HOP Ministry
الذهاب إلى القناة على Telegram
HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
445
المشتركون
+224 ساعات
+237 أيام
+6630 أيام
أرشيف المشاركات
446
+5
#ኢየሱስ_ይወደናል!!
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10
446
#እኔ_ምስክር_ነኝ!
የእኔ ማንነት፣ የኋላ ታሪኬ፣ ባህሪዬ ታይቶ እና ሚዛን ላይ ተቀምጦ ቢሆን እግዚአብሔር እኔን የመረጠኝ፦ ከክብሩ የጎደልኹ፣ ለመንግሥቱ የማልበቃ፣ ከእግዚአብሔር ሕይወት የተለየሁ፣ ከሙታን መካከል አንዷ ነበርኹ።
ነገር ግን በበደሌ እና በኃጢአቴ ሙት በነበርኹ ጊዜ እግዚአብሔር ከወደደኝ ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣ ከክርስቶስ ጋር ሕይወትን ሰጠኝ፤ በእኔ ሥራ ሳይሆን በጸጋው አዳነኝ፣ የመንግሥቱ ወራሽ አደረገኝ።
እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን እንደሚወድ፤ በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ በኩልም ቀርቦ እንደሚታረቃቸው፤ ዳግም ልደት ሰጥቶ አዲስ ፍጥረት እንደሚያደርጋቸው፤ ኃጢአት፣ በደል፣ መተላለፋቸውን ሁሉ በልጁ በኢየሱስ ደም እንደሚያነጻ፣ ልጆቹ እንደሚያደርጋቸው እኔ ማሳያ ነኝ፣ እኔ ምስክር ነኝ።
ዛሬ፣ ጌታ ፈቅዶ በሚጨምርልኝም ቀሪ እድሜ ጸጋው ቢበዛልኝና መንፈሱ ቢያግዘኝ የምተጋው፦ እንዲህ ለወደደኝ ኢየሱስ ታማኝ አፍቃሪው ለመሆን፣ ሞቴን ለሞተልኝ ኢየሱስ ሕይወቱን ልኖርለት ነው።
#ኢየሱስ_ይወደናል!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 19, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
#እንደራሴ እንደራሴነቱ ለወከለው አካል እንጂ ለራሱ እና ለግል ጉዳዩ አይደለም።
እንደራሴ በላኪው፣ በውክልና ሰጪው ቦታ ሆኖ እርሱ ቢሆን የሚያደርገውን ሁሉ ያደርጋል።
የእንደራሴ ስራና ሀላፊነቱን በአግባቡ መወጣቱ በወካዩ (በላኪው) አካል ይገመገማል።
አንድ እንደራሴ (አምባሳደር) አገሩን እና የአገሩን መንግሥት ወክሎ ወደ ሌላ አገር ሲሄድ፣ በዚያ በሚኖረው ቆይታ የላከውን መንግሥት ሳይሆን የራሱን አጀንዳ ሲያስፈጽም ቢሰነብት፣ ላኪውንም ባይወክል እንደራሴነቱ (አምባሳደርነቱ) ምን ላይ ነው?
2ኛ ቆሮንቶስ 5 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁸ ይህ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፤ እርሱ በክርስቶስ አማካይነት ከራሱ ጋር አስታረቀን፤ የማስታረቅንም አገልግሎት ሰጠን፤
¹⁹ እግዚአብሔር በክርስቶስ ዓለምን ከራሱ ጋር ሲያስታርቅ የሰዎችን በደል አይቈጥርባቸውም ነበር፤ ለእኛም ደግሞ የማስታረቅ ቃል ሰጠን።
²⁰ ስለዚህ እኛ የክርስቶስ እንደራሴዎች ነን፤ እግዚአብሔርም በእኛ አማካይነት ጥሪውን ያቀርባል፤ እኛም ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን በክርስቶስ እንለምናችኋለን።
✍️ መክሊት አየለ
📆 February 23, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
#እንደራሴ እንደራሴነቱ ለወከለው አካል እንጂ ለራሱ እና ለግል ጉዳዩ አይደለም።
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10
446
#ከምድሩ_የሚበልጥ_ተስፋ_አለን!
ተስፋችን ወንዝ የማያሻግር፣ ወንዝ የማይሻገር አይደለም። ተስፋችን ራሱ የተባረከ ተስፋ ነው፤ የሚዳሰስ የሚጨበጥ አካል ያለው ነው።
ተስፋችን በተለምዶው "ተስፋዬ እየመነመነ ሄደ" እንደምንለው አይነት ተስፋ አይደለም። ይልቁንም ተስፋ እያደረግነው እና እየጠበቅነው በሄድን ቁጥር የምንገናኝበት፣ ፊት ለፊት የምንተያይበት ቀን እየፈጠነ ነው።
ቀን ሲጨምር ከሚያባብለን፣ ሊያዘገየን ከሚጣጣረው የዓለም ብልጭልጭ እያፈተለክን ወደ ተስፋችን እየተቃረብን ነው።
በየመስሪያ ቤቱ፣ በየተቋማቱ የ5፣ የ10፣ የ30፣ የ50....ከዚያም በላይ ዓመት፦ እቅድ፣ ስትራቴጂካዊ ንድፍ እየተባለ የሚነገረን ነገር የምድርን ሕይወት ለማበጃጀት፣ በዚህ ያለንን ቆይታ የተሳካ ለማድረግ ቢጠቅምም፤ ማብቂያ፣ የቁርጥ ቀን፣ ፍጻሜ ግን አለው።
ሁሉን እያስጌጥን፣ እያስዋብን እዚህ መኖራችን አይቀጥልም። ከዚህኛው ሕይወት የሚበልጥ ሕይወት፣ ከዚህ ምድር ያለፈ ተስፋ አለን። ክርስቶስም ለዚህች ሕይወት ብቻ ተስፋ አይደረግም።
የተባረከውን ተስፋችንን ተስፋ እያደረግን፦ በጽናት፣ በትጋት ነቅቶ መጠበቅ፣ መኖር ይሁንልን!!
“ክርስቶስን ተስፋ ያደረግነው ለዚህች ሕይወት ብቻ ከሆነ፣ ከሰው ሁሉ ይልቅ የምናሳዝን ነን።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥19 (አዲሱ መ.ት)
“እኛ ግን አገራችን በሰማይ ነው፤ ከዚያ የሚመጣውንም አዳኝ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በናፍቆት እንጠባበቃለን፤”
— ፊልጵስዩስ 3፥20 (አዲሱ መ.ት)
ዮሐንስ 14 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ “ልባችሁ አይጨነቅ፤ በእግዚአብሔር እመኑ ፤ በእኔም ደግሞ እመኑ።
² በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ ይህ ባይሆንማ ኖሮ እነግራችሁ ነበር፤ የምሄደውም ስፍራ ላዘጋጅላችሁ ነው።
³ ሄጄም ስፍራ ካዘጋጀሁላችሁ በኋላ፣ እኔ ባለሁበት እናንተም ከእኔ ጋር እንድትሆኑ ልወስዳችሁ ዳግመኛ እመጣለሁ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 18, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
የተባረከውን ተስፋችንን ተስፋ እያደረግን፦ በጽናት፣ በትጋት ነቅቶ መጠበቅ፣ መኖር ይሁንልን!!
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10
446
መዝሙር 23 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፤ አንዳች አይጐድልብኝም።
² በለመለመ መስክ ያሳርፈኛል፤ በዕረፍት ውሃ ዘንድ ይመራኛል፤
³ ነፍሴንም ይመልሳታል። ስለ ስሙም፣ በጽድቅ መንገድ ይመራኛል።
⁴ በሞት ጥላ ሸለቆ ውስጥ፤ ብሄድ እንኳ፣ አንተ ከእኔ ጋር ስለ ሆንህ፣ ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ፣ እነርሱ ያጽናኑኛል።
⁵ ጠላቶቼ እያዩ፣ በፊቴ ማዕድ አዘጋጀህልኝ፤ ራሴን በዘይት ቀባህ፤ ጽዋዬም ሞልቶ ይፈስሳል።
⁶ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣ በጎነትና ምሕረት በእርግጥ ይከተሉኛል፤ እኔም በእግዚአብሔር ቤት፣ ለዘላለም እኖራለሁ።
“ቀድሞ እንደ ጠፉ በጎች ትቅበዘበዙ ነበር፤ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥25 (አዲሱ መ.ት)
ዮሐንስ 10 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ “መልካም እረኛ እኔ ነኝ፤ በጎቼን ዐውቃለሁ፤ እነርሱም ያውቁኛል፤
¹⁵ ይህም አብ እኔን እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው ነው። ሕይወቴንም ስለ በጎቼ አሳልፌ እሰጣለሁ።
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
#TheLordIsMyShepherd
446
እያንዳንዱን እርምጃችንን ከእርሱ ጋር ለመሄድ፤ በነገሮቻችን ሁሉ ላይ ከእግዚአብሔር ጋር ለመመካከር፤ የማያሳስት፣ የእውነት ምክር እና አቅጣጫን ለመቀበል ታድለናል፤ በማስተዋል እንጠቀምበት።
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10
446
#በማስተዋል_እንጠቀምበት!
እግዚአብሔር በሕይወታችን ሲኖር፣ ሞገስ ሲሆነን የሰው Recommendation አያስፈልገንም።
ማንም ሰው ከጎናችሁ ሳይኖር፣ ዓለም ሁሉ ፊቱን አዙሮባችሁ፣ ስለ እናንተ እውነት የሚመሰክር አንድ እንኳን ጠፍቶ፤ ለእናንተ ላዘጋጀው፣ ለሚገባው ስፍራ እግዚአብሔር ብቻውን፣ የማንም እርዳታ ሳያስፈልገው Recommend ሊያደርጋችሁ፤ ስፍራን ሊሰጣችሁ ይችላል።
ከሕያው አምላክ ጋር የልብ ወዳጅ፣ የቅርብ ጓደኛ የመሆን ዕድል፣ Privilege ተሰጥቶናል፤ በማስተዋል እንጠቀምበት።
እያንዳንዱን እርምጃችንን ከእርሱ ጋር ለመሄድ፤ በነገሮቻችን ሁሉ ላይ ከእግዚአብሔር ጋር ለመመካከር፤ የማያሳስት፣ የእውነት ምክር እና አቅጣጫን ለመቀበል ታድለናል፤ በማስተዋል እንጠቀምበት።
በማንም ሰው ፊት የማንሆነውን ነገር በእግዚአብሔር ፊት ለመሆን፣ ለማንም የማናሳየውን ማንነታችንን ለእግዚአብሔር ለማሳየት፣ ለማንም የማንነግረውን የልባችንን ሸክም ለእግዚአብሔር ግልጥልጥ አድርገን ለመንገር፣ የውስጥ ማንነታችንን፣ ጥልቁን ሳይቀር በእግዚአብሔር ለማስመርመር ታድለናል፤ በማስተዋል እንጠቀምበት።
ምንም ያህል ትሁት፣ ታጋሽ፣ ሰው አድማጭ ቢሆኑ የልብ ወዳጅ ያልናቸው ሰዎች እነርሱም የራሳቸው የሆነ ብዙ ሸክም፣ አድማጭና አማካሪ የሚፈልጉበት ብዙ ጉድለት አለባቸውና የሆነ ቀን ተነስተው፦ " ዛሬ ጥሩ ሁኔታ ላይ አይደለሁም፤ ለማውራት፣ ለመስማት ዝግጁ አይደለሁም።" ማለታቸው አይቀርም።
ፍጹሙ፣ የዘላለም የልብ ወዳጅ የሆነው፣ ሸክማችንን በየዕለቱ የሚሸከምልን፣ አዳኝ አምላካችን፣ ጌታ እግዚአብሔር ግን ሳይሰለቸን ከእኛ ጋር ሊሆን፣ ሊጸና፣ ሊሸከመን የታመነ ነውና ይህንን ድንቅ ዕድል በማስተዋል እንጠቀምበት።
“ሸክማችንን በየዕለቱ የሚሸከምልን፣ አዳኝ አምላካችን፣ ጌታ ይባረክ። ሴላ”
— መዝሙር 68፥19 (አዲሱ መ.ት)
"Blessed be the Lord, who daily bears us up; God is our salvation. Selah"
Psalm 68: 19 (ESV)
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 17, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
ከሕያው አምላክ ጋር የልብ ወዳጅ፣ የቅርብ ጓደኛ የመሆን ዕድል፣ Privilege ተሰጥቶናል፤ በማስተዋል እንጠቀምበት።
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10
446
#ታዲያ_ምን_እናገኝ_ይሆን?
ጌታችን ኢየሱስ በምድር በነበረበት ወቅት ሐዋርያው ጴጥሮስ ኢየሱስን ለመከተል ሁሉን ትቶ ለአያሌ ቀናት አብሮት ከሰነበተ፣ መውጣት መግባቱንና አገልግሎቱን በጥንቃቄ ከመረመረ፣ ከቃሉ ከተማረ፣ ብዙ ተአምራቶች በኢየሱስ እጅ ሲደረጉ ካየ፣..... ከሁሉም በላይ ደግሞ ኢየሱስ:- ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ከመሰከረ በኋላ አንድ ነገር ያሳስበውና ቆም ብሎ ኢየሱስን ይሄን ጥያቄ ይጠይቀዋል፦
“ጴጥሮስም መልሶ፣ “እኛ ሁሉን ትተን ተከትለንሃል፤ ታዲያ ምን እናገኝ ይሆን?” አለው።”
— ማቴዎስ 19፥27 (አዲሱ መ.ት)
ሁሉን ትቶ ኢየሱስን የመከተሉን ትርፍ፣ ዋጋ፣ ብድራት ለማወቅ፤ በወሰነው ሁሉን ትቶ ኢየሱስን የመከተል ውሳኔ ምትክ የሚቀበለውን ነገር #quantify ለማድረግ ያቀረበው ጥያቄ እያስገረመኝ፣ በውስጡም ራሴን እያየሁ ነበር።
የጌቶች ሁሉ ጌታ፣ የሁሉ ፈጣሪ፣ የነገሥታቱ ንጉሥ ኢየሱስ በአጠገቡ ቆሞ፣ ከእርሱ ጋር እያለ፤ ወደ ምድር ያመጣው ዋነኛ ጉዳይም የጠፋውን የሰው ልጅ ሊፈልግ እንደሆነና እነርሱን፣ የሰው ልጆችን ለማዳን ራሱን፣ ነፍሱን እንኳን ሳይሰስት ለሞት አሳልፎ ሊሰጥ እንደሆነ ለደቀመዛሙርቱ እየነገራቸው ይሄ ኢየሱስ ከዓሣ አጥማጅነት አውጥቶ ሰው አጥማጅ ያደረገው ጴጥሮስ ግን ትቶ በተከተለው ነገር ምትክ የሚያገኘው ነገር አሳስቦት #ታዲያ_ምን_እናገኝ_ይሆን? እያለ ይጠይቃል።
ታዲያ እኛስ ከጌታ ከኢየሱስ ጋር በጀመርነው ኑሮ፣ በደቀመዝሙርነት ሕይወታችን ላይ በመሃል ቆም እያልን፣ ስለ ኢየሱስ የተውናቸው ነገሮች ፊታችን ላይ ድቅን እያሉ እርሱን በመከተሌ ምን አገኝ ይሆን? እያልን እንጠይቅ ይሆን? ራሱን ስለኛ አሳልፎ የሰጠው፣ ውዱ ስጦታችን፣ የሕይወት እንጀራችን ኢየሱስ ከሁሉ ልቆ ሳይታየን፣ በእርሱ ሳናርፍና ሳንረካ እርሱን ለመከተል፣ ሁለንተናዬን ለእርሱ ለመስጠት ስል በተውኩት ነገር በወሰንኩት ውሳኔ ትርፌ ምን ይሆን እንል ይሆን?
ጌታ ይርዳን!! ጌታ ኢየሱስ ብቻ ይኑረኝ እንጂ
ምንስ ባይገኝ፣ ምንስ ባይኖረኝ የምንልበትን ጸጋ ያብዛልን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 January 30, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
#ታዲያ_ምን_እናገኝ_ይሆን?
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10
446
እግዚአብሔር በሰጠን በልዩ ልዩ ጸጋ ከምናገለግለው አገልግሎት፣ ከምንሰዋው መስዋዕት በፊት፦ ቅዱስ፣ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ፣ ሕያው ሆኖ ለእርሱ የተሰዋ ሰውነታችንን ይፈልገዋል።
ይህም እንደ ባለ አእምሮ የምናቀርበው አምልኮአችን፤ ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችን ነው። ለእግዚአብሔር በተሰጠ ማንነት መትጋት ይሁንልን!!
“እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ ሰውነታችሁን ቅዱስና እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕያው መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፤ ይህም እንደ ባለ አእምሮ የምታቀርቡት አምልኮአችሁ ነው።”
— ሮሜ 12፥1 (አዲሱ መ.ት)
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 18, 2021
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
446
#ለአእምሮ_የሚመች_አገልግሎት!
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10
446
ሳንሸማቀቅ፣ ሳናፍር፣ እውነት መሆንኽ ገብቶን የምንከተልህ ኢየሱስ። አንተን በዚህች ሕይወት ብቻ ተስፋ አናደርግኽም፤ እስከወዲያኛው ታዋጣናለህ፣ ታዛልቀናለህ።
