ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Відкрити в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Показати більше2 955
Підписники
+1424 години
+247 днів
+38330 днів
Архів дописів
50 አለቃ ካሳሁን ኃይሌ በመሐል ሳይንት ግንባር የአፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ 47ኛ ክ/ጦር #አትሮንስ_ሻለቃን ተቀላቀለ:: 50 አለቃው የዲሽቃ ምድብተኛ ሻንበል መሪ ነበር።
50 አለቃ ካሳሁን ኃይሌ ስለጠላት አሁናዊ ቁመና ሲናገር "ለምንና በምን ምክንያት እንደሚዋጋ የማያውቅ፤ ዓላማ የሌለውና የጥቂት ግለሰቦችን ሥልጣን ለማስከበር መተኪያ የሌላትን አንድያ ህይወቱን የሚገብር በመሆኑ፣ መላው ሠራዊት በደመ_ነፍስ የሚቅበዘበዝ ሆኗል። ሞራሉም ዋዥቋል፤ ወታደር የሞራል ስንቅ ካልታጠቀ ደግሞ በየአውደ_ውጊያው የሽንፈትን ፅዋ ቢጎነጭ የሚደንቅ አይደለም" ብሏል።
የአፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር የዘመቻ መምሪያ ም/ኃላፊው አርበኛ ጎሹ ታረቀ ኮብላዩን በክብር ተቀብሎታል!
ምንጭ:- የአፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ 47ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አርበኛ Eyob Ashenafi
ከ"ዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ" ማግስት የብልፅግና ሰራዊት መፍረሱን ቀጥሏል!
ለብልፅግና የዙፋን መንበር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ እየታተረና እየተጋ የሚገኘው ብልፅግና መራሹ ጦር በዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ በከባድ ሚዛን በፋኖ ክንድ የተመታው ሰራዊት ከአሐዱ በመፍረስ ፋኖ ወደሚገኝበት ቦታ ሁሉ እየተቀላቀለ ይገኛል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ኮር አካል የሆነውን 19ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት አስር አለቃ አማረ ተፈራ እና ጓደኛው ከ34ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት በመውጣት የፋኖን ቤት የተቀላቀሉ ሲሆን መከላከያ አሁን ባለው ቁመና የመዋጋት አቅም እንደሌለውና ሰራዊቱም በፍፁም መሰላቸትና በከባድ የስነ-ልቦና ውድቀት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በሌላ መረጃ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር አካል የሆነውን 30ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት የ13ኛ ዕዝ ኦፕሬተር የነበሩት:-
1ኛ. መሰረታዊ ወታደር ማርይሁን ጌታ
2ኛ. መሰረታዊ ወታደር ዮሴፍ አዱኛው
3ኛ. መሰረታዊ ወታደር ቴዎድሮስ ጥላሁን
ሁላቸውንም ቤተሰቦቻቸው ልከው ከሚያስተምሯቸው ኮሌጅ ላይ በማፈን ወደ ማሰልጠኛ በማስገባት ተገደው የገቡ እንደሆኑ ገልፀው የአገዛዙን ጓዳ ከፈተሹና ከመረመሩ በኋላ ለቤተሰቦቻችንና ወንድም እህቶቻችን ማጥፊያ ስርዓትና ተቋም አናገለግልም በማለት ፋኖን እንደተቀላቀሉ ተናግረዋል።
ስቦ በማስከዳት ስርዓቱን ከማፍረስ ጋር ተያይዞ ከመስከረም 14/2018 ዓ/ም ዘመቻ አደም አሊ (አባ ናደው)ን ጨምሮ ለተከታታይ ስምንት ወራት ከ850 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት መከላከያ፣ አድማ ብተና፣ ፖሊስ፣ ሚሊሻና ስርዓቱን አገልጋይ ካቢኔ አባላት 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ፋኖን የተቀላቀሉ ሲሆን አሁንም አልረፈደምና ቀሪው የአገዛዙ ሰራዊት በፍጥነት ፋኖን በመቀላቀል ህይዎቱን እንዲታደግ ሲል የኮሩ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በሪሁን ደምሌ ጥሪ አቅርቧል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ቢሆነኝ ቢያበይን መረጃውን አድርሷል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ
ሰኔ 04/2018 ዓ.ም
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ወገንን የማንቃት እና ጠላትን የማፍረሱን ስራ ዛሬም እንደ ትላንቱ ቀጥለውበታል!
የኦህዴድ/ብልፅግና ሥልጣን ጠባቂ ቅጥረኞች ከአመራር እስከ መሠረታዊ ወታደር እንደ እንቧይ ካብ እየተናደ ነው። 11ኛ ዕዝ 104ኛ ኮር 9ኛ ክ/ጦር እንደ ጨው እየሟሟች ነው። ይህ ወንጀለኛ ቡድን ሥልጣኑን ለማራዘም በመሰዊያው አምድ ላይ ለማቆም በትምህርት ቤትና በሌሎችም ቦታዎች እያፈሰ ያስገባቸው ወታደሮች "በእኛ ውድ ህይወት የአንባገነኖችን ሥልጣን አናፀናም" በማለት ወደ ወገን መቀላቀላቸውን ቀጥለዋል።
ዛሬ 03/10/2018 ዓ.ም አትሮንስ ሻለቃን የተቀላቀለው 50 አለቃ ካሳሁን ኃይሌ የዲሽቃ ምድብተኛ ሻንበል መሪ ነው። ሃምሳ አለቃ ካሳሁን ኃይሌ ስለጠላት አሁናዊ ቁመና ሲናገር "ለምንና በምን ምክንያት እንደሚዋጋ የማያውቅ፤ ዓላማ የሌለውና የጥቂት ግለሰቦችን ሥልጣን ለማስከበር መተኪያ የሌላትን አንድያ ህይወቱን የሚገብር፣ በመሆኑ መላው ሠራዊት በደመ-ነፍስ የሚቅበዘበዝ ሆኗል። ሞራሉም ዋዥቋል፤ ወታደር የሞራል ስንቅ ካልታጠቀ ደግሞ በየአውደ-ውጊያው የሽንፈትን ፅዋ ቢጎነጭ የሚደንቅ አይደለም " ብሏል።
በዚሁ ምዕራብ ወሎ ቀጠና በጃማ ወረዳ 33ኛ ዋሲል ክፍለጦር ነፃ ባወጣው አህያፈጅ ቀጠና ከአሉ የአባት አርበኞች ጋር አመርቂ ውይይት አካሄደ። በዚህ ውይይት አሁናዊ የአማራ ሕዝብ የትግል ቁመና፣ የአማራ ትግ የደረሰበት ደረጃ እና ወቅታዊ የአገዛዙን ውድቀት ላይ ጥልቅ ውይይት ከአባት አርበኞቹ ጋር ተካሂዷል። የብልፅግናው አገዛዝ ሊያደርገው የነበረውን የማደናገሪያ ምርጫ በአባት አርበኛው ንቁ ተሳትፎ እንደከሸፈ በዚህም የአፋብን ወታደራዊ ፍርድ ቤት ሰብሳቢ አርበኛ አለባቸው ቀስቅሴ ምስጋና አቅርበዋል። አርበኛው አያይዘውም በመጭው ወራት አማራ ጠሉን ጥቁር ናዚ ስርዓት ሙሉ በሙሉ እናፀዳዋለን ብለዋል። ለዚህም ሁሉም የአማራ ህዝብና የአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ደጋፊ ኢትዮጰያዊ ራሱን ለመጨረሻው የለውጥ አብዮት ያዘጋጅ ብለዋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 03/2018 ዓ.ም
ከሪፎሙ ማግስት ከፍተኛ የዕዝና የኮር አመራሮች በተገኙበት የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር ደማቅ የተሃዲሶ መርሃ ግብር በማካሔድ እራሱን ለላቀ ግዳጅ ብቁ ማድረጉን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ለዕዙ በላከው መረጃ አስታወቀ።
አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በስሩ የሚገኙ ክፍለ ጦሮችን ተከታታይ ጥልቅ ግምገማ በማድረግ ለቀጣይ ግዳጅ በተሻለ ቁመና ላይ ለማብቃት ያለመ የተሃዲሶ መርሃ ግብር እያካሔደ ይገኛል።
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው ምኒልክ ክፍለጦር ትላንት ሰኔ 02 ቀን 2018ዓ.ም ከፍተኛ የዕዝና የኮር አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ደማቅ የተሃዲሶ መርሀ ግብር ማካሔዱን ኮሩ የገለፀ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ ወቅቱን የዋጀ የተለያዩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ ባስተላለፉት መልዕክት "ምኒልክ ክፍለ ጦር የተሰየመችው የዘመኑ የአፍሪካው መሪ የኢትዮጵያው ንጉስ በሆኑት የአድዋው ፊትአውራሪ ምልክት በዳግማዊ ንጉስ አፄ ምኒልክ ስም ሲሆን እኛም የእነዛ ጀግኖች ትላንት የውጭ ወራሪዎችን አከርካሪ ሰብረው የመለሱ፣እምቢ ለባርነት ብለው የተዋደቁ፣ ደማቸውን አፍሰው፣አጥንታቸውን ከስክሰው ነፃነትን ያጎናፀፉን ኩሩ የነፃ ህዝቦች ልጆች ነን ያሉ ሲሆን፣ የአሁኑ ትውልድም በአባቶቹ የጀግንነት መንፈስ የኦሆዴድ መራሹ የውጭ ተላላኪ አማራ ጠል ብልፅግና አንዲሁም ብአዴንን የመሰለ የዘመናችን እንቁላል ቀቃይ የሀገር ውስጥ ተላላኪ ባንዳዎችን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ታሪካችንን በደማችን የምንፅፍ የምኒልክ ልጆች ነን ብለዋል" አክለውም "ምኒልክ ክፍለ ጦር ልክ እንደ አባቶቻችን በአፄ ምኒልክ ታሪክ፣ በመይሳው ካሳ ዘመን ተሻጋሪ ጀግንነት፣ በአባ ኮስትር በላይ ዘለቀ ታሪክ እንዲሁም የዘመናችን እንቁ የትግሉ ችቦ ለኳሽ በርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ፅጌ የጀግንነት መንፈስ የተቃኘ ከጎጥና ከአካባቢ እሳቤ የፀዳ የአማራ ሰራዊት የኢትዮጵያ ተስፋ መሆን አለበት" በማለት በሰራዊቱ ፊት ተገኝተው ወቅታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመርሀ ግብሩ ላይ የክፍለ ጦሩ መስራች የነበረው አርበኛ ሙሴ ሸዋፈራ ለሰራዊቱ ባስተላለፉት መልዕክት "ምኒልክ ክፍለጦር እንደ ስሟ በአምሳለ አባታችን አፄ ምኒልክ አይረሴ ታሪኮችን በመስራት የአማራ ፋኖ ቁመና ይዛችሁ የህዝባችሁ አገልጋይ እንድትሆኑ" ሲሉ አዲስ ለተዋቀረው የክፍለጦሩ አመራሮችና ለሰራዊቱ የአደራ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም የተሀዲሶ መርሀ ግብሩ በተለያዩ ኪነ ጠበብ ታጅቦ ቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ በስኬት መጠናቀቁን በመርሀ ግብሩ ላይ በአካል ተገኝቶ ፕሮግራሙን የተከታተለው የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ከስፍራው ለዕዙ ዜና ክፍል በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል።
''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 03/2018ዓ.ም
አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ ክ/ር ግዙፍ 2ኛ ዙር ኮማንዶ የፋኖ ሰራዊት አስመረቀ!!!
በትናንትናው እለት ሰኔ 2/2018 ጣና ብርጌድ በመባል የሚታዎቀው አደረጃጀት አሁን ላይ ከቀጠናው አቀማመጥ ለግዳጅ በሚያመች መንገድ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በዉል በማጤንና በመምከር ታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው ሙጨ ያለመውን ትክክለኛ የመታገያ ሀሳብ ከዳር ለማድረስ ጥልቅ ውይይት በማድረግ የክ/ሩን አደረጃጀት አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ በሚል ስያሜና በስሩ አራት ሬጅመንቶችን በማደራጀት ካጠናቀቀ የሰነባበተ ሲሆን ለወራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ብዙ መሰናክሎችን በማለፍ በተለይ የታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው መስዋትነት ሳይበግራቸው እንደ ታጋይ በቁጭት የተሻለ በመስራት አንድ ልቡ ቢሰዋ እሽ ልቡ ይወለዳል በማለት ስልጠናውን በብቃት ማጠናቀቅ ተችሏል ሲል የክ/ሩ የህ /ግ አርበኛ አንደበት አበጀ ገልጿታል።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር የህ/ግ ክፍል
ሰኔ 3/2018
ሻንበል መሪው ቲም መሪው እና ብሬን ተኳሹ ወደ ፋኖ 201ኛ ኮር 54ኛ እና 74ኛ ክ/ጦር ተቀላቅለዋል።
◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉◉
........ሰኔ 3/2018 ዓ.ም
1.በውቀት በላይ...ዋና ብሬን ተኳሽ 54ኛክ/ጦር
2.አበባው ጌትነት....አድማ ብተና
3.ወንድም በሬ...ፓራኮማንዶ...ቲም መሪ
4.ደጉ ጥጋቡ....የጥምር ጦሩ.. ሻንበል መሪ
5.ብልሀቱ ካሳ..ሚሊሻ74ኛክ/ጦር የገቡ ሲሆን በክፍለ ጦር አመራሮቸ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ለማይረባ እና ሽርፍራፊ ጥቅም ብላቹህ መተኪያ የሌለው ህይወታቹህን አትገበሩ ኑ እራሳቹን አድኑ
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
√ሰላም የተከበራችሁ የትግላችን ደጋፊዎች በሙሉ ትግላችን ድርጅቱ በፈለገው አቅጣጫ እየተጓዘ ቢሆንም የትግል ዋና ሞተሩ የሰው ሃይል መሆኑ ይታወቃል በአለማችን ትልልቅ የጦር ሰራዊት የግነቡት ሀገራት የሰው ሃይል በማሰልጠን በማደረጃት በማስታጠቅ ነው የአማራ ፋኖ አደረጃጀቱን እያሻሻለ መምጣቱ ለሁላችንም ግልፅ ነው!!
አሁን በክልላችን በርካታ ምልስ ሰራዊት እንዳለ የውስጥ አርበኞች መረጃ በየዕለቱ ይደርሰናል በዚህም መሰረት በምኒልክ ዕዝ ቀጠና (50000ሺ ) አምሳ ሺ ምልስ ሰራዊት ፣ በአሳምነው ዕዝ (36000) ሰላሳ ስድስት ሺ ፣በቴዎድሮስ ዕዝ (60000) ስልሳ ሺ ፣ በበላይ ዕዝ (52 000) አምሳ ሁለት ሺ ምልስ ሰራዊት እንዳለ አጣርተናል ስለዚህ ሀገር እየተደፈረ ህዝብ እየተሰቃየ የውትድርናን ሙያ ይዘህ እቤትህ ቁጭ ያልክ ወታደር እንዴት አስቻለህ ትናት ከባድማ እስከ ጦረና ግባር ከሀገር ውስጥ ሶማሊያ ከኦጋደን በረሃ እስከ ከሶማሊያ ሞቋድሾ ከዚያም አልፎ እስከ ሱዳን በርሃ ድረስ የከፈልነውን መስዋትነት ሁላችሁም ታውቃላችሁ ታዲያ ዛሬ የአማራ ህዝብ እንደ ህዝብ የሞት አዋጅ ታውጆብን በጅምላ እየተቀበርን በጅምላ እየታረድን እንደነገድ ሊያጠፉን ቦታና ጊዜ እየጠበቁ ባሉበት ስዓት እንዴት አስችሏችሁ በህዝባችሁ ላይ ልባችሁ ጨክኖ እጅና አግራችሁን አጥፋችሁ ቤታችሁን ዘግታችሁ መቀመጥን መረጣችሁ ትናትን ያወራነው ዛሬ በህይወት ስላለን ነው ነገ በህይወት ካለን ስለቀጣዩ ታሪክ እናወራ ይሆናል!
ግን በህይወት እስካለን በቻልነው ሙያ ለህዝባችን ባሪያ ሆነን እንታገል ህዝባችንን እንዳን እርስታችንን እንጠብቅ እኔ የምታገለው የአማራን ህዝብ ጥቅም አሳልፎ ለመሸጥ አይደለም
ወይም በህዝባችን ቁማር ለመቆመር አይደለም አማራ ያለማንም ጣልቃ ገብነት በእራሱ በአብራኩ ልጆች ወደ ክብሩ በነፃነት እንዲመለስ ነው እንደ ባለፈው ሁለተኛ/ሶስተኛ ወገን ሆነን እንደ ብአዴን አሽከር/ተለጣፊ ለመሆን አይደለም።
√ ሁላችንም ብዙ በደል ደርሱብን ያውቃል ወታደር ቤት እያለን ያንን ሁሉ መከራ አልፈን እዚህ ደርሰናል! ህይወት እራሷ ፈተና ነች ግን ፅናት ያስፈልጋታል! በርግጥ ትግሉ አልጋ በአልጋ አይደለም ብዙ ውጣ ውረድ አለ ከዚያ ካሳለፍነው ህይወት አይበልጥም!
ፋኖ ላይ ለህዝብህ ስትል የምከፍለው መስዋት ውስጥህ እየረካ መንፈስህ እየታደሰ ሞትህ የፃዲቅ ሞት ቁስልህ የውሻ ቁስል እንደሆነ እያወክ ከጀርባህ ብዙ አባት ፣እናት ፣እህት ፣ወንድም ስላለህ ደስ እያለህ ትታገላለህ! ስለዚህ ወንድሞቸ በአልቧልታ ውሬ ሳትወናበዱ ኑ ከህዝባችሁ ጋር ታረቁ አባት ለልጁ ይቅር ይላል ትግላችን መሪር ነው ! አሁንም አረፈዱም ወደ ቀልባችሁ ተመልሱና ወደ እኛ መጥታችሁ የትግላችን አጋር የህዝባችሁ እምባ አባሽ ፣የእኛ የወንድሞቻችሁ መከታ ፣ የጠላታችሁ መርዶ እንድትሆኑ እንሻለን!
ወደ ትግሉ ለመቀላቀል የምትፈልጉ ወንድሞቸ በሙሉ በራችን ከፍት ነው እኔም ሆኑ ጓዶቸ እናተን ለመቀበል ዝግጁ ነን!
ስለአፄ ቴዎድሮስ ጀግንነት ከተነገረው አንድ ልበላችሁ!
"ቋራ ላይ ሆኖ ክንፉ ሲያገሳ
የመይሳው ልጅ ቢጨመር ካሳ
ግብፅን ጨነቀው ነፍሱን ረሳ
እንኳን ጤነኛው ሬሳው. ፈሳ!"
ፋኖ የአማራ ህዝብ የመዳኛ መንገድ!
ፋኖ ያሸንፋል አማራነት ወይ ሞት!
ጆሲ __
ተራሮቹ ሁልጊዜም ፅናተኞች ናቸው። ነገር ግን ዝምታቸው የጀግኖችን ደምና የባንዳዎችን ክህደት አምቆ የያዘ ሚስጥራዊ ሳጥን ነው። ታሪካችን የሚጀምረው አንጸባራቂው የለማ አዝመራ በነፈሰ ቁጥር፣ ልቡ በጥቅም በሚወዘወዘው በአንዱ የውስጥ ሰው ቤት ውስጥ ነው። ካሜራው ከተራራው ወርዶ አንዲት ጥንታዊት የሳር ጎጆ ላይ ያርፋል። በጎጆው ውስጥ አንዲት የሸክላ ማሰሮ በከሰል እሳት ላይ ትንተከተካለች።
በዚህም አንድ አረጋዊው አባ መላኩ ጠቆር ያለውን ጋቢያቸውን በትከሻቸው ላይ እያማረጡ፣ ከፊታቸው ለተቀመጠው ወጣት ልጃቸው ለአሰፋ በትኩረት ይመለከቱታል። አሰፋ አይኖቹ እረፍት የላቸውም። በእጆቹ የወርቅ ሳንቲሞችን ያገላብጣል፤ ፊቱ ላይ ግን የፍርሃትና የስግብግብነት ጥላ ያንጸባርቃል።አባ መላኩ፦ ድምፃቸው በጥበብና በክብደት ተሞልቶ አሰፋ… ልጄ ሆይ! ይሄ እጅህ ላይ ያለው ወርቅ የትናንት እንጀራህ እንዳልሆነ አውቃለሁ። ይሄ ወርቅ የዛሬው ወገንህ የነገው የሞት ደብዳቤ ነው ይለዋል።
አሰፋ፦ ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ፣ በቁጣ አባባ! እናንተ ሁልጊዜ ስለ ሀገርና ስለ ክብር ታወራላችሁ! ሀገር ምን በላች? ክብር ምን አጠጣች? ከውጭ የመጡት ሰዎች እኮ እኔን የዚህ አካባቢ አስተዳዳሪ ሊያደርጉኝ ቃል ገብተውልኛል። እኔ ባልመራቸው ሌላ ሰው መርቶ ያሳያቸዋል። እኔ መብላት ካለብኝ፣ ለምን አሁን አልበላም?
አባ መላኩ፦ በትካዜ ራሳቸውን እየነቀነቁ አየህ… አሰፋ። እኛን የመጣብን ጠላት ሊያጠፋን አይችልም ነበር። ምክንያቱም እኛ ይሄን ገደል፣ ይሄን ተራራ፣ ይሄን ጫካ ጠንቅቀን እናውቀዋለን። ጠላት ግን መሬቱንም ሰማዩንም አያውቀውም። ጠላት አይኑ እውር ነበር። ነገር ግን ያ አሳፋሪ ታሪክ የተጻፈው... አንተና መሰሎችህ ሆዳችሁን ለማርካት ጥቅማጥቅም ፍለጋ ስትሉ የጠላት አይን ሆናችሁ ስትመሩት ነው። የአማራ ባንዳ እራሱ ሆዳም አማራ መሆኑን ስታይ ነው የውስጥ ቁስሉ የሚደማው። የውጪው ጠላትማ በሩን አንኳክቶ ይገባል፤ በሩን የከፈትከው ግን አንተ የውስጡ ሰው ነህ!
አሰፋ፦ ፊቱ እየተለዋወጠ እኔ ወንድሞቼን አሳልፌ አልሰጠሁም! እኔማ... የራሴን እድል ነው የሞከርኩት። አባ መላኩ፦ ከመቀመጫቸው ተነስተው ወደ አሰፋ እየተጠጉ፣ አይን አይኑን እያዩ እድልህን ሳይሆን ክብሩን የጠበቀውን ማኅበረሰብህን ነው የሸጥከው! ታሪክ ነገ የአንተን ስም በወርቅ ሳይሆን በጥቁር ቀለም ነው የሚጽፈው። ጠላት ለአንተ የሰጠህ ወርቅ አንተን ለማክበር ሳይሆን፣ አንተን ተጠቅሞ ወንድሞችህን ካረደ በኋላ አንተንም እንደ በግ አርዶ ለመጣል ነው። ለባንዳ የሚሆን ክብር የትም ሀገር የለም! ካሜሪው ከአረጋዊው አባ መላኩ አይን ወጥቶ፣ ውጭ ወዳለው ጨለማ ተራራ ይወጣል። ድንገተኛ የነፋስ ጩኸትና የሩቅ የተኩስ ድምፅ ይሰማል።
እናም ምን ልላችሁ መሰላችሁ እውነት ነው… ታሪክ ዛሬም ድረስ ይመሰክራል። የአንድ ማኅበረሰብ ትልቁ ጠላት ከሩቅ የመጣው ወራሪ ሳይሆን፣ በመካከሉ በቀለ የተፈጠረ፣ ለጊዜያዊ ጥቅም ሲል የሕዝቡን ደምና ትግል አሳልፎ የሚሸጠው "የውስጥ ሆዳም" ነው። ነገር ግን ታሪክ ባንዳዎችን ይረሳቸዋል፤ ወይም ደግሞ በውርደት ስማቸውን ያነሳዋል። ጽናትና እውነተኛነት ግን ለዘላለም እንደ ተራሮቹ ይኖራሉ።
ንቃት... የውስጥ ክህደትን የሚያክሽፍ ታላቅ ጋሻ ነው! #Dawit #Amhara ከንጉስች መንደር
#ገሊላ_ደምበጫ‼️
ቀን 02/10/2018 ዓ/ም
ጀብደኛው 99ኛ ክ/ጦር የጠላትን ቅስም በመስበር ያሰብውን ሳያሳካ ወደመጣበት አስፈርጥጦ መልሶታል።
በጀብደኝነታቸው አለም የመሰከረላቸው ወጣትነታቸውን ለአማራ ሕዝብ የሰጡ በወጣት መሪዎች የበለፀገው 99ኛ ክ/ጦር የጠላትን ቅስም በመስበር ወደ ገሊላ ቀጣና የተንቀሳቀሰውን የብርሃኑ ጁላን ግብስብስ ሰራዊት ሙቱን እና ቁስለኛውን በቅጡ ሳይሸክፍ ወደ መጣበት #ደምበጫ ከተማ በአቦሸማኔ ፍጥነት እንዲመለስ አስገድደውታ። ።በዚህ የጠላት እንቅስቃሴ ስረገላ ማርያም ሁለት ሕፃናትን በማቁሰል የአማራ ጠል ስራውንም አሳይቷል::
ነገሩ እንዲህ ነው ከቀኑ 10 ስዓት ገዳማ ጨለማን ትራስ አድርጎ የደምበጫ ወረዳ ታዳጊ ከተማ የሆነችውን #ገሊላን ለመቆጣጠር መነሻውን ደምበጫ ከተማ በማድረግ ወደ ገሊላ ተንቀሳቀሰ ነገር ግን በወጣት የጦር ጠበብቶች የተሞላው 99ኛ ክ/ጦር በአጭር ጊዜ የመከላከል እና መልሶ የማጥቃት ጥበብን በመጠቀም በጠላት ላይ ፈርጣማ ክንዶቹን አሳረፈ ።ከአባል እስከ አማራር እሳት ሲተፉ አመሹ እንኳን ገሊላን ለመቆጣጠር ይዞት የመጣውን ጓዱን ሳይሸክፍ ወደመጣበት የቀበሮ ጉድጓዱ አስፈረጥጠውታል። በዚህ አውደ ውጊያ በርካታ ሰራዊት ሙት እና ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል
©99ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት!
02/10/2018 ዓ.ም
ፍርድ ቤት ቀረበ
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያው
Girmaw Ashebir ዛሬ ፍርድ ቤት አቅርበውት ነበር።
ግርማ ሰሞኑን በአርሲ ክርስቲያኖች ጉዳይ ባሰማው ድምጽ ምክንያት "በሚዲያ ህዝብን ለአመጽ በማነሳሳት" የሚል ክስ ቀርቦበታል።
በፍርድ ቤቱም 7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆበታል።
በአርሲው ጭፍጨፋ ጉዳይ እዛው ባህር ዳር ላይ የመንግስት ባለስልጣናት ሳይቀር ማህበራዊ ሚዲያው ላይ ድምጻቸውን ባሰሙበት ሁኔታ ነው ግርማው ለብቻ ተነጥሎ እንዲጠቃ የተደረገው።
ዩኒቨርሲቲው ሰሞኑን አዘጋጅቶት በነበረው የሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው የመጻህፍ ምርቃት መርሃ ግብር መድረክ መሪ ነበር !!
#አርሲየኦሮቶዶክሳዊያንየደምመሬት
