uz
Feedback
HOP Ministry

HOP Ministry

Kanalga Telegram’da o‘tish

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
560
Obunachilar
+324 soatlar
+217 kun
+5530 kun
Postlar arxiv
#መንፈሳዊ_ግለትን_መጠበቅ! በተለምዶ ቀዝቃዛ ውሃ ወደ መፍላት የሚደርሰው የሚያገኘው ሙቀት እየጨመረ በሄደበት ልክ ነው። ቀዝቃዛ የነበረው ውሃ እሳት ሲያገኝ ለብ እያለ፣ እየሞቀ፣ እየሞቀ፣....እየሞቀ፣.....እየጋለ፣ ወደ መፍላት ይደርሳል። በተቃራኒው ደግሞ የፈላው ውሃም የሚቀዘቅዘው በአንድ ጊዜ ሳይሆን በጊዜ ሂደት ውስጥ ነው፤ ትኩሳትና ሙቀቱ እየቀነሰ፣ ለብ እያለ፣ በረድ እያለ፣ ወደ መቀዝቀዝ ይደርሳል። በሁለቱም ሂደት ውስጥ የሙቀቱ መጠን መለዋወጥ ነው የውሃውን ሁኔታ የሚወስነው። ማለትም የውሃው የሙቀት መጠን መጨመር ወይም መቀነስ፣ መውጣት ወይም መውረድ ውሃው በሚያገኘው የሙቀት መጠን ላይ ይወሰናል። መንፈሳዊ ሕይወታችንም ልክ እንደዚሁ የውሃ ምሳሌ ሲዋዥቅ እናስተውላለን። በምድር እስካለን ድረስ ላይ ወጥቶ የሚቀር መንፈሳዊ ሕይወት እንደሌለ ሁሉ ታች ወርዶ የሚቀርም የለም። ነገር ግን መንፈሳዊ ግለታችንን መጠበቅ የእኛ ድርሻ ነው። መንፈሳዊ ሕይወታችን እንዲጎለብት፣ ብስለት እንዲኖረን፣ በመንፈስ የጋልን እንድንሆን ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት ካልቆየን፣ የእግዚአብሔርን ቃል ካላጠናን፣ ካልጸለይን፣ በመንፈስ ቅዱስ ካልተሞላን፣ ከቅዱሳን ጋር ሕብረት ካላደረግን፣....... በአጠቃላይ በመንፈሳዊው ነገር ላይ #አተኩረን ዕለት ተዕለት መንፈሳችንን ካልመገብን፣ የውስጥ ሰውነታችንን ካላጠነከርን እያሽቆለቆልን ሄደን ለብታ ላይ መድረሳችን፣ መንፈሳዊ ሕይወታችንም ቀዝቃዛና በራድ መሆኑ #አይቀሬ! ነው። ስለዚህ መንፈሳዊ ግለታችንን አስጠብቆ ለመንቀሳቀስ የሕይወታችን ባለአደራ እንዲሁም መጋቢ ነን ማለት ነው። እኛ ያልሰራንበት፣ ያልመገብነው ሕይወታችን ከየትም መጥቶ እንደምንናፍቀው፣ እንደሚጠበቅበት ሊያድግና ሊያፈራ አይችልምና ዘወትር ራሳችን ላይ ለመስራት እንበርታ!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 23, 2024 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

Lauren_Daigle_-_Once_And_For_All__Audio_(128k).m4a3.92 MB

Once and for All Song by Lauren Daigle ‧ 2015 "God I give You all I can today These scattered ashes that I hid away I lay them all at Your feet From the corners of my deepest shame The empty places where I've worn Your name Show me the love I say I believe Oh Help me to lay it down Oh Lord I lay it down Oh let this be where I die My lord with thee crucified Be lifted high as my Kingdom's fall Once and for all, once and for all There is victory in my Saviors loss And In the crimson flowing from the cross Pour over me, pour over me yes Oh let this be where I die My lord with thee crucified Be lifted high as my Kingdom's fall Once and for all, once and for all Oh Lord I lay it down Oh Lord I lay it down Help me to lay it down Oh Lord I lay it down Oh let this be where I die My Lord with thee crucified Be lifted high as my Kingdom's fall Once and for all Once and for all Oh once and for all Once and for all"

Track-01-ትሁን-ፈቃድህ-Bereket-Lemma-Tihun-Fekadh.m4a5.61 MB

የእግዚአብሔር አብሮነት የሌለበት ከነዓን አይረባንም። አብሮነቱ በሌለበት ከሚሰጠን ከነዓን ይልቅ፤ ሁሉን አጥተን እግዚአብሔርን ማግኘት፣ በእርሱም መገኘት ይብዛልን!! 🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. https://t.me/hopministry10

#የእግዚአብሔር_አብሮነት_ከከነዓን_ይበልጣል። የእግዚአብሔር አብሮነት ከከነዓን ይበልጣል። ለእግዚአብሔር ሕዝብ፦ የእግዚአብሔር አብሮነት የሌለበት ከነዓን ሕይወት አይሆነውም፣ አይረባውም። የእግዚአብሔር ሕዝብ ልዩነትና ሞገስ፦ ያለው ሀብት፣ በረከት፣ የሚወርሰው ከነዓን ሳይሆን፤ ሁሉን ሰጪው፣ የባርኮቱ ምንጭ የሆነው አምላኩ እግዚአብሔር ነው። የእግዚአብሔር አብሮነት የሌለበት ከነዓን አይረባንም። አብሮነቱ በሌለበት ከሚሰጠን ከነዓን ይልቅ፤ ሁሉን አጥተን እግዚአብሔርን ማግኘት፣ በእርሱም መገኘት ይብዛልን!! ከእግዚአብሔር ሀልዎት ውጪ እኛን ሕያው፣ ልዩ፣ ባለ ሞገስ የእግዚአብሔር ሕዝብ የሚያደርገን ምን አለ? ዘጸአት 33 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁴ እግዚአብሔር (ያህዌ) “ሀልዎቴ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ ዕረፍትም እሰጥሃለሁ” ብሎ መለሰ። ¹⁵ ከዚያም ሙሴ እንዲህ አለው፤ “ሀልዎትህ ከእኛ ጋር ካልሄደ ከዚህ አትስደደን። ¹⁶ አንተ ከእኛ ጋር ካልሄድህ፣ አንተ በእኔና በሕዝብህ መደሰትህን ሌላው እንዴት ያውቃል? እኔንና ሕዝብህንስ በገጸ ምድር ከሚገኙት ከሌሎቹ ሕዝቦች ሁሉ ልዩ የሚያደርገን ሌላ ምን አለ?” ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 21, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

So Will I (100 Billion X) Song by Hillsong Worship and Taya ‧ 2018 "God of creation There at the start Before the beginning of time With no point of reference You spoke to the dark And fleshed out the wonder of light And as You speak A hundred billion galaxies are born In the vapour of Your breath the planets form If the stars were made to worship so will I I can see Your heart in everything You've made Every burning star A signal fire of grace If creation sings Your praises so will I God of Your promise You don't speak in vain No syllable empty or void For once You have spoken All nature and science Follow the sound of Your voice And as You speak A hundred billion creatures catch Your breath Evolving in pursuit of what You said If it all reveals Your nature so will I I can see Your heart in everything You say Every painted sky A canvas of Your grace If creation still obeys You so will I So will I If the stars were made to worship so will I If the mountains bow in reverence so will I If the oceans roar Your greatness so will I For if everything exists to lift You high so will I If the wind goes where You send it so will I If the rocks cry out in silence so will I If the sum of all our praises still falls shy Then we'll sing again a hundred billion times God of salvation You chased down my heart Through all of my failure and pride On a hill You created The light of the world Abandoned in darkness to die And as You speak A hundred billion failures diappear Where You lost Your life so I could find it here If You left the grave behind You so will I I can see Your heart in everything You've done Every part designed in a work of art called love If You gladly chose surrender so will I I can see Your heart Eight billion different ways Every precious one A child You died to save If You gave Your life to love them so will I Like You would again a hundred billion times But what measure could amount to Your desire You're the One who never leaves the one behind"

"And as You speak A hundred billion failures diappear Where You lost Your life so I could find it here If You left the grave behind You so will I I can see Your heart in everything You've done Every part designed in a work of art called love If You gladly chose surrender so will I"

4_5870647052936942063.mp35.48 MB

#ኢየሱስ_ማን_መሆኑን_በቅጡ_ማወቅ! ብዙ ነገሮች አጥተን ኖረን አይተነዋል፤ ብዙ ነገሮች ጥለውን ሄደው ስንቀጥል ራሳችንን አግኝተናል። ጌታ ኢየሱስን ላየ፣ ቸርነቱን ለቀመሰ ሰው ግን ከኢየሱስ መለየት፣ ያለ እርሱም መኖር ሞት ነው። የኢየሱስ ሁሉ በሁሉነት ሲገባን የሚያስፈልገን እርሱ ብቻ እንደሆነ፤ ያለ እርሱ መኖር፣ ምንም ማድረግ እንደማንችል እንረዳለን። ኢየሱስ ከያዕቆብ ጉድጓድ መብለጡ የእውነት ለገባው ሰው ኢየሱስ ጊዜያዊ ጥምን የሚያረካ ነገር ሳይሆን የዘላለም ውኃ ምንጭ፣ የሕይወት ውኃ ነው። ኢየሱስ ማን መሆኑን ማወቅ የዘላለም ሕይወትን ማትረፍ ነው። ያውም ትርፉ በምድር ስሌት የማይሰላ ዘላለማዊ ትርፍ ነው። ሳምራዊቷ ሴት ኢየሱስ ማን መሆኑን በቅጡ ሳትረዳ በፊት የያዕቆብ ጉድጓድ የምታዜምለት፣ ታላቅነቱን የምትመሰክርለት፣ ከእርሱ ሌላ ምንጭ ያለ እንኳ እስካይመስላት ድረስ የምትመካበት ምንጯ ነበር። የኢየሱስ የዘላለም ውኃ ምንጭነት ሲገባት ግን አይደለም ደግማ ስለ ያዕቆብ ጉድጓድ ልታወራ፣ "አንተ ይህን ጉድጓድ ከሰጠን ከአባታችን ከያዕቆብ ትበልጣለህን?" ብላ ኢየሱስን ከያዕቆብ ጋር ልታወዳድር ይቅርና ስለ ኢየሱስ የዘላለም ውኃ ምንጭነት መለስ ብላ ለማሰብና ለመጠራጠር እንኳ ጊዜ አላገኘችም። ለእርሷ የበራላት ብርሃን ለብዙዎች እንዲበራ፣ ያየችውን ብዙዎች እንዲያዩት፣ የገባትንና የቀመሰችውን እውነት፣ ሕይወት ብዙዎች እንዲቀምሱ፣ ብዙዎችን ወደ እርሱ ልታፈልስ ወደ ሕዝቡ ሮጠች፤ እርሱ ማን መሆኑን አውቃለችና። ኢየሱስ ማን መሆኑን በቅጡ ማወቅ፦ ከብዙ ብክነት፣ በአላስፈላጊ፣ በሰው ሰራሽ፣ ጥምን በማይቆርጡ፣ በጥቃቅን ምንጮች ከመርካት ይጠብቃል፤ እርሱን ብቻ ለመጠማት፣ ከእርሱ ብቻ ለመጠጣት፣ በእርሱ ብቻ ለመርካት ይጠቅማል። ኢየሱስን በማንነቱ ማወቅ፣ እርሱ ማን መሆኑን በቅጡ መረዳት፣ ማስተዋል ይሁንልን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 19, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

Amazing_worship_ህልውና_yosefe_almerew_with_kalkidan128k.m4a9.50 MB

ዘምሬ_የማልጠግበው_zemre_yemaltegbew_ይድነቃቸው_ተካ_Yidnekachew_teka_መዝሙር128k.m4a5.40 MB

#የማያልቅ_ርዕሰ_ጉዳይ! በምድር ስላሉት ጉዳዮቻችን፣ ስለምንፈልጋቸውና ስለሚያስፈልጉን ነገሮች የምንጸልየው ፀሎት በፀሎት መልስ ይሻራል። መልሳችንን ስንቀበል፣ የጠየቅነውን ነገር ስናገኝ ፀሎቱን እንተወዋለን፣ እንቀይረዋለን። ስለ ራሱ ስለ እግዚአብሔር፣ ስለ መገኘቱ፣ ስለ ሕልውናው፣ ስለ መንፈሱ የሚደረግ ፀሎት ግን ጊዜ የማይሽረው፤ አሁንም፣ ዛሬም፣ ነገም፣ ከነገ በስቲያ፣ በምድር እስካለን ድረስ፣ ጌታን ፊት ለፊት እስከምናየው ድረስ የሚዘልቅ፣ መዝለቅ ያለበት ፀሎት ነው። በጊዜያዊ ነገሮች ላይ የፀና ፀሎት እንደተቀያየረ፣ እንደዋዥቀ ይኖራል፤ ድካም አለበት፣ ጉልበትን ያዝላል። ዘላለማዊውን ነገር፣ ዘላለማዊውን አምላክ ለማግኘት የሚደረግ መቃተት ግን ሕይወት አለበት፤ ጸላዩን፣ ፈላጊውን ሕያው እያደረገ፣ እያለመለመ ይሄዳል፤ በቃኝም አይባልም ሌላ እልፍ ረሃብ ይወልዳል። ጌታ በቸር እጆቹ ይንካን፤ ቸር መሆኑን ያቅምሰን፤ ያኔ እያየነው፣ እያገኘነው፣ በእርሱ እየተዳሰስንና እየተነካን፦ የያዝነው አይመስለንም፣ አብረነው ሆነን ይናፍቀናል፣ የእርሱ እልፍ ረሃብ ይበዛልናል፣ ጌታን ጌታን ብለን እየናፈቅነው፣  እያገኘነው ይርበናል፣ ይርበናል....፣ እርሱን መከተል፣ መከታተል ስራችን ይሆናል። ከምንፈልገው፣ ከሚያስፈልጉንም ነገሮች በላይ እግዚአብሔር፣ መንፈስ ቅዱስ፣ ኢየሱስ ያስፈልገናል። እግዚአብሔርን እየፈለግን መፈለግ፣ እየናፈቅን መናፈቅ ይሁንልን!! የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር የምትመረምረው መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሙላን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 18, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

ከምንፈልገው፣ ከሚያስፈልጉንም ነገሮች በላይ እግዚአብሔር፣ መንፈስ ቅዱስ፣ ኢየሱስ ያስፈልገናል። እግዚአብሔርን እየፈለግን መፈለግ፣ እየናፈቅን መናፈቅ ይሁንልን!! 🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. https://t.me/hopministry10

ሌሎች ረሃቦቻችንን ሁሉ ተቀምተን #በአንድ_ረሃብ (በእግዚአብሔር ብቻ) ብንጠመድ፣ ሌላውን ለማየት፣ ለመስማት፣ ለመንካት፣ ለመብላት አቅም አጥተን ለሕይወት ቃል፣ ለሕይወት ውሃ፣ ለሕይወት ውሃ ምንጭ ረሃብ፣ ጥማት ብንበረታ፤ የጌታ የፍቅሩ ትኩሳት የልባችንን ጓዳ ቢያሞቀው፣ ለብታችን በፍቅሩ እሳት ግለት ቢሻር፣ ትናንት ባላየነው መንገድ ጌታ ቢያገኘን፣ መሰዊያችን ቢታደስ፣ ከማለዳ እስከ ምሽት የቃሉ አሰላስሎት አሳባችንን ቢቆጣጠረው፣ ማብቂያዋ መቼ እንደሆነ የማይታወቀው እንፋሎት ዘመናችን ለኢየሱስ እየነደደች የምታበራ መብራት ብትሆን.....ይሄ ሁሉ ልቤ የሚብሰለሰልበት፣ ጌታ በኃይሉ ችሎት ቢያደርግልን ብዬ የምናፍቀው ናፍቆቴ፣ ቁጭቴ ነው። ናፍቆቴን እንደምትጋሩኝ እምነቴ ነው፤ ይህ ሁሉ በእኛ እውን እንዲሆን የመንፈስ ቅዱስ ጉብኝት ያግኘን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 April 12, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. https://t.me/hopministry10

Addisu_Worku_(Alechenekem)(128k).mp34.81 MB

እግዚአብሔርን አምነን፣ ታምነን በመንገዱ ላይ እየሄድን ከሆነ፦ እርሱ አላዘገየንም፣ አላስቸኮለንም፤ እርሱ ሁሉን በፈቃዱ ምክር መሰረት እየሰራ ይገኛል። ረፈደብኝ፣ ወደኋላ ቀረሁ፤ መፍጠን ከሚገባኝ በላይ ፈጥኜ በአላስፈላጊ መንገድ ተጓዝኹ አንበል። እግዚአብሔር ብቻውን መምራት፣ ከግብ ማድረስም ያውቅበታልና ሕይወታችንን በመሪያችን እጅ ላይ በእምነት እናኑር፤ እግዚአብሔርን አምነን፣ ሳናይ እንከተለው፣ እንከታተለው። በእግዚአብሔር መንገድ ፀንተን አንጸጸትም፤ እርሱ ያሳርፈናል!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 16, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. በእግዚአብሔር መንገድ ፀንተን አንጸጸትም፤ እርሱ ያሳርፈናል!! https://t.me/hopministry10

““እናንት ሸክም የከበዳችሁና የደከማችሁ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም ዕረፍት እሰጣችኋለሁ።”   — ማቴዎስ 11፥28 (አዲሱ መ.ት) “እርሱ ስለ እናንተ ስለሚያስብ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።”   — 1ኛ ጴጥሮስ 5፥7 (አዲሱ መ.ት) #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional