HOP Ministry
Відкрити в Telegram
HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.
Показати більшеКраїна не вказанаКатегорія не вказана
560
Підписники
+324 години
+217 днів
+5530 днів
Архів дописів
560
#መንፈሳዊ_ግለትን_መጠበቅ!
በተለምዶ ቀዝቃዛ ውሃ ወደ መፍላት የሚደርሰው የሚያገኘው ሙቀት እየጨመረ በሄደበት ልክ ነው። ቀዝቃዛ የነበረው ውሃ እሳት ሲያገኝ ለብ እያለ፣ እየሞቀ፣ እየሞቀ፣....እየሞቀ፣.....እየጋለ፣ ወደ መፍላት ይደርሳል። በተቃራኒው ደግሞ የፈላው ውሃም የሚቀዘቅዘው በአንድ ጊዜ ሳይሆን በጊዜ ሂደት ውስጥ ነው፤ ትኩሳትና ሙቀቱ እየቀነሰ፣ ለብ እያለ፣ በረድ እያለ፣ ወደ መቀዝቀዝ ይደርሳል። በሁለቱም ሂደት ውስጥ የሙቀቱ መጠን መለዋወጥ ነው የውሃውን ሁኔታ የሚወስነው። ማለትም የውሃው የሙቀት መጠን መጨመር ወይም መቀነስ፣ መውጣት ወይም መውረድ ውሃው በሚያገኘው የሙቀት መጠን ላይ ይወሰናል።
መንፈሳዊ ሕይወታችንም ልክ እንደዚሁ የውሃ ምሳሌ ሲዋዥቅ እናስተውላለን። በምድር እስካለን ድረስ ላይ ወጥቶ የሚቀር መንፈሳዊ ሕይወት እንደሌለ ሁሉ ታች ወርዶ የሚቀርም የለም። ነገር ግን መንፈሳዊ ግለታችንን መጠበቅ የእኛ ድርሻ ነው። መንፈሳዊ ሕይወታችን እንዲጎለብት፣ ብስለት እንዲኖረን፣ በመንፈስ የጋልን እንድንሆን ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት ካልቆየን፣ የእግዚአብሔርን ቃል ካላጠናን፣ ካልጸለይን፣ በመንፈስ ቅዱስ ካልተሞላን፣ ከቅዱሳን ጋር ሕብረት ካላደረግን፣....... በአጠቃላይ በመንፈሳዊው ነገር ላይ #አተኩረን ዕለት ተዕለት መንፈሳችንን ካልመገብን፣ የውስጥ ሰውነታችንን ካላጠነከርን እያሽቆለቆልን ሄደን ለብታ ላይ መድረሳችን፣ መንፈሳዊ ሕይወታችንም ቀዝቃዛና በራድ መሆኑ #አይቀሬ! ነው።
ስለዚህ መንፈሳዊ ግለታችንን አስጠብቆ ለመንቀሳቀስ የሕይወታችን ባለአደራ እንዲሁም መጋቢ ነን ማለት ነው። እኛ ያልሰራንበት፣ ያልመገብነው ሕይወታችን ከየትም መጥቶ እንደምንናፍቀው፣ እንደሚጠበቅበት ሊያድግና ሊያፈራ አይችልምና ዘወትር ራሳችን ላይ ለመስራት እንበርታ!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 23, 2024
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
Once and for All
Song by Lauren Daigle ‧ 2015
"God I give You all I can today
These scattered ashes that I hid away
I lay them all at Your feet
From the corners of my deepest shame
The empty places where I've worn Your name
Show me the love I say I believe
Oh Help me to lay it down
Oh Lord I lay it down
Oh let this be where I die
My lord with thee crucified
Be lifted high as my Kingdom's fall
Once and for all, once and for all
There is victory in my Saviors loss
And In the crimson flowing from the cross
Pour over me, pour over me yes
Oh let this be where I die
My lord with thee crucified
Be lifted high as my Kingdom's fall
Once and for all, once and for all
Oh Lord I lay it down
Oh Lord I lay it down
Help me to lay it down
Oh Lord I lay it down
Oh let this be where I die
My Lord with thee crucified
Be lifted high as my Kingdom's fall
Once and for all
Once and for all
Oh once and for all
Once and for all"
560
የእግዚአብሔር አብሮነት የሌለበት ከነዓን አይረባንም። አብሮነቱ በሌለበት ከሚሰጠን ከነዓን ይልቅ፤ ሁሉን አጥተን እግዚአብሔርን ማግኘት፣ በእርሱም መገኘት ይብዛልን!!
🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice.
https://t.me/hopministry10
560
#የእግዚአብሔር_አብሮነት_ከከነዓን_ይበልጣል።
የእግዚአብሔር አብሮነት ከከነዓን ይበልጣል።
ለእግዚአብሔር ሕዝብ፦ የእግዚአብሔር አብሮነት የሌለበት ከነዓን ሕይወት አይሆነውም፣ አይረባውም።
የእግዚአብሔር ሕዝብ ልዩነትና ሞገስ፦ ያለው ሀብት፣ በረከት፣ የሚወርሰው ከነዓን ሳይሆን፤ ሁሉን ሰጪው፣ የባርኮቱ ምንጭ የሆነው አምላኩ እግዚአብሔር ነው።
የእግዚአብሔር አብሮነት የሌለበት ከነዓን አይረባንም። አብሮነቱ በሌለበት ከሚሰጠን ከነዓን ይልቅ፤ ሁሉን አጥተን እግዚአብሔርን ማግኘት፣ በእርሱም መገኘት ይብዛልን!!
ከእግዚአብሔር ሀልዎት ውጪ እኛን ሕያው፣ ልዩ፣ ባለ ሞገስ የእግዚአብሔር ሕዝብ የሚያደርገን ምን አለ?
ዘጸአት 33 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ እግዚአብሔር (ያህዌ) “ሀልዎቴ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ ዕረፍትም እሰጥሃለሁ” ብሎ መለሰ።
¹⁵ ከዚያም ሙሴ እንዲህ አለው፤ “ሀልዎትህ ከእኛ ጋር ካልሄደ ከዚህ አትስደደን።
¹⁶ አንተ ከእኛ ጋር ካልሄድህ፣ አንተ በእኔና በሕዝብህ መደሰትህን ሌላው እንዴት ያውቃል? እኔንና ሕዝብህንስ በገጸ ምድር ከሚገኙት ከሌሎቹ ሕዝቦች ሁሉ ልዩ የሚያደርገን ሌላ ምን አለ?”
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 21, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
So Will I (100 Billion X)
Song by Hillsong Worship and Taya ‧ 2018
"God of creation
There at the start
Before the beginning of time
With no point of reference
You spoke to the dark
And fleshed out the wonder of light
And as You speak
A hundred billion galaxies are born
In the vapour of Your breath the planets form
If the stars were made to worship so will I
I can see Your heart in everything You've made
Every burning star
A signal fire of grace
If creation sings Your praises so will I
God of Your promise
You don't speak in vain
No syllable empty or void
For once You have spoken
All nature and science
Follow the sound of Your voice
And as You speak
A hundred billion creatures catch Your breath
Evolving in pursuit of what You said
If it all reveals Your nature so will I
I can see Your heart in everything You say
Every painted sky
A canvas of Your grace
If creation still obeys You so will I
So will I
If the stars were made to worship so will I
If the mountains bow in reverence so will I
If the oceans roar Your greatness so will I
For if everything exists to lift You high so will I
If the wind goes where You send it so will I
If the rocks cry out in silence so will I
If the sum of all our praises still falls shy
Then we'll sing again a hundred billion times
God of salvation
You chased down my heart
Through all of my failure and pride
On a hill You created
The light of the world
Abandoned in darkness to die
And as You speak
A hundred billion failures diappear
Where You lost Your life so I could find it here
If You left the grave behind You so will I
I can see Your heart in everything You've done
Every part designed in a work of art called love
If You gladly chose surrender so will I
I can see Your heart
Eight billion different ways
Every precious one
A child You died to save
If You gave Your life to love them so will I
Like You would again a hundred billion times
But what measure could amount to Your desire
You're the One who never leaves the one behind"
560
"And as You speak
A hundred billion failures diappear
Where You lost Your life so I could find it here
If You left the grave behind You so will I
I can see Your heart in everything You've done
Every part designed in a work of art called love
If You gladly chose surrender so will I"
560
#ኢየሱስ_ማን_መሆኑን_በቅጡ_ማወቅ!
ብዙ ነገሮች አጥተን ኖረን አይተነዋል፤ ብዙ ነገሮች ጥለውን ሄደው ስንቀጥል ራሳችንን አግኝተናል። ጌታ ኢየሱስን ላየ፣ ቸርነቱን ለቀመሰ ሰው ግን ከኢየሱስ መለየት፣ ያለ እርሱም መኖር ሞት ነው። የኢየሱስ ሁሉ በሁሉነት ሲገባን የሚያስፈልገን እርሱ ብቻ እንደሆነ፤ ያለ እርሱ መኖር፣ ምንም ማድረግ እንደማንችል እንረዳለን።
ኢየሱስ ከያዕቆብ ጉድጓድ መብለጡ የእውነት ለገባው ሰው ኢየሱስ ጊዜያዊ ጥምን የሚያረካ ነገር ሳይሆን የዘላለም ውኃ ምንጭ፣ የሕይወት ውኃ ነው። ኢየሱስ ማን መሆኑን ማወቅ የዘላለም ሕይወትን ማትረፍ ነው። ያውም ትርፉ በምድር ስሌት የማይሰላ ዘላለማዊ ትርፍ ነው።
ሳምራዊቷ ሴት ኢየሱስ ማን መሆኑን በቅጡ ሳትረዳ በፊት የያዕቆብ ጉድጓድ የምታዜምለት፣ ታላቅነቱን የምትመሰክርለት፣ ከእርሱ ሌላ ምንጭ ያለ እንኳ እስካይመስላት ድረስ የምትመካበት ምንጯ ነበር።
የኢየሱስ የዘላለም ውኃ ምንጭነት ሲገባት ግን አይደለም ደግማ ስለ ያዕቆብ ጉድጓድ ልታወራ፣ "አንተ ይህን ጉድጓድ ከሰጠን ከአባታችን ከያዕቆብ ትበልጣለህን?" ብላ ኢየሱስን ከያዕቆብ ጋር ልታወዳድር ይቅርና ስለ ኢየሱስ የዘላለም ውኃ ምንጭነት መለስ ብላ ለማሰብና ለመጠራጠር እንኳ ጊዜ አላገኘችም። ለእርሷ የበራላት ብርሃን ለብዙዎች እንዲበራ፣ ያየችውን ብዙዎች እንዲያዩት፣ የገባትንና የቀመሰችውን እውነት፣ ሕይወት ብዙዎች እንዲቀምሱ፣ ብዙዎችን ወደ እርሱ ልታፈልስ ወደ ሕዝቡ ሮጠች፤ እርሱ ማን መሆኑን አውቃለችና።
ኢየሱስ ማን መሆኑን በቅጡ ማወቅ፦ ከብዙ ብክነት፣ በአላስፈላጊ፣ በሰው ሰራሽ፣ ጥምን በማይቆርጡ፣ በጥቃቅን ምንጮች ከመርካት ይጠብቃል፤ እርሱን ብቻ ለመጠማት፣ ከእርሱ ብቻ ለመጠጣት፣ በእርሱ ብቻ ለመርካት ይጠቅማል። ኢየሱስን በማንነቱ ማወቅ፣ እርሱ ማን መሆኑን በቅጡ መረዳት፣ ማስተዋል ይሁንልን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 19, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
#የማያልቅ_ርዕሰ_ጉዳይ!
በምድር ስላሉት ጉዳዮቻችን፣ ስለምንፈልጋቸውና ስለሚያስፈልጉን ነገሮች የምንጸልየው ፀሎት በፀሎት መልስ ይሻራል። መልሳችንን ስንቀበል፣ የጠየቅነውን ነገር ስናገኝ ፀሎቱን እንተወዋለን፣ እንቀይረዋለን።
ስለ ራሱ ስለ እግዚአብሔር፣ ስለ መገኘቱ፣ ስለ ሕልውናው፣ ስለ መንፈሱ የሚደረግ ፀሎት ግን ጊዜ የማይሽረው፤ አሁንም፣ ዛሬም፣ ነገም፣ ከነገ በስቲያ፣ በምድር እስካለን ድረስ፣ ጌታን ፊት ለፊት እስከምናየው ድረስ የሚዘልቅ፣ መዝለቅ ያለበት ፀሎት ነው።
በጊዜያዊ ነገሮች ላይ የፀና ፀሎት እንደተቀያየረ፣ እንደዋዥቀ ይኖራል፤ ድካም አለበት፣ ጉልበትን ያዝላል። ዘላለማዊውን ነገር፣ ዘላለማዊውን አምላክ ለማግኘት የሚደረግ መቃተት ግን ሕይወት አለበት፤ ጸላዩን፣ ፈላጊውን ሕያው እያደረገ፣ እያለመለመ ይሄዳል፤ በቃኝም አይባልም ሌላ እልፍ ረሃብ ይወልዳል።
ጌታ በቸር እጆቹ ይንካን፤ ቸር መሆኑን ያቅምሰን፤ ያኔ እያየነው፣ እያገኘነው፣ በእርሱ እየተዳሰስንና እየተነካን፦ የያዝነው አይመስለንም፣ አብረነው ሆነን ይናፍቀናል፣ የእርሱ እልፍ ረሃብ ይበዛልናል፣ ጌታን ጌታን ብለን እየናፈቅነው፣ እያገኘነው ይርበናል፣ ይርበናል....፣ እርሱን መከተል፣ መከታተል ስራችን ይሆናል።
ከምንፈልገው፣ ከሚያስፈልጉንም ነገሮች በላይ እግዚአብሔር፣ መንፈስ ቅዱስ፣ ኢየሱስ ያስፈልገናል። እግዚአብሔርን እየፈለግን መፈለግ፣ እየናፈቅን መናፈቅ ይሁንልን!! የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር የምትመረምረው መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሙላን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 18, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
ከምንፈልገው፣ ከሚያስፈልጉንም ነገሮች በላይ እግዚአብሔር፣ መንፈስ ቅዱስ፣ ኢየሱስ ያስፈልገናል። እግዚአብሔርን እየፈለግን መፈለግ፣ እየናፈቅን መናፈቅ ይሁንልን!!
🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice.
https://t.me/hopministry10
560
ሌሎች ረሃቦቻችንን ሁሉ ተቀምተን #በአንድ_ረሃብ (በእግዚአብሔር ብቻ) ብንጠመድ፣ ሌላውን ለማየት፣ ለመስማት፣ ለመንካት፣ ለመብላት አቅም አጥተን ለሕይወት ቃል፣ ለሕይወት ውሃ፣ ለሕይወት ውሃ ምንጭ ረሃብ፣ ጥማት ብንበረታ፤ የጌታ የፍቅሩ ትኩሳት የልባችንን ጓዳ ቢያሞቀው፣ ለብታችን በፍቅሩ እሳት ግለት ቢሻር፣ ትናንት ባላየነው መንገድ ጌታ ቢያገኘን፣ መሰዊያችን ቢታደስ፣ ከማለዳ እስከ ምሽት የቃሉ አሰላስሎት አሳባችንን ቢቆጣጠረው፣ ማብቂያዋ መቼ እንደሆነ የማይታወቀው እንፋሎት ዘመናችን ለኢየሱስ እየነደደች የምታበራ መብራት ብትሆን.....ይሄ ሁሉ ልቤ የሚብሰለሰልበት፣ ጌታ በኃይሉ ችሎት ቢያደርግልን ብዬ የምናፍቀው ናፍቆቴ፣ ቁጭቴ ነው።
ናፍቆቴን እንደምትጋሩኝ እምነቴ ነው፤ ይህ ሁሉ በእኛ እውን እንዲሆን የመንፈስ ቅዱስ ጉብኝት ያግኘን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 April 12, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
እግዚአብሔርን አምነን፣ ታምነን በመንገዱ ላይ እየሄድን ከሆነ፦ እርሱ አላዘገየንም፣ አላስቸኮለንም፤ እርሱ ሁሉን በፈቃዱ ምክር መሰረት እየሰራ ይገኛል።
ረፈደብኝ፣ ወደኋላ ቀረሁ፤ መፍጠን ከሚገባኝ በላይ ፈጥኜ በአላስፈላጊ መንገድ ተጓዝኹ አንበል። እግዚአብሔር ብቻውን መምራት፣ ከግብ ማድረስም ያውቅበታልና ሕይወታችንን በመሪያችን እጅ ላይ በእምነት እናኑር፤ እግዚአብሔርን አምነን፣ ሳናይ እንከተለው፣ እንከታተለው። በእግዚአብሔር መንገድ ፀንተን አንጸጸትም፤ እርሱ ያሳርፈናል!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 July 16, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
🌿 HOP Ministry — Hear. Obey. Practice.
በእግዚአብሔር መንገድ ፀንተን አንጸጸትም፤ እርሱ ያሳርፈናል!!
https://t.me/hopministry10
560
““እናንት ሸክም የከበዳችሁና የደከማችሁ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም ዕረፍት እሰጣችኋለሁ።”
— ማቴዎስ 11፥28 (አዲሱ መ.ት)
“እርሱ ስለ እናንተ ስለሚያስብ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 5፥7 (አዲሱ መ.ት)
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
