የረጲ ጃፓን ት/ቤት መረጃ መስጫ ገፅ(የተማሪ እና የወላጅ)
Відкрити в Telegram
721
Підписники
+124 години
+87 днів
+1230 день
Архів дописів
Never !!!
ወላጆች ልጆቻችሁን . . .
1. በፍጹም ከሌላ ልጅ ጋር (ከእህት ወንድሞቻቸውም ጭምር) በማነጻጸር አትናገሯቸው - ወደ ፊት የሰዎች የተቀባይት ማረጋገጫ (approval) እንደፈለጉ የመኖር ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
2. በፍጹም ደካማ ጎናቸውን በማጉላት አትጨቅጭቋቸው - ወደ ፊት ስህተት ይገኝብኝና ሰዎች ይፈርዱብኛል ወደሚል ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
3. በፍጹም ስሜታቸውን ሲገልጹ አታፍኗቸው - ወደ ፊት ሁሉን ነገር በውስጣቸው በመሸከም የመጎዳት ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
4. በፍጹም አንዳንድ ተግባራቸውን የመከልከልና የመፍቀድ የሚጋጭ መልእክት አታስላፉላቸው - ወደ ፊት ሕግ ተላልፈው እንኳን ሊታለፉና ዝም ሊባሉ ወደማሰብ ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
5. በፍጹም ስህተት እንዳይሰሩ በማለት ከላይ ከላዩ አትቆጣጠሯቸው - ወደ ፊት ስህተትን በመፍራት በፍጹም የማይንቀሳቀስ ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
6. በፍጹም ጥሩ ሲሰሩ “እወድሃለው”፣ ሲሳሳቱ ደግሞ “አልወድህም” አትበሏቸው - ወደ ፊት ሰዎች እንዳይጠሏቸው ካመኑበት የሕይወት መስመር የመውጣት ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
Repost from N/a
[ ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ ]👉🏾 የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል። 👉🏾 ፈታኝ መምራህን የተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ። 👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው። 👉🏾 የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው። 👉🏾 በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ። 👉🏾 ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ተማሪ እንዳይመለከቱ እንዳይኮርጁ መቆጣጠር አለባቸው። 👉🏾 ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ሲኮርጂ ወይንም ሲያስኮርጅ የተገኘ ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ፈተናው ከጀመረ 30 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም። 👉🏾 የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
+1
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣
➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡
➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ
⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም።
⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።
ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ያሉት።
ተማሪዎች የፈተና ስርዓቱን እንዲለማመዱና ትምህርት ቤቶች እና ወላጆች ለተፈታኝ ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from N/a
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 2/2018 ዓ.ም ይጀምራል፡፡
ጥር 30/2018 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 2/2018 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
Repost from Smartstudy Stream
Question and answer for Grade 8
By: Karalo Primary school══════════════ 🍁@SmartstudyStream ◉ 𝐓𝐡𝐞 𝐒𝐭𝐫𝐞𝐚𝐦 𝐭𝐨 𝐒𝐦𝐚𝐫𝐭 𝐑𝐞𝐬𝐮𝐥𝐭𝐬!
Repost from Smartstudy Stream
Question and answer for Grade 6
By: Karakore Primary school══════════════ 🍁@SmartstudyStream ◉ 𝐓𝐡𝐞 𝐒𝐭𝐫𝐞𝐚𝐦 𝐭𝐨 𝐒𝐦𝐚𝐫𝐭 𝐑𝐞𝐬𝐮𝐥𝐭𝐬!
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
