በጭብጨባ ተሞላ። ከዚያማ ያቺ ድምፀ ለስላሳዋ የጓደኛዬ ሚስት በሙላቱ አስታጥቄ ድምፅ ትለፈልፍ ጀመር “ተቃጠልኩ! አረርኩ!” “ማነህ?” አለ ነብዩ “ጠቋር ነኝ” “ተናገር የት ነው የያዝካት?” “ባሏ ነኝ። ከልጅነቷ አሳድጌ ነው ያገባኋት” አለ ሴጣኑ። ጓደኛዬን አየሁት ሚገባበት ጠፍቶታል። “ጭራሽ የሌላ አካልን ሚስት ነው ያገባሁት?” የሚል ይመስላል። አጋንንቱ ጭራሽ ወደሱ አፍጥጦ “አጠፋሃለሁ አንተ እርጉም ሚስቴን ነጠቅከኝ” እያለ መጮህ ጀመረ። ቺት አድርጋበት መሆኑ ነው። ጓደኛዬ እንዲሁም ፈሪ ነው ጭራሽ አሁን ከሰይጣን ጋር የግል ፀብ ውስጥ በመግባቱ ያልበው ጀመር። ያቺ መላአክ የመሰለች ሚስቱ ጭራሽ አይኗን አፍጣ በወፍራም ድምፅ ዛቻዋን ቀጠለች። “ወንድወሰን ደበበ ጊሚራው” አለችው ሌባ ጣቷን ወደሱ ጠቁማ። {ዳዲ ቀረ በቃ} ነብዩ ዝም ብሎ ያያል። “አንተን ካላጠፋሁ እኔ ጠቋር አይደለሁም” አለ መንፈሱ። ጓደኛዬ እንባ ተናነቀው። በሆዱ "Who TF did i marry?" እያለ ነው “ብዙ ግዜ በተኛህበት በገጀራ እንድትሰነጥቅህ አቅጄ ነበር። ዛሬ ይሄ ነብይ ቀደመኝ” እያለ ማጓራት ጀመረ። ጓደኛዬ እንባውን በአራት መንታ አወረደው። ምን ውስጥ ነው የገባሁት? የሚል ይመስላል። ብቻ አጋንንቱ ከነብዩ ጋር ውጣ አትውጣ እያለ ሲታገል እኔ እንደምንም ሾልኬ ወጥቼ ወደቀበሌ ጃምቦ ቤት ሮጥኩ። ከአዳራሹ ወጥቼ ጥቂት እንደሮጥኩ ሩጫዬን አቀዘቀዝኩና ወደኋላዬ ስዞር ጓደኛዬ ኮቱን ጥሎ በሩጫ ወደኔ ይመጣል። አጠገቤ ሲደርስ እያለከለከ ቆመና “ወዴት ነው ጥለኸኝ ምትሮጠው” አለኝ “እንዴ አንተስ ሚስትህን ጥለህ ወዴት ነው?” ስለው “አፍህን ዝጋ” ብሎኝ አብሮኝ ወደግሮሰሪ አመራ። አሁን ሰባተኛ ጃምቧችን ላይ ደርሰናል። “እኔ ግደሉኝ እንጂ ያቺን ሴት አምኜ እዛች ቤት አላድርም” ስላለ ተሰብስበን ወደቤቱ እንዲሄድ እየለመንነው እንገኛለን። By Noah Daniel @wegoch @wegoch @paappii

የቆሰለ ነገር ፣የከሳ ፣የኮሰመነ እንሰሳ እሚያድን አውሬ ያስጠላኛል ምቹ ግዜ እየጠበቀ ድምፁን እና ሁኔታውን የሚቀያይር ሰው ግን ያስፈራኛል። ስዩም ፦ ጓደኛው ነኝ ጓደኛዬ ግን አይደለም። ብዙኅ አሳልፈናል ። ቢሰማብኝ የማፍረውን ነገር ወይ ቢሰማብኝ ጉድ የሚያደርግብኝን ነገር አልነግረውም ። እፈራዋለሁ። ቋሚ ወዳጅ ስለሌለው እና ዋሉልኝ ያለቸውን ሰዎች ሁሉ በየምክንያቱ ስለሚተዋቸው እፈራዋለሁ ። ከጓደኞቹ X ስር ስለማይጠፋ ስሜቱን ሁሉ የተሰማው ሰዓት ስለማያንፀባርቅ አብሬው ሆኜ አይጥ ለመያዝ ትክ ብላ እንደምታደባ ድመት ነው የማየው። እሱ እንደድመቷ ትኩረት ሲያደርግ ሁኔታው እንደድመቷ አይነት አይደለም አያስታውቅበትም ። ዘና እያለ እየሳቀ ሚስጥር እየነገረ ነው ሚስጥር የሚያስወጣው ። ስዩምን እፈራው ነበረ .....! ችግር ገጠመኝ ከሁሉም በላይ አብሮኝ ሆነ ያለውን ሁሉ ሰጠኝ አሰጣጡ ስሙልኝ እዩልኝ ያለው አልነበረም በችግሬ አብረውኝ ያልነበሩትን ስወቅሳቸው እያገዘ አላባባሰብኝም... "ተዋቸው አልሞላ ብሎቸው ነው" አለኝ ....ከነሱ ጋ ሆኜ ያጣጣልኩት ስዩም አብሮኝ ቆመ .... ተፀፀትኩ ...! ከብዙ ግዜያት በኋላ ስዩምን በየወሬው እንደዚ አትመስለኝም ነበር እያልኩ እሱ ላይ ያለኝን አቋም ተናዘዝኩ አልተናደደም ሳቀ ስልከው እና ሲላከኝ እንደኩያ አይደለም እንደታናሽ ነው ሲተማመንብኝ እንደታላቅ ነው ...! እሚያግዘን እና የሚኮራብን ወዳጅ የኛ ሲሆን የሚሰማውን ምቾት አሰማኝ ከጥቂት ግዜ በኃላ ... ስራ በዛብኝ ብዬ የሰጠሁንት ላግዝ ብሎ የወሰደውን ሙሉ ውክልና ተጠቅሞ መኪናዬን ሸጦ አውሮፓ መግባቱን ከሳምንት በሆላ ሰማሁኝ ... ስስቅ ላየኝ ሰው ተታልዬ አልመስልም ነበር ... ማመን ከመጠራጠር በላይ ዋጋ ያስከፍላል ማለት ነው ?? መፍራት ከመድፈር በላይ አቅም አለው ማለት ነው ?? ኮቴ በሰማን ቁጥር እየባነንን የት ድረስ እንሄዳለን ?? የሄድንበትን መንገድ እየጠየቅን መሄድ የሰውነት እጣ ፈንታ ነው ??.... በርግጥ የግዜ ጉዳይ እንጂ ከተካደ ሰው የከዳ ሰው ያሳዝናል!! By Adhanom Mitiku @wegoch @wegoch @paappii

Repost from Sunset Hiking
🌄 We’re Back And We’re Hiking Again Hey Sunset community 🌄 Life happened. The city got louder. And for a while, the sunsets
🌄 We’re Back And We’re Hiking Again Hey Sunset community 🌄 Life happened. The city got louder. And for a while, the sunsets were quieter without us. Sunset Hiking is officially back with a stronger team, clearer plan, and a growing 4,000+ hiking community ready to move again. Over the next weeks, we’ll be sharing: 🥾 Upcoming sunset hikes 🌅 Community moments 🧭 Safe, well-organized experiences If you’re still here, it means you love nature as much as we do. Let’s start again one sunset at a time. 🌄👣

የ ሥዓሊ እና መምህር ኃይሉ ክፍሌ "ተገማች፡ ዋዜማ" የሥዕል አውደርዕይ እዚህ ትርዒት ላይ ተገኝቼ፣ በከተማ ዝመና ውስጥ የማንነትንና የትዝታን ትርጉም የሚፈትሹ ስራዎችን ተመልክቻለሁ። የጥበብ ስራዎ
+9
የ ሥዓሊ እና መምህር ኃይሉ ክፍሌ "ተገማች፡ ዋዜማ" የሥዕል አውደርዕይ እዚህ ትርዒት ላይ ተገኝቼ፣ በከተማ ዝመና ውስጥ የማንነትንና የትዝታን ትርጉም የሚፈትሹ ስራዎችን ተመልክቻለሁ። የጥበብ ስራዎቹ የሚጠቀሟቸው ቁሶችና የሚያነሷቸው ሰብአዊ ጥያቄዎች ቆም ብሎ ለማሰብ ትልቅ እድል ይሰጣሉ። የለውጥ ሂደቱ ወዴት እየወሰደን ነው? የጋራ ትዝታችንን እያካተትን ነው ወይስ እየረሳን? እነዚህንና መሰል ጥያቄዎችን የሚመልስ ድንቅ ትርዒት ነው። እድሉ ያላችሁ እንዳያመልጣችሁ! 📍 እስከ ግንቦት 24 ድረስ ክፍት ነው @Seiloch #Hailukifle #artExhibition.

ሰው ብቻ አይደለሽም! Sirak Wondemu እናትነት ዓለምን አምጦ መውለድ ነው። በምጥ ጣር ተይዞ ለሚቃትት ነፍስ የውልደት እልልታን በከንፈሩ ሰማይ ይዞ እንደሚዞር ደመና ነው። ሰው እውነትን መፃፊያ ጠመኔ ሲሆን እናት የጠመኔው መዳረሻ ሰፊ ሰሌዳ ናት። ትሁንልህ መወደሻ ተብላ በባርኮት የተሰጠች ስጦታ! በግምባሯ መስመር ላይ ዘመን ፅፋለች። በመዳፏ ስር ሕይወት ወልዳለች። ሽብሽብ ቆዳዋ እድሜን ዘምሯል። ዳሳሽ ጣቶቿ ቀንን ፈክሯል። ሰው ብቻ አይደለችም! በወዟ ጠፈፍ ከራሰ የሻሿ ጨርቅ የበለጠ የዓለም ታሪክ የለም። ጊዜና የሕይወት ዑደት አዳውረው በጥቁር ጸጉሯ መሀል እንደበተኑት የሽበት ተክል ያህል መቆዘሚያ ሀሳብ አልነበረም። እማማ ንፁህ ፈገግታሽ የንግስ ቀን ነው። የእሺታ ደጅሽ የዓለም ብርሃን ነው። ሁሉን ቻይ ልብሽ ዕፁብ ተምሳሌት ... በጊዜ ጣይ ፊት የማይሞት አይነት ፤ ነው። ኩርፊያሽ ውስጥ እንደነገሩ የወለድሽው ልጅ ፈገግታሽ ያጫውተኛል። የውሸት ተኮሳትረሽ ከሸበሸብሽው የግምባርሽ መስመር ላይ መጥምቁ ዮሐንስ እየሱስን ባጠመቀበት ቅፅበት ትከሻው ላይ ያረፈችውን ፀዓዳ እርግብ እመለከታለሁ። አለሀሳብ መከደን ካማረው መንታ ዓይኖችሽ ውስጥ ፍቅር ጠምቃለሁ። ሰው ይርበኛል። ተስፋ ጠምጄ... እምነት አርሳለሁ! እማማ ልጄ ሰው ሆነልኝ ዩኒቨርስቲ ገባልኝ ብለሽ ግማሽ ደስታ ግማሽ ሀዘን ሆነሽ የሸኘሽኝ ቀን ትምህርትን ለዘላለም ረገምኩ። ከእነዚያ ብርሃናማ ዓይኖች ብርቅ ... ከህመም ፈዋሽ ጠረኖችሽ ብሸሽ ... ከሞት መላሽ ዳሳሽ ጣቶችሽ ብሰደድ ፤ ማወቅ የገሀነም ፀሎት ሆነብኝ። ክረምቱ መጥቶ ጉያሽ ውስጥ ሽሽግ እንድል አርጩሜ ቆርጠሽ በጋውን አባሪልኝ። ኮስተር ብለሽ ሀምሌን ጥሪው። ነሀሴም ይምጣ! አንቺ ከተቆጣሽ ሁሉም ቀና ይሆናል! እማማ እምባ አርግዞ በስስት የሚያየኝ ክርትት አይኖችሽ እንዴት ናቸው? ዛሬም ለመንገደኛ እንዳዘኑ ነው? ለነፍሰጡር ላም እንደተንሰፈሰፉ ነው? በቅርሻቴ ያረጠብኩት ጀርባሽ ... ዓለሜን የተሸከመው ጫንቃሽ ዛሬም ከመቻሉ አልተፈታም? እኔማ እነሱን ለማየት ለመንካት በስንት ቀናትና ወራቶች ደረት ላይ ተሳብኩ! ሺህ ናፍቆት ከፊቴ ሺህ ጉጉት ከኋላዬ አጅቦኝ በርሽ ለመቆም ተሳልኩ! ለስንት ንጋቶች ለፈፍኩ! ሰው ብቻ አይደለሽም። ብትይኝም አላምንሽም! ሞገስሽ ልክ እንደታቦት ነው። ቁጣሽ ሀገር ያርማል። የወደቀ ቀዬን አንስቶ በውል ያቆማል። ዝምታሽ እንደፍርድ ቀን ይጨንቃል። ይጠባል። ሳቅሽ እንደእሸት ባቄላ ታኝኮ አይጠገብም። መርቀሽ የሳምሽኝ ግንባሬ ዛሬም በብርሃን እንደታጀበ ነው። ኑርልኝ ብለሽ የመረቅሽኝ ምርቃት እኔ ካልሰለቸኝ ከሞት እንደሚታደገኝ ቃል ገብቶልኛል። እማዬ ከእንግዲህ ይራባል ብለሽ አትስጊ! ይልቅ የስጋት በርሽን ዝጊ! ያኔ በጨቅላነቴ ዘመኔ እንደወፍ ልጅ ከአፍሽ ነጥቄ የጎረስኩት እስከ እለተ ሞቴ ከአንጀቴ ይኖራል። አምሳያ የሌለው ውዴታሽ ሞትን ማምለጫዬ ነው። የአንቺ ትካዜ የሀገር መፍረስ ነው። ያ ልዝብ ቃልሽ የንጋት ቀን ነው። ሰው ብቻ አይደለሽም! በነጠላሽ ጫፍ የሰው ልጅ ቋንቋ የማይገልፀው የእረፍት ዋኔ - በመቀነትሽ ስር ያልታየ ያልተሰማ ስውር ቅኔ ተቋጥሯል። ከአንቺ ጋር አይደለም አስር ሀያዬን ሰባ ሰማኒያዬን መሰንበት እፈልጋለሁ። እማ አንቺ ወዳጅ የለሽም ወዳጅሽ እኔ ነኝ። እኔም የአንቺን ያህል ግምት ሰጥቶ የሚቀበለኝ ወዳጅ የለኝም። ወዳጄ አንቺ ነሽ! ቀሚስሽን በለጋ ጣቶቼ ጨብጬ የቆምኩባቸው የጎረቤት ቡና ቅፅበቶች አይረሱኝም። ገበያ ሄደሽ እስክትመለሺ መንገድ መንገዱን እያየሁ ጉበን ታቅፌ የተኮራመትኩባቸው ወቅቶች አይኔ ላይ ናቸው። አባቴ ነጥቆሽ ዓመት ከዓይንና ድምፅሽ ርቄ የተመለስኩ ቀን ዘማች በህይወት ተርፎ እንደመጣልሽ ሁሉ በስስት ያነባሽው ዕምባ አንቺ ብትፈቅጂ ወንዝ ሆኖ ይወስደኝ ነበር። ሰውነትን የለካሁብሽ ፤ የፍቅርን ትርጉም የሰፈርኩብሽ ፤ ትናንትን ፣ ዛሬንና ነገን የመዘንኩብሽ ሚዛኔ ነሽ። ሳቅሽ ውሎ ሳይገባ እንዳይመሽ እፀልያለሁ። ስጋትሽ ስጋት በልቶት ሳይጠፋ ዘመን እንዳያልፍ እፈልጋለሁ። በትከሻሽ ላይ ቆሜ ጎበዝ ተብያለሁ። አንድ የናፍቆትሽ ዘለላ አንገቴ ላይ ቢታሰር ይዞኝ ጥልቅ እንደሚወርድ ግን የተረዳኝ የለም። አድጌ አንቺን ረሳለሁ? ቤት ይኖረኛል? እሸሽሻለሁ? አመመኝ ብትይ እረጋጋለሁ? ልቤ ይሰክናል? እኔ'ንጃ ! ልጅ ሆኜ አጎቴ ሞቶ በሀዘን ቅስምሽ ስብር ሲል ፤ ማቅ ስትለብሺ እግዜር ከትምህርት ቤታችን ዳገት በላይ ያለ እየመሰለኝ ሄጄ «አንተ አትችልም እናቴ ትሁን! » ብዬ መኮሳተር ያምረኛል። ሰፈር ሰው ሞቶ ለቅሶ ስትሄጂ መንደርተኛው እርር ሲል ... ምርር ብሎ እምባውን በጉንጩ በራፍ ሲደፋ ያ አባባሌ እውነት ሆኖ እታዘባለሁ። « በቃ እሱ አይችልም እናቴ ትሁን! » እላለሁ በልቤ። እዝነት እንደሌለው ሁሉ ፤ ምህረትን እንደማያውቅ ዝንጉ አባት ፍፁምነቱን እንድጠራጠር ያደረገኝ ፍቅርሽ ነው። ለሁሉም ነገር ሆደ ባሻ የሚሆነው አዛኝ አንጀትሽ ነው። አንቺ እኮ እግዜርን ብትሆኚ የሰፈራችን ሰዎች በሙሉ ማሪያም ቤተክርስቲያን እንዳሉ ዛፎች ሰማይ ጠቀስ እንደሆኑ ይሸብቱ ነበር። እማማ እርጅና በአንቺ ላይ ስልጣን እንዳይኖረው የአንቺን ቁጣ ኮርጄ እቆጣዋለሁ። ሞት በሰፈርሽ እንዳያልፍ በርሽ ላይ አያ-ጅቦ እንዳለ ነግሬ አስፈራራዋለሁ። እማማዬ ቃል የእምነት እዳ ነው ይላል ፀጋዬ። ቃል የእምነት ዕዳ መሆኑን የተረዳሁት ግን በአንቺ ነው። ዛሬም በሰው ሀገር ሆኜ የተቆላ ቡና ሲሸተኝ ትዝ ትይኛለሽ። ትኩስ ሽሮ ሲሸተኝ ፤ ጠይም ፈገግታም እናት ስመለከት ዓይኔ በእምባ ይሞላል። ማን ያውቃል ዛሬም ህፃን ልጅ ሲጮህ ትደነግጫለሽ አይደል? በሌለሁበት ቀዬ ተጋደሉ ሲሉሽ እግርሽን ብርክ ብርክ ይልሻል አይደል? እማዬ ጌሾ ያልወቀጠልሽ እጄን እጠላዋለሁ። ስታዢኝ በእምቢታ የሰበቅኳቸውን ትከሻዎቼን እጠየፋቸዋለሁ። ለእነዚያ ጊዜ ... ለእነዚያ ወቅቶች መዳፍሽ ስር ፊቴን ቀብሬ ማልቀስ እፈልጋለሁ። ስትገርፊኝ ያኮረፍኩባቸውን ቀኖች ባገኛቸው እንደልጅነቴ ድንጋይ ወርውሬባቸው ሮጣለሁ። ማጀትሽ በጥጋብ ይሙላ! ... ሰላምሽ እንደአሸን ይፍላ! የጦር ቃል ጆሮው ይደፈን ... በደጅሽ ፍቅር ይሸመን! ማሳሽ ላይ አዝዕርት ይብቀል! ... ይመር ሰማዩ እንደምንጭ ይጥለል። አዛኝ ነሽና መርቂኝ አለሁ... ክፉሽን ከቶ አልስማ ሳለሁ! ገብያሽን ጥጋብ ይውረሰው አይጉደል ዘመኑን ሙሉ... የተኳረፈም ይታረቅ ሁሉ! አካል ነሽና ለምድሩ ለሰው... ስሁት ደስታሽን ቀን ይደግሰው! ብቻ እማማ አንቺ ሰው ብቻ አይደለሽም ፤ እግዜር ነሽ ለልጅሽ ... ሚዛን ነሽ ለምድሩ.. ባርኮት ነሽ ለሰማይ አድባር ነሽ አውጋር ነሽ የኔ አድባር። መላዕክ ነሽ ልዩ ሰው! የአጥቢያ ዳኛ የአንቺን ያህል ፍትሕ አያውቅም! ውብ አዝማሪ ከእሽሩሩሽ የተሻለ ዜማ አይደርስም። በዓይኖችሽ ስር የፀነስሽው የተስፋ እምባ ለመኖሬ ለመዳኼ ሆኗል መባ! አለው ዋጋ! አለው ፀጋ። አስራቴ ነሽ ጃኖ ጥለት... ወደር የለሽ የሰው ቁመት። ብቻ ብቻ . . . አንቺ ሰው ብቻ አይደለሽም... ብትይኝም አላምንሽም። . . . መልካም የእናቶች ቀን ❤

ሶምሶማ የአጫጭር ልቦለዶች መጽሐፍ -በጃፋር መጽሐፍት መደብር(ለገሀር) -አብዱ book delivery (ፒያሳ) - +251994886247 ሰለሞን አራት ኪሎ ያገኙታል።@sirakoo @wegoch @wegoch @wegoch

ADDIS ABABA — FOR SUDAN Voices From Sudan On April 21, join us for a powerful evening where film, music, and community come t
ADDIS ABABA — FOR SUDAN Voices From Sudan On April 21, join us for a powerful evening where film, music, and community come together to mark the 3rd anniversary of the Sudan war. The night opens with a special live performance by The Tana Quintet by Hazim Alshafei, bringing the rhythm, soul, and resilience of Sudan to life—followed by a screening of the acclaimed film Khartoum. ✨ Free Entrance This is more than a screening. It’s a gathering. It’s a shared moment. It’s solidarity in action. Expect a full house, a powerful atmosphere, and a night that will stay with you. 📅 Tuseday, April 21, 2026 📍 Bata Complex 22, around Golagul 🕠 5:30 PM Bring your friends. Be present. Stand with Sudan. #Khartoum #Sudan #AddisAbaba #InDeepCultures #FilmScreening #LiveMusic #1960Films #AddisCinemaClub

📌 በሀዋሳ ከተማ አዲስ የስነ-ጥበብ ትምህርት ቤት የምዝገባ ጥሪ! ጥበብን ለሚወዱ እና ተሰጥኦአቸውን ማሳደግ ለሚፈልጉ ሁሉ ታላቅ እድል! በሀዋሳ ከተማ ከዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አዲስ የስነ-ጥበብ (ስዕል) ትምህርት ቤት ስራ ሊጀምር ዝግጅቱን አጠናቋል። 🎨 ለምን ይመዘገባሉ? • በዘርፉ ብቁ በሆኑ ባለሙያዎች የታገዘ ስልጠና ለማግኘት። • ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በተቀናጀ መልኩ እውቀትን ለማዳበር። • የፈጠራ ስራዎትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር። 🌟 የእርስዎ ድርሻ፦ ጥበብ የሀገር መገለጫ ናት! ይህ መልዕክት እንዲደርሳቸው የሚገባቸው ወጣቶች እና ፍላጎቱ ያላቸው ግለሰቦች እንዲያውቁት በማጋራት (Share በማድረግ) ማህበራዊ ሀላፊነትዎን ይወጡ። ምዝገባው ተጀምሯል!👇👇 link ይጫኑ https://tally.so/r/D4Jjrl.

ፖስታዬንና ክርታሴን አንጠልጥዬ እንትና በሰጠኝ አድራሻ ታክሲ ይዤ አዲስአባ አስራምስት ቀን ያህል ቆይተን ለመመለስ ሁለት ቀኖች ሲቀረን ሄድኩ። ስድስት ኪሎ አፍንጮ በር አካባቢ ነበር። በር ሳንኳኳ የከፈቱልኝ ጥምጥም ያደረጉ፤ ፂማቸውን የተላጩ፣ ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት ገፅ ያላቸው መልከ መልካም ጠይም ሽማግሌ ነበሩ፡፡ መምጣቴን ቀደም ብዬ ስልክ ደውዬ ነግሬአቸው ስለነበር፣ በስሜ ጠርተው በትህትና እንድገባ ጋበዙኝ፡፡ ቤት ውስጥ እሳቸውና ፊታቸው ብቻ እስኪቀር የተከናነበ ሌላ ሴት ነበሩ፡፡ ገና እንደተቀመጥኩ ራት በልቼ (ማታ ላይ ነበር የደረስኩት) እንድሄድ ሲጠይቁኝ፣ በሥነስርዓት ተከላክዬ ፖስታውንና እቃቸውን በእጃቸው ሰጠኋቸው። ስለ ልጃቸው ጤንነት ከጠየቁኝ በኋላ፤ የሚያበረታታቸውን መልስ ሰጥቼ ከተቀመጥኩበት ስነሳ፣ አንድ የሚያጫውቱኝ ነገር ስላለ በጥሞና እንድሰማቸው አግባቡኝና ተመልሼ በመመቻቸት ተቀመጥሁ። «እግዚአብሄር አንድ ነው፣ አየህ፤ ስሙን ሰዎች ይለያዩታል እንጂ አላህ ብትል፣ እግዚአብሄር ብትል አንድ ነው። ቅድመ አያቴ እስላም ነበሩ። ልጃቸው ክርስቲያን አገባና ከዚያ በኋላ ክርስትናው ቤታችን ገባ። የድሮ ሰዎች ናቸው። ለምን? በለኝ አላህ በለው እግዜር በለው ያው ነው። ልጄ ሆላንድ የቤተክርስቲያን አመራር ይሠራል ሲባል ሰምቼአለሁ፣ እሱም አንዴ ሰላም ሊል ደውሎ አጫውቶኛል። ልክ ነው? (‘ኧረ የማይገባበት ቦታ የለም’) አንድ ነገር ልንገርህ፤ እኔ ወደ ቅድመ አያቶቼ ሐይማኖት ተመልሼአለሁ» ግድግዳ ላይ በመስታወት ውስጥ ሆኖ የተሰቀለ ዳንቴል የመሰለ የዐረብኛ ነገር የተፃፈበት ነገር አሳዩኝ፡፡ «ዐረብኛውን ባላውቀውም አላህ ከሰዎች ጋር በሚገባቸው ቋንቋ ይናገራል፡፡ ነቢዩም እንዲህ ነው የሚያስተምሩት፤ ስማቸው ይባረክና፡፡ ግን ልጄ እንዲከፋው አልፈልግም፡፡ ‛አባቱም እናቱም ሰለሙ' ተብሎ ቢሰማ ያዝናል፣ ይበሳጫል፡፡ (ኧረ ካሽ ካገኘ ግድ የለውም)፡፡ ግን እዚያም ስገዱ ነው፣ እዚህም ስገዱ ነው። 'አለማየሁ' የተባለ ስሜን ‛አብዱላሂ' አሰኝቼአለሁ፡፡ የሰፈር ሰው ገና አለማየሁ' ነው የሚለኝ፡፡ ክፋት የለውም፡፡ እንዲህ ያደረግነው ለጥቅም አይደለም፡፡ ለእሱ ነው። ለእምነቱ ነው። ታዲያ ከልጄ ጋር ተገናኝታችሁ ድንገት ወሬ ቢነሳ መነሳቱ መቼም አይቀር፣ እንደ ሰለምኩ አትንገረው፡፡ ይኼን ቃል ግባልኝ፡፡ ያለዛሬ አይቼህ አላውቅም፡፡ መቼም ታምነህ የተላክህ ሰው ስለሆንክ፣ ብትግባቡ ነው መቼም (‛ከቴም ተግባባን') ቢሰማ ችግርይኖረዋል? እንጃ እንግዲህ ባትነግረው ባታወራው ግን ይመረጣል፡፡ እንዳይሳትህ ብዬ ነው» ሴትዮዋ/ባለቤታቸው ከእኛ ራቅ ብለው በጋቢያቸው ተሸፋፍነው ታስረው የተቀመጡ መስለዋል፡፡ ቃል አውጥተው አይንገሩኝ እንጂ ከአስተያየታቸው፣ ከአንገት አደፋፋቸው እየተለማመጡኝ እንደሆነ ይገባኛል፡፡ ለሰውዬው ከአፌ ቃል እንደማይወጣኝ፣ በተፈጥሮዬ (ምናልባት ስወለድ ጀምሮ ወይም ከእናቴ ሆድ ጀምሮ ለሐይማኖት ግድ እንደሌለኝ፤ እንደውም እሳቸው ያሉት የእግዜር መመሳሰል ትልቁ እውነት እንደ ሆነ አንስቼ) ሳይሆን አይቀርም ሚስጢር ቀርቃሪ በመሆኔ ትንፍሽ እንደማልል፣ አንዲት ቃል ከአፌ ጠብ እንደማትል ቃሌን ሰጠኋቸው፡፡ ክርስቶስን ጠርተው መረቁኝ፡፡ ከተቀመጡበትም ተነስተው ትከሻዬ ላይ ሳሙኝ፡፡ ሲሰናበቱኝና ሲሸኙኝ ሽማግሌው ዐይኖች ውስጥ ሊሸፍኑት ያልቻሉት ወፍራም እፍረት ነበር፡፡ ለመቅደስ ይሄን ሁሉ አልነገርኳትም፡፡ *** By | አዳም ረታ/ 📖 ይመያመ @wegoch @wegoch @paappii

የሳሪሱ ወጣት እና የቱርኳ Player ------------------------------------- ምነው ባላወቅኳት ያልኩበት ጊዜ ነበር...! at that time She gave me a Trauma. የደግነት ማስኳን አጥልቃ ነገር ግን የክ-ፋት ሀሳቧንም በውስጧ ሰቅዛ ተለሳልሳ ስትቀርበኝ ምን ነበር አይኔን የጋረደው..? 😁 . . እንዴት ልታሳየኝ የፈቀደችውን ብቻ ተመለከትኩላት..? ልትደብቅ የሞከረችውን ማንነት እንዴት ማየት አቃተኝ..? ወቅቱ 2014 ዓ.ም ነው። ወርሀ መጋቢት። ክስተቱ ዛሬ ድፍን አራት አመት ሞላው። በአንዲት የቢሾፍቱ ቆንጆ የተታለልኩበት ሁኔታ እና አጋጣሚ ተፈጥሮ ነበር። አጃጃለችኝ። አሞኘችኝ። አጭበ-ረበረችኝ። አወጫበረችኝ። የምትኖረው ቱርክ ነው። በወቅቱ Turkey መኖር ከጀመረች 3 አመታትን ያህል አስቆጥራለች። የተዋወቅነው በ Facebook ነው። Long Distance Relationship መሆኑ ነው እንግዲህ። ከ Messanger ወደ Telegram ባደገው የስልክ ልውውጣችን - በየቀኑ ለሰአታት በ Video call እናወራ ነበር። አስታውሳለሁ የሆነ ሰአት ላይ እንዲሁ በ Telegram - Video call አውርተን ስንጨርስና መጨረሻ ላይ ቻው ስንባባል - ስልኩን "አንተ ዝጋው..አንቺ ዝጊው..አንተ ዝጋው.." ተባብለን እናውቃለን። ከአንዴም ብዙ ጊዜ። Straight 5 ሰአት ያህል በስልክ የምናወራበትም ጊዜም ነበር። . እንደ እኔ እንደ እኔ ይህ ፍቅር የሚባለው ነገር መጃጃል ነው የሚመስለኝ።It is all Imagination. Glazing a person without any valid reason. There is no reason to glaze someone like that. ይህ ጉዳይ በሳይንሳዊው ዓለም Limerence ወይም ደግሞ Halo Effect ተብሎ ይጠራል። አንድ ሰው ሲያፈቅር አንጎሉ ውስጥ የሚረጩት Dopamine እና Oxytocin ልክ እንደ እ-ፅ ናቸው። እነዚህ ኬሚካሎች ሲበዙ ደግሞ... የወደድነውን ሰው ድክመት እንዳናይ ያደርገናል፣ የማይረቡ ነገሮችን እንደ ትልቅ ቁምነገር እንድንቆጥር ያደርገናል፣ በዚህ ሰዓት የምንወስነው ውሳኔ Logic የለውም። . ለማንኛውም.. የባለታሪካችንን ስም R እንበለው። R እሳት ነች ፤ ዛሬ ላይ ሁሉም ነገር አልፎ ሳስበው አድናቂዋ ነኝ። እንዴት እንዳወጫበረችኝ ሳጤነው በራሴ ሽምቅቅ እላለሁ። ቢሾፍቱ ተወልዳና አድጋ የመሀል ከተማ ልጅ [ የአዲስአበባ ልጅ ] ለዛውም የሳሪስ ልጅ ላይ ድራማ የሰራች እሳት ናት። መጀመርያ ከእኔ ጋር የፍቅር ግንኙነት ስትጀምር ሌላ ያላለቀ ግንኙነት ላይ እያለች ነው። እኔ ይህንን አላውቅም ነበር። መጨረሻ ላይ ነው የደረስኩበት። መጀመርያውኑ ፍቅረኛ እያላት ለምን ከእኔ ጋር መሆን ፈለገች..? . ከእኔ ጋር እንደተዋወቅን እንዲሁም ለረጅም ጊዜ [ ለ 4 ወር ያህል ] in Contact እያለን የበፊት ፍቅረኛዋን ሙሉ ለሙሉ አልተወችውም። በሳምንት 1ዴ ወይም 2ቴ እየደወለች ታወራዋለች። ከእኔ በፊት የነበረውን ልጅ ከመተዋወቋ በፊት ደግሞ ሌላ ፍቅረኛ ነበራት - unfortunately ያንንም አልተወችውም። ከዛ በፊትም ሌላ ፍቅረኛ ነበራት - ያንንም አልተወችውም። ሁላችንንም አልተወችንም። እንደ የቤት አውቶሞቢል [ የቤት መኪና ] በአንድ ጊዜ 4 ሰው አሳፍራ ነበር ስትጓዝ የነበረው። ልጅቷ Multi-tasking ትችላለች። በአንድ እጇ ለኔ ቴክስት እየፃፈች፣ በሌላኛው እጇ ደግሞ ከሌላው ጋር ቪዲዮ ኮል ታደርጋለች። 4 መኪና በአንድ ጊዜ የምትነዳ Formula 1 ድራይቨር ናት። ይሄን ሁሉ መጨረሻ ላይ ነው የማውቀው። ከአንድ ወንድ ጋር ሆና - ወደ ሌላ ወንድ። እኔን አስምጣ ወደ ሌላ - ያኛውንም አስምጣ ወደ ሌላ - ይሄኛውንም አስምጣ ወደ ሌላ። She is a player type of sh-it. . በአንድ ጊዜ አራት ወንዶችን እንደ ቼዝ ጠጠር እያገላበጠች ስታጫውት አንዱ ለሌላው እንቅፋት እንዳይሆን ያደረገችው Scheduling የሚገርም ነበር። እኔ ስልኩን "አንቺ ዝጊው.. አንተ ዝጋው" እየተባባልኩ በቪዲዮ ኮል ስሟገት፣ እሷ ግን ለካ በሌላ ስልኳ ሌላኛውን "አንተ ዝጋው.." እያለችው ነበር። ፍቅር ሳይሆን ለካ የኔትወርክ መጨናነቅ ውስጥ ነበርኩ..😁 በነገራችን ላይ.. እኔ በጣም ጠንቃቃ ነኝ። እንደ እኔ ተጠራጣሪ ሰው አልነበረም / አሁንም የለም። ማንንም አላምንም። መጨረሻ ላይ ይሄ ባህሪዬ ወይም ጥርጣሬዬ [ my Gut felling ] ነው እውነታው ላይ እንድደርስ ያደረገኝ። እኔ ጥላዬንም አላምንም። እሷን ግን እንዴት ላምናት እንደቻልኩና - ሙሉ ሀሳቤን እንደሰጠኋት ሳስብ ይገርመኛል። እንኳን ክፉ ድርጊት ሊያደርግ ያሰበን ሰው ይቅርና ያላሰበን ሰው ራሱ የምጠራጠር አይነት ሰው ነኝ። . ልባችሁ የሆነ ነገር ሲነግራችሁ አትናቁት። ልባችሁ የሚነግራችሁን አትናቁ። እኔ ተጠራጣሪው የሳሪስ ልጅ፣ በውበቷ ምክንያት እውነታው ተጋርዶብኝ Gut Fellingኤን አላዳመጥኩም ነበር። ቆንጆ ፊትና የተረጋጋ አንደበት ሁልጊዜም ቅንነትን አይወክሉም። አንዳንዴ እጅግ Calculated የሆነ አቀራረብ ከጀርባው የተቆፈረ ጥልቅ ጉድጓድ እንዳለው ማወቅ ነበረብኝ። እኔ ተጠራጣሪ ነኝ እያልኩ ግን የእኔ Gut feeling የሚሰጠኝን ምልክት ውበቷ ሸፍኖብኝ ነበር። ጥርጣሬ መጥፎ አይደለም። መጠርጠር ማለት ነፍስህ ራስህን እንድታድን የምትሰጥህ Alarm ማለት ነው። Infact በመጀመርያዎቹ ሳምንታት ያሳየችኝ እጅግ Calculated የሆነ - እንዲሁም የተጠና አቀራረብ አውሮኝ ነበር። . በውበቷ አሻፍዳኝ፣ በምላሷ አታላኝ የገባሁበት የ 6 ወር የፍቅር ህይወት በመጠኑም ቢሆን Scar ጥሎብኝ አልፏል። ፍቅር እውር ነው ይላሉ። እኔ ግን ሽፍድናዬ ነው ያሳወረኝ እላለሁ። ልጅቷ ቆንጆ ናት። በተለምዶ ቀይ የምንለው ወይም Light skinned የሆነው የቆዳ ቀለሟ - እንዲሁም ሰላም ተስፋዬን የሚመስለው መልኳ - ጨዋ ጨዋ የምትጫወተው ነገር - ምሁር ምሁር አንባቢ አንባቢ የሚያደርጋት ነገር - ይሄ ሁሉ ተደማምሮ አስምጣኝ ነበር። በኋላ ላይ ግን ሁሉንም ነገር ስደርስበት እኔ ብቻ አይደለሁም የተጣላኋት። እያንዳንዱ ስታወራቸው የነበሩ ወንዶችን ሰብስቤ እስካሁን እየተጫወተችብን እንደሆነ ነግሬያቸው አስረድቻቸው እነሱም አይንሽን ለአፈር ብለው ተለይተዋታል። . ታዲያ በመጨረሻ ሁሉንም መኪናዎች በአንድ ጊዜ ለማሽከርከር የሞከረችው Formula 1 ድራይቨራችን፣ በራሷ ስህተት Crash አደረገች። እያንዳንዱን ተሳፋሪ / ተበዳይ ሰብስቤ እውነታውን ሳስረዳቸው፣ ለካ ሁላችንም በአንድ ቃል ተገዝተን፣ በአንድ መስመር ስንታለል የነበርን ምስኪኖች ነን። ፍቅር እውር አይደለም ፤ ፍቅር አስተዋይ ነው ፤ እውር የሚያደርገን ግን የምናየው ውበት ሳያንስ የምንመኘው ህልም ነው። ዛሬ ላይ ሆኜ ሳስበው ግን ይሄ ራሱ አንድ ትልቅ ትምህርት ነው። አሁን የገዛ ጥላዬንም ቢሆን ፋይዳ መታወቂያ / National ID ካላሳየኝ አላምነውም..! 😁 By Fraol Habesha @wegoch @wegoch @paappii

የተወደዳችሁ የወግ ብቻ ቻናል አባላት ነገ በወመዘክር ጊቢ ተገኝታችሁ መጽሐፌን ትመርቁልኝ ዘንድ ልባዊ ግብዣዬ ነው!!
የተወደዳችሁ የወግ ብቻ ቻናል አባላት ነገ በወመዘክር ጊቢ ተገኝታችሁ መጽሐፌን ትመርቁልኝ ዘንድ ልባዊ ግብዣዬ ነው!!

ከአንዲት ቆንጅዬ ልጅ ጋ ነበርኩ። መኪና ውስጥ ነበርን ፒዛ እየጋበዝኳት አስተናጋጁ ሲያልፍ በእጄ ቢል እንዲያመጣልኝ ነገርኩት ቢል ይዞ መጣ እያየኝ ከፊት ከኃላ ኪሴ አውጣጥቼ ሂሳብ ከፈልኩ ... ሄደ .... መልስ መጠበቅ ጀመርኩ አልመጣም ጠበኩት አልመጣም ተበሳጭቼ ክላክስ አስጮህኩ (ሱሰኛ ይመስላል ፣ የቀረውን ገንዘብ ለማስቀረት አስቦ ነው ፣ ጉርሻ በፍቃደኝነት የሚሰጥ እንጂ በብልጠት የሚዘገን አይደለም ፣ ሲቆይብን ሰልችቶን እንድንሄድ ነው ) ያስጮኩትን ክላክስ ሰምቶ መጣ "መልስ ስጠን እንጂ ጌታው "አልኩት "የሰጠኸኝ ስድስት መቶ ነው ሂሳቡ ደሞ ስድስት መቶ ሰላሳ አምስት ብር ነው "አለኝ ( ስበረብር ስላየኝ የለው ይሆናል በማለት ተሳቆ ነው እንዳልገረጣ ይጎላል ያላለው ) ከሌለህ ብዬ ነው አይነት ፊት አሳየኝ ። አንዳንድ አድራጎት የሚያገዝፈው አደራረጉ ነው ። ይቅርታ ቢሉን በደንብ ስላላስተዋልኩት ነበር። በጣም አመሰግናለሁ አልኩት እንደገና ኪሴን በርብሬ ድፍን ሁለት መቶ ብር ሰጠሁት እንዲመጣልኝ እንዳልቸኮልኩ እንዲሄድልኝ ቸኮልኩ መልስ ሊያመጣልኝ ሄደ ሳይነግሩን ለዋሉልን እየነገርን መዋል ነውር ነው አይደል ? ሳይመጣብኝ ሄድኩኝ ። By Adhanom Mitiku @wegoch @wegoch @paappii

ያች ከልታማ ወለተ ስላሴ ናት አሉ እንደዛሬው ሁዳዴ ፆም ሊገባ ሲል እሁድ ማታ ቅበላ ተብሎ ድስት ሙሉ ወጥ ተሰርቶ ሲዛቅ አምሽቶ ትንሽ ተርፎባቸው አደረ። በበነጋታው ፆሙ ገብቶ እቃ ልታጥብና የፆም ምግብ ልትሰራ ስትል ያደረውን ስጋ ወጥ ለመድፋት አንዤቷ አልችል አለ።እንጀራዋን እጥፍ አርጋ ድስቱን ጠራርጋ በልታ በሳምንቱ ንስሃ ገባችና ስግደት ታዘዘላት። ይችው ሴትዮ ደግሞ ፆሙን ፆማ ጨርሳ ፋሲካ እሁድ ሊሆን ቅዳሜ ማታ ዶሮ ሰርታ አሻቦውን ለመቅመስ ብላ እንጀራዋን መዥረጥ አድርጋ አንዱን ክንፍ አቀላጠፈችው። በበነጋው ለንሰሐ አባቷ ድጋሚ ተሳሳትኩኝኮ ብላ ሀፅያቷን ስትነግራቸው አባ ግራ ገብቷቸው እንዲህ አሏት:-ምነው ወለተ ስላሴ ይሄንን ፆም አላስገባ አላስወጣ አልሽው? እና ይሄንን ያረጀ ወግ ለምን አወጋኋችሁ መሰላችሁ ምነው ግን ፆሙን አላስገባ አላስወጣ አላችሁት? ሊገባ ሲልም ዳንኪራ፣ዝሙት እና ስጋ ሊወጣ ሲልም ዳንኪራ፣ዝሙት እና ስጋ እስኪ ቢያንስ ወይ በመግቢያው ወይ በመውጫው በኩል ሰከን ብላችሁ አስተናግዱት! By koan Ad @wegoch @wegoch @paappii

ሳሯን . . . ----------- አንድ ድሮ መቀለ መካነ ኢየሱስ ቤ/ክርስቲያን አንድ "ገበሬ ነኝ" ይሉን የነበሩ ከአድዋ? ይመጡ የነበሩ አባት ስለ ዕምነት የነገሩን ምሳሌ አለች። ሰውዬው ተንሸራተው ወድቀው ከገደል አፋፍ ላይ ተንጠልጥለዋል። ወደገደሉ ከመውደቅ ያዳነቻቸው አንዲት ገደሉ አፋፍ ላይ የበቀለች ሳር ነች። እሷን ይዘው ጥቂት እንደቆዩ እጃቸው ዛለ። ሊወድቁ ሆነ። ይሄኔ ድምፅ አውጥተው ፀለዩ። "ጌታ ሆይ አድነኝ!" ይሄኔ መልዓክ ብቅ አለና ሰውዬውን "በአምላክህ አዳኝነት ካመንክ ላድንህ ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኬ የመጣሁ ነኝ!" ይላቸዋል። ሰውዬውም "ታዲያ ምን ትጠብቃለህ፣ አምናለሁ! አድነኝ!" ይላሉ። መልዓኩም "መጀመሪያ የያዝካትን ሳር ልቀቅና!" አላቸው። * * * ሳሯን አስለቅቀኝ 🤲 By gemechu merera fana @wegoch @wegoch @paappii

የክብራን ገብርኤል መናኝ ገጠመኝ በዕለታት በአንዱ ቀን ከኪዳን ፀሎት በኋላ ንፋስ ለመቀበል ወደ ሀይቅ ዳርቻ አመሩ፡፡ ተፈጥሮን ያስተውሉ ጀመር፡፡ ሀይቁ፣ ንፋሱ፣ አዕዋፋት፣ በሀይቁ ዳርቻና በደኑ ጥግ የሚራወጡት አርጃኖዎች ብዙ ናቸው፡፡ ጠላቂ አዕዋፋት ሰምጠው ቆይተው የዕለት ምግባቸውን ራሳቸውን ወደ ፈጣሪ አንጋጠው አንገታቸውን ቀጥ አድርገው የዕለት ምግባቸውን ወደ ሆዳቸው ያወራርዳሉ፤ ሁሉም የአቅሙን ይጥራል፣ የመጠኑን ያገኛል፣ ይመገባል፤ ትርፍ ማግበስበስ የለም፤ የአቅምን የድርሻን ብቻ፡፡ በዚህ ትዕይንት መካከል አንድ ንሥር ከገዳሙ ረጅም ዛፍ ጫፉ ላይ ተቀምጦ በንሥር ዓይኖቹ የዓሣዎችን እንቅስቃሴ በንቃት ያማትራል፤ በድንገት በተመለከተው ትልቅ ዓሣ ጓጉቶ ተወርውሮ ወደ ሀይቁ ወረደ፡፡ እንደ ሰንጢ የሾሉ ጥፍሮቹን ከመቅፅበት በዓሣው ገላ /ጐን/ ላይ ሰገሠገ፡፡ የተለመደው ድርጊት ከዚህ በኋላ ረጃጅም ክንፎቹን እያማታ ወደ ላይ መነሣትና ወደ ረጅሙ ዛፍ አልያም ወደ ሀይቁ ዳርቻ በርሮ የዕለቱን ሢሣይ ማጣጣም ነበር፡፡ በዕለቱ መነኩሴው የተመለከቱት ግን አስገራሚ ነበር፡፡ ንሥሩ አድኖ የያዘው ዓሣ እጅግ ትልቅ ከመሆኑ የተነሣ ተሸክሞ መብረር አልቻለም፡፡ ጥፍሮቹ ጫፋቸው ላይ ቆልመም ያሉና እንደ ሜንጦ ያሉ ስለነበር ከዓሣው ለማላቀቅም አልቻለም፡፡ መጨረሻ ክንፎቹን አማትቶ ሲደክመው ሀይቁ ላይ ተመልሶ አረፈ፡፡ ዓሣው ነፍስ ዘራና ወደ ሀይቁ ንሥሩን ይዞት ሰጠመ፡፡ የንሥሩ እጣ ፈንታ መሞት እንደነበር ግልፅ ነው፣ እርግጥ ዓሣውም ከጐኑ የተሰካውን ጥፍር ባለቤት ትልቅ ንሥርን ያህል ተሸክሞ መኖር አይችልም፡፡ ሁለቱም አዳኝና ታዳኝ እጣ ፈንታቸው ሞትና ለሌላ አውሬ ሢሣይ መሆን ነው፡፡ መነኩሴው ባዩት ትዕይንት ተመስጠው ለራሣቸው “ለዐይን የሚያስጎመጅ ሁሉ አይበላም፤ ምናልባት ሞት ያለውም በሚያሰጎመጅ ነገር ውስጥ ይሆናል” አሉ፡፡ ነገሩ እስከ አሁን ድረስ እንደሚደንቃቸውም አጫወቱኝ፡፡ @wegoch @wegoch @paappii By Alemayehu wassie

''ማንቺስተር ያሸነፈ ቀን !'' ትናንት ማንቺስተር አሸንፎ ደጋፊዎቹ መሬት አልበቃቸው ብሎ ሳይ እንደሁሌውም ትዝያለኝ ያ ራሱን 'የአርሰናል ቁልፍ ሰው' አድርጎ ይቆጥር የነበረው ታናሽ ወንድሜ ነው በፍቃዱ ብርሃኑ ይባላል… እማዬ “ፍቃዴ” ትለው ነበር፡፡ እኔን ጨምሮ እሱን የሚያውቁት ሁሉ “ፍቄ” ብለው ነበር የሚጠሩት፡፡ በህጻን አዛውንቱ ተወዳጅ የነበረ ወንድሜ .... ዛሬ በህይወት የለም። ፍቄ ሁሌም ማታ የጠንቋይ መጣፍ የመሰለ ደቃቅ ጽሁፍ የታጨቀበትን ሊብሮ ጋዜጣ ይዞ ወደቤት ይመጣል። ገና ጎረምሳ ነው፡፡ ረጅም ...1 ሜትር ከ87 ሳ.ሜ ቁመቱን በአሮጌው ሶፋ ላይ ዧ አድርጎ እንሩን አንፈራጦ ይቀመጥና …. ፊቱን ጋዜጣው ውስጥ ቀብሮ …ኮስተር ፈታ እያለ ‘የነቡናን እና የነአርሴን' ወግ ይጨመጭማል። “… ምንድነው ግን የምታነበው?” ትለዋለች እማዬ፡፡ ”ስፖርት ነው እማ.. ብዙም አታውቂውም” ይላታል። ”ኡኡቴ! አዋቂ ነኝ ብለህ ሞተሃል..ደሞ ለቅሪላ ወሬ!” ትላለች። ” ጭንቅላትህን በኳስ ዕወቀት ከምትሞላ ትምህርትህ ላይ አትበረታም ነበር? …ደደብ!! …ነገ አርሰናል መጥቶ ይፈተንልህ መሰለህ? ..” ብዬ ልጮህበት እፈልጋለሁ። ግን ብዙ ጊዜ ይህንን ብዬው ጉሮሮዬን አመመኝ እንጂ ያመጣሁት ለውጥ የለም። እማዬ ማለዳ ወደቤተክርስቲያን በምትሄድባቸው ቀናት ወደእግዜር ከምትወስደው የራሷ ጥያቄዎች በተጨማሪ ፍቄ የሚያዛት ተጨማሪ ፀሎት አለ። ጨዋታ ያለ ቀን ወይ ቡና… ወይ አርሰናል እንዲያሸንፍ እንድትጸልይለት ይነግራታል፡፡ የሆነ ጊዜ የቡና ረከቦቷን የምትሸፍንበትን ጨርቅ አነስቶ ጥሎ በምትኩ ሁለት የቡና አርማ ያለበትን ባንዲራ አሰርቶ አመጣና አንዱን “የቡና ስኒ በቡና አርማ ነው መሸፈን ያለበት” ብሎ ሰጣት፡፡ አንዱን ደግሞ የቤታችን ግድግዳ ላይ በሚስማር መትቶ ሰቀለው፡፡ ቤት ስገባና የሆነውን ሳይ ተናደድኩና ገንጥዬ ጣልኩበት፡፡ የረከቦቱን ግን እማዬ ከለከለችኝ፡፡ "ይሁን፣በገዛ ሲኒዬ ምን አገባህ" ብላ ፡፡ እነዚያ ጨርቆች ዛሬም ድረስ ቤታችን አሉ፡፡ እማዬን “ እሙ!” ነበር የሚላት፡፡ የሚተኛው ከሷ ጋር ነው፡፡ የመጨረሻ ልጅ ስለሆነ ነው መሰለኝ እንደነፍሷ ትወደዋለች፡፡ ጨዋታ ያለ ቀን ታዲያ እማዬ ማለዳ ወደቤተክርስቲያን ለመሄድ ስትነሳ የተሸፈነበትን ብርድልብስ ገለጥ ያደርግና “እሙ! ዛሬ የኔ ቡድን ይጫወታል።እንዲያሸንፍ ጸልዪልኝ ...ካሸነፍን ስለት ታስገቢልኛለሽ! ” ይላታል፡፡ “አይ እዳዬ!..... ደሞ ዛሬ አቡነ ተክለሃይማኖት እንዴት ያረጉኝ ይሆን” ትላለች ። እማዬ ስትምልም ስትለምንም በአቡነ ተክለሃይማኖት ነው፡፡ አንድ ቀን 'የምር ስለሱ ኳስ ጨዋታ ትጸልያለሽ?' ብዬ ጠየቅኳት፡፡ “እንዴ አዎና!...ተክልዬ !! የዚህን ልጅ ልብ የበሉት ባለኳሶች እንዲያሸንፉ እርዱልኝ…..ጉድ እንዳይሰሩኝ ኋላ! እላቸዋለሁ” አለችና አሳቀችኝ። ምን ታድርግ? የርሱ ክለብ የተሸነፈ’ለታ ቤታችን የሚፈጠረውን ነገር ስለማውቅ አልፈረድኩባትም፡፡ ጨዋታ ያለ ቀን ገና በጠዋቱ አጠገቤ ቆም ይልና…”መላ’ዬ …ጨዋታው 3 ከ 45 ይጀምራል። ከዚያ በፊት ሃይላይት አለ። ወደ አምስት ሰዓት አካባቢ ያልቃል። እንደጨረስኩ ወዲያው እመጣለሁ።” ይላል። ማስፈቀዱ ነው፡፡ ዝም እላለሁ።ቆሞ ያየኛል።ዝም እላለሁ። አይሄድም፡፡ እኔ ጥዬው እሄዳለሁ። አንዳንዴ የሆነ ልቡን ስልብ አድርጎ ራሱን የሚያስተው ነገር አለ፡፡ ሲጨነቅ ወይም ሲበሳጭ እንዲያ ይሆናል፡፡ አርሰናል የተሸነፈ’ለት ታዲያ ብዙ ጊዜ ያ ህመም ይነሳበታል፡፡ ቤት እንደገባ በዚያ ቁመቱ ሶፋ ላይ ዧ ብሎ ይወድቃል፡፡ ጸጥ ነው የሚለው፡፡ አንዳንዴ ሞተ ብለን የምንጮህበት ቀን አለ።ውሃም ጸበልም ደፋፍተንበት ነፍስ ከዘራ በኋላ “ደህና ነኝ እኮ” ሲል ደግሞ የኔ ንዴት በተራው አናቴ ላይ ይወጣል። “አንተ በማይረባ ኳስ እየመጣህ ትዘረጋለህና እኛ መጨነቅ አለብን?” ብዬ እጮህበታለሁ፡፡ መልስ አይሰጠኝም፡፡ሌላ ቀንም እንዲሁ ይሆናል፡፡ የሆኑ ከሌላ ሰፈር የሚመጡ የጊዮርጊስ ይሁኑ የማንቺስተር ደጋፊዎች እሱን ሁሌም እንደተቃረኑት ነበር። ኳስ የሚያዩት አብረው መሰለኝ ፡፡ ጨዋታ ያለ ቀን ታዲያ...ብዙ ጊዜ እኩለ ሌሊት ከእንቅልፌ የሚያባንነኝ በራችን አቅራቢያ የምሰማው የብዙ ልጆች ዘፈን የሚመስል ጫጫታ ነበር። እኛ ቤት በር ላይ አርሰናልን የሚሳደብ ዘፈን ከሰማሁ በቃ ነገር አለ ማለት ነው !። ፍቄን ለማብሸቅ የሚዘፈን ዘፈን መሆኑን አውቃለሁ። ልጆቹ የሚሉት ነገር አይገባኝም። ግን ሁለቱ ቡድኖች ከማንም ጋር ይጫወቱ ብቻ አርሰናል ከተሸነፈ ወይም ማንቺስተር ካሸነፈ እሱን ለማብሸቅ እኩለ ሌሊት በራችን ላይ ይመጡና ይጨፍራሉ። አንድ ቀን ከነሱ ጋር ሲደባደብ ፖሊሶች ደረሱና ብዙዎቹን ያዟቸው፡፡ እሱንም ይዘውት መኪና ላይ ከጫኑት በኋላ የኔ ወንድም መሆኑን ሲነግራቸው ደውለው ጠርተውኝ ፊቴ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥተው ለቀቁት፡፡ ለእማዬ ብዬ እንጂ እስር ቤትን ትንሽ ቢቀምሳት ቅር አይለኝም ነበር፡፡ እሱ የሚደግፈው ቡድን ያሸነፈ’ለት ደግሞ ታሪክ ይገለበጣል፡፡እማዬ ይህንን ስትሰማ ወደሰማይ እያንጋጠጠች “ዛሬስ ተክለሃይማኖት ገላገሉኝ !” ትላለች። የዚያን ቀን ታዲያ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ አይወስደውም። ብቻውን ይስቃል። አልጋው ራስጌ ፎቷቸውን የሰቀለውን ማንነታቸውን የማላውቃቸውን ተጨዋቾች በተኛበት አንጋጦ ያያቸዋል፡፡ ጸጥ ባለው ሌሊት ድንገት ይነሳና “ይሄ የተረገመ ልጅ! ሰራላቸው እኮ!” ብሎ በሳቅ ፍርስ ይላል። አንዳንዴ ዝም ብዬ ሳየው ጤነኛ ሁሉ አይመስለኝም ነበር ።እማዬ ግን “ተወው ልጅ አይደል? ብቻ አይመመው እንጂ ሲለፈልፍ ቢያድር እኔ ምን ቸገረኝ…ሲያድግ ይተወዋል” ትላለች፡፡ ፍቄ ገና በ21 ዓመቱ አንድ እሁድ ቀን ድንገት ራሱን ስቶ ወደቀ፡፡ ሆስፒታል በገባ በሶስተኛ ቀኑ …እኛንም የሚወዳቸውን ቡናና አርሰናልንም ሳይሰናበት በዚያው ሄደ። የቀብሩ ዕለት የነበረው ህዝብ ብዛት እስካሁን ሳስበውም ይገርመኛል። በዚያ እድሜው ትምህርቱን ትቶ በሚሰራው ስራ የሚያገኘውን ደመወዝ ሁሉ የሰፈር አቅመደካሞችን ፣ ልጅ ያላቸው የኔ ቢጤዎችን ወዘተ በቋሚነት ይረዳበት እንደነበር ያወቅኩት የለቅሶው ሰሞን ሰዎች ስለርሱ ሲያወሩ በሰማኋቸው ታሪኮች ነው፡፡ በስሙ ትልቅ የእግር ኳስ ግጥሚያ ተዘጋጅቶለትም ነበር፡፡ የዋንጫው ቀን አሸናፊውን ቡድን ስሸልም ስሜቴን መቆጣጠር አቅቶኝ ነበር ፡፡ አሁንም ታዲያ ኳስ በሚታይባቸው ቤቶች በኩል ሳልፍ የደጋፊዎችን ጩኸት ስሰማ ፊቴ ላይ ድቅን የሚልብኝ አሱ ነው ። ምን ያደርጋል ያንን ምድር የማይበቃው የሚመስል ዋልያ …ያች ቀዝቃዛ ቀን እንደዋዛ ይዛው ሄደች....የርሱ መጉደል በቤታችን ይዞት የመጣው ከባድ ሃዘን እናቴን ህመምተኛ አድርጓት ኖሯል፡፡ ባሰብኩት ቁጥር የሚናፍቀኝ ከፊቱ የማይጠፋው ፈገግታ ነው፡፡ ፍቄ ወንድሜ ! ….ነፍስህ በሰላም ትረፍ !! By Melaku Berhanu @wegoch @wegoch @paappii

የማባልጋት ባለትዳር ነበረች ። ዋና ተግባራችን ወሲብ ነው ። የምንቀጣጠረው ለወሲብ ብቻ ነው ። የምናወራው ስለ ወሲብ ነው ። አንዳችን አንዳችንን የምንፈልገው ወሲብ ሲያምረን ነው ። አጠገቤ ሆና ባሏ ደውሎ ያውቃል: "ሰውዬሽ ደወለ" ብዬ ስልኳን አቀብያት አቃለሁ ። ምንም እንዳልተፈጠረ ስታወራው እርቃኗን አትመስልም ነበር። ይገርመኛል ድድብናችን ። ነውራችን ስለተደጋገመ ተግባራችን ብልግና መሆኑ ተሰወረብን ። ቢሮዋ እሄዳለሁ፣ ቢሮዬ ትመጣለች ። ጓደኛዬ ቤት፣ እኔ ቤት፣ የሆነ ኮስመን ያለ ሰዋራ ቦታ ፣የሆነ ድብቅ ፅድት ያለ ስፍራ ፣ መኪና ውስጥ ... ብዙ ብዙ ቦታ ትመጣለች እንዋሰባለን ። የታሪካችን መነሻ እና መድረሻው ወሲብ ነው ። አንድ ቀን በደነገጠ: ተስፋ በቆረጠ ድምፅ "ባሌ አወቀብን" አለችኝ .....ደነገጥኩ ። ጠፋሁኝ ...ጠፋች ከአስራ ሰባት ቀን በኋላ ጓደኞቼ "ገኒ ሃዘን ላይ ነች፣ ሙሉ ከላይ እሰከታች ጥቁር ለብሳለች፣ ከስታለች" አሉኝ "ምን ሆነች?" አልኩ "ባሏ ሞቶባት ነው፤ ራሱን አጥፍቶ ነው የሞተው" አሉ። ስደነግጥ፣ ፊቴ ሲቀያየር ፣ እምባዬ ሲያመልጠኝ አዝኜለት ነው የመሰላቸው ። እኔ እንደገደልኩት አልጠረጠሩም ። የጥፋተኝነት ስሜት ሊገለኝ ሲል ማምለጫ መፅሃፍ ቅዱስ ገለጥኩ። "ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳል " የሚለው ከሁሉም ጎልቶ ተነበበኝ ። .. ሰው ይዞ መውደቅ ፤ ማስተካከል የማይቻል አወዳደቅ ፣ ሲያስታውሱት የሚያስነክስ አይነት አወዳደቅ፣ እነሳለሁ የማይሉት አወዳደቅ ፣ ወድቄ ነበር የማይሉት አወዳደቅ። በግዜ ምክንያት የማይደበዘዝ አወዳደቅ ... እንደዚህ አይነት መውደቅ ሲ..ያ...ስ..ጠ..ላ !! ! By Adhanom Mitiku @wegoch @wegoch @paappii

እውነት ሁሉም ነገር 'upgrade' ያረጋል! ህይወት፣ ኑሮው፣ ሳሩ፣ ቅጠሉ፣ ሰፈሩ፣ መንደሩ፣ ሰዉ ሁሉ  'upgrade' ያረጋል! እብድ ነው። ከሰፈሬ ሁለት አቋራጭ ራቅ ብሎ የሚኖር። በልጅነቴ ወደትምህርት ቤት ስሄድ ነው ማየው።  በጫት ገረባ የተሞላው አፉ፣ ያገኘውን ከብስኩት ልጣጭ እስከ አፉን እስካስጌጠባት ገረባ ድረስ እጁ ለመያዝ ከልካይ የለውም። በተለይም ከተማውን በእርቃኑ ማካለሉ የሱ ትልቁ መለያ ነው። ወንዱን ሴቱን አዛውንት ጨቅላ ሳይለይ ያለከልካይ  ያስኮመኩመናል።  ወንዶቹ በሱ ባዶ ገላነት ደስተኛ እንዳልሆኑ አውቃለው (እኔስ እንደው ልጅ ነኝ)  ይህ ነገራቸው ለሱ ከማዘን የመነጨ ሳይሆን በእንትኑ ምክንያት ነው። ረዥም ነው ከረዥምም ረዥም። በምን ይሉኛል ብሂል  አቀርቅሮ  ከማለፍና በእጆቻቸው አይናቸውን ከመከለል በዘለለ ለአፍታ እንኳ ቢሆን ድንገት በእይታ ይህንን በረከት የተቋደሱ ሴቶች የከተማውን ወንድ በዛ ልክ ይጠብቁታል የሚለው ስጋት እንጂ።  ጊዜያት ነጎዱ። እኔም አደኩ ወደ ወንዶቹ ጎራ። ከብዙ ጊዜያት በኋላ ያንን እብድ አየሁት። ተለውጧል። መላ መላውን የማውቀው  አሁን ላይ ከላይ እስከታች ታጥቋል። ቲሸርት ሱሪ አልቀረው። ከአንዴም ሁለቴ ለብሶ  አየሁት። ያ በእጁ የሚይዛት በአፉ የሚያጣጥማት ገረባው ግን አሁንም የሱ ነች። upgrade መሆኑ ነው። ወንድ ነኝ ያልኩት እኔ እራሴን አየሁት። በዘመኑ ኑሮና ህይወት እየተራቆትኩኝ ነው። የፊተኞች ኋለኞች የኋለኞች ፊተኞች ነው መሰል ነገሩ። እኔንስ የሚያሳስበኝ  ግን እንደው ውል ብሎኝ ብራቆትስ? በብዙ እብዶች መሀል ያለው አንድ ጤነኛ ነኝ ሚሉትን ቅኔ ብቀኝስ? የኔውን እንደሆነ በማይዳሰሱ ቅርፆች UNESCO ላይ አስመዝግቤዋለው። የከተማው ወንዶች ነን ባዮችንስ አስገምት ይሆን?  አቤ...ት! በሰላም ማይታበድባት ሀገር ... By 乃丨丂尺卂ㄒ @wegoch @wegoch @paappii

አስፈሪወቹ ሌሊቶች! የሆነ ጊዜ የሚከራይ ቤት ስፈልግ አንድ ክልፍልፍ ደላላ "ግራውንድ ፕላስ 2 " ቪላ አጠገብ ያለች ቆንጆ የብሎኬት ቤት አሳየኝ። ለታክሲ ቅርብ፣ ፅድት ያለች በዚያ ላይ ዋጋዋ የማይታመን ርካሽ! ቤት። እድሌን አመስግኘ ወዲያው ተስማማሁ። መስኮቷን ስከፍት ፊት ለፊት የተንጣለለው ውብ ቤት ይታየኛል። መሀል አዲስ አበባ እንደዛ ሰፊ ግቢ ውብ ህንፃ...ዙሪያውን ያለ ደካማ መንደርተኛ እያየሁ "ወይ አዲስ አባባ የኑሮ ልዮነት..." እያልኩ እሁድ ገብቸ እስከማክሰኞ አለሜን ቀጨሁ። ማክሰኞ እኩለ ሌሊት አካባቢ ነበር ድንገት ከአልጋየ የሚያነጥር ድምፅ እንደሰፌድ ቆሎ አንቀርቅቦ ያስነሳኝ። መድፍ ነበር የመሰለኝ። ደንግጨ ብነሳ ሀድራው ደርቷል ጭብጨባው፣ ጉሪያው፣ ከበሮው.... ሌላ ነገር ነው። በተለይ ከበሮው የአደዋ ዘማችን ነጋሪት ያስንቃል...ይነዝራል! ድዝዝ ድዝዝ ድዝዝ ... ጨብ ጨብ ጨብ እሰይ እስይ እሰይ እሰይ ሁርርርርር፣ ሁይይይ፣ አሀይ ..... እህህህህህህ ! ግርጭው ብርጭው አፍከኸከት ግራጭገት አጉዛራ ቀወዢራ ጆቢጃራ እሁይይይይ ....ደግሞ በጎች በመሀል ይጮሃሉ! ባኣኣኣኣ! ዜማውን ሁሉ እስካሁን አስታውሰዋለሁ። መስኮቴን በቀስታ ከፍቸ ባጮልቅ ያ ቪላ ቤት ዙሪያውን በቆሙ የቤት መኪኖች ተጥለቅልቆ ሰፈሩ በከርቤ ጭስ ታፍኗል። በሩ ላይ ነጠላ ያደገደጉ ሰወች ቁመዋል፣ መብራቱ ፀሐይ ይመስላል። እንዳለ በሩ ቄጤማ ተጎዝጉዞበታል። ህልም ነበር የሚመስለው። በኋላ ስሰማ የታዋቂ ጠንቋይ ቤት ሆኖ ተገኘ። የተከራየሁት ቤት ለሰባት ወር ባዶውን እንደከረመ አንዲት ያለሁበት ግቢ ልብስ የምታጥብ ልጅ ነገረችኝ። ድምጿን ቀንሳ በፍርሃት "ጥሩ አይደለም የገባው ሁሉ ተጥመልምሎ ነው የሚወጣው ቶሎ ልቀቅ ይሄን ቤት...ከአንተ በፊት ተከራይቶ የነበረው ልጅ፣ ሌሊት አያለሁ ብሎ በመስኮት ብቅ ሲል አፉ ወደግራ አፍንጫው ወደቀኝ ተጠነጋግሮ እግሩም ተጥመልምሎ ቁጭ! " አለችኝ....። አንች ለምን አልተጥመለመልሽም ልላት ፈልጌ ከአፌ መለስኩት። ውስጤ ቢፈራም "ሳለ መድሃኒያለም ለጠንቋይማ ርስቴን አለቅም" ብየ ጧት ጧት አፌና አፍንጫየ አለመጣመሙን በእጀ እየዳሰስኩ መኖሬን ቀጠልኩ። አንድ ቀን ጧት ቁርሴን ስበላ በአጋጣሚ ወደአፌ የላኩት ማንኪያ አፌን ሳተው። የደነገጥኩት መደንገጥ። መስተዋት ፊት ቁሜ ሳይግን አልተጣመምኩም። ነፍሴ መለስ አለች። እና ማክሰኞና ሐሙስ "ላይቭ ባንድ በሚያቀርበው ጭፈራ እየተዝናናሁ መኖር አዝናኝ ሆነልኝ። አንድ ሐሙስ እንደውም ፀጥ ብሎብኝ ማዛጋት ጀምሮኝ ማንን ልጠይቅ ስል? ያችው ልብስ አጣቢ "ግንቦት ገባ፣ በዚህ ወር ሁልጊዜ ሰውየው የሆነ ቦታ ስለሚሄድ ሰላም እናድራለን" አለችኝ። እውነትም ጠንቋዮ ሙሉ ግንቦትን ጠፍቶ ሰኔ ላይ ተመለሰ። ሰፈሩም ትንሽ ዘና ብሎ ከረመ። በሳምንትም በወርም ከመንደርተኛው አንዱ ጠንቋዮን የተሳፈጠ ይጣመማል የሚል ወሬ ስለነበር እነዛ ሌሊቶች አስጨናቂ ነበሩ። ጠንቋይ እንዲህ ተፈሪ መሆኑን ያኔ ነው ያወኩት። በሹክሹክታ በሚደርሰን ስጋት ብዙ አስፈሪ ሌሊቶች የምናሳልፍ ህዝቦች ነን። እንግዲህ በሳምንት ሁለት ቀን ማክሰኞና ሐሙስ ሌሊት እንዲቹ ሲቀወጥ ያድራል። የገረመኝ ይሄ አይደለም! ብዙ ባለሀብትና ታዋቂ ሰው የሚሰግድለትን፣ ስንቱን ሐብት በሐብት ያደረገ ነው የሚባለው ይሄ ጠንቋይ ለማየት ስመኝ አንድ ቀን በሁለት ሰወች ታጅቦ ሲወጣ አየሁት! ...(ጠንቋይ ከዛ በፊት አይቸ ስለማላውቅ ፤ የሆነ ፍጥረት ነበር የጠበኩት) ....ምን ገጠመኝ? መናኛ ሙሉ ልብስ ለብሶና ከዘራውን ይዞ የሚያዘግም ሽማግሌ። ያችው ወሬ ወዳድ ልብስ አጣቢ እየተጣደፈች መጥታ ነበር "ወጣልህ ና እየው" ያለችኝ። ...እና ምን አለችኝ? "ጡረታውን ሊቀበል እየሄደኮ ነው" ጡረታ? "አወ ...ወታደር ነበር...ቢሞት ጡረታውን አያሳልፍም ከቤት የሚወጣውም በዚቹ ቀን ነው" 😀 @wegoch @wegoch @paappii