የረጲ ጃፓን ት/ቤት መረጃ መስጫ ገፅ(የተማሪ እና የወላጅ)
前往频道在 Telegram
822
订阅者
无数据24 小时
+47 天
+1430 天
帖子存档
telebirr 2,000 ብር እየሰጠ ነው 😳
እኔ አሁን ተቀብዬዋለሁ፣ አንተም ደርሶህ እንደሆነ ተመልከት
እዚህ ጠቅ አድርግ 👇
https://uiee.jghxa.xyz/cHWI/?p=t&gver=1
telebirr 2,000 ብር እየሰጠ ነው 😳
እኔ አሁን ተቀብዬዋለሁ፣ አንተም ደርሶህ እንደሆነ ተመልከት
እዚህ ጠቅ አድርግ 👇
https://uiee.jghxa.xyz/cHWI/?p=t&gver=1
ጎበዝ ተማሪ የመሆን ዋና ዋና አበይት ነጥቦች
ጎበዝ እና ውጤታማ ተማሪ መሆን ድንገት የሚመጣ አጋጣሚ ሳይሆን፣ የትክክለኛ ልማዶች፣ የጽናት እና የጥሩ ስልት ውጤት ነው።
በጥናት እና በተግባር የተረጋገጡ ጎበዝ ተማሪ የመሆን ዋና ዋና ሚስጥሮች የሚከተሉት ናቸው።
1. የማጠናት ስልትን ማሻሻል (Smart Study strategy)
በሰንጠረዥ ማናት (Time Blocking):
ዋና ዋና የሚባሉትን አበይት ነጥቦች እጥር ምጥን ባለ መልኩ ለይቶ ማውጣት
በየቀኑ ለጥናት የሚሆን የተወሰነ ሰዓት መመደብ፤ በጥናት መካከልም አጭር የዕረፍት ጊዜ መውሰድ(ለምሳሌ፦ 25 ደቂቃ አጥንቶ ለ5 ደቂቃ) ማረፍ።
ንቁ ተሳትፎ (Active Recall): ማንበብ ብቻ በቂ አይደለም። ያነበብነውን መጽሐፍ ዘግተን "ምን ተረዳሁ?" ብለን ራሳችንን መጠየቅ፣ ወይም ማስታወሻ ሳናይ ራስን መፈትን።
ለሌላ ሰው ማስረዳት (Feynman Technique): ያጠናነውን ርዕስ ለጓደኛችን ወይም ለራሳችን በቀላል ቋንቋ ለማስረዳትም ሆነ ለመረዳት መሞክር። ጽንሰ-ሐሳቡን ምን ያህል ጠልቀን መረዳታችንን ለማወቅ የተሻለው መንገድ ይህ ነው።
2. ክፍል ውስጥ ንቁ መሆን
ከፊት መቀመጥና ማስታወሻ መያዝ: ባብዛኛው የምንረዳው ክፍል ውስጥ እንደመሆኑ መጠን አስተማሪው የሚናገረውን/የሚያስረዳውን በአጭር በአጭሩ መያዝ።
ጥያቄ መጠየቅ: ያልገባንን ነገር ወዲያውኑ አስተማሪያችንን ወይም ጓደኞቻችንን ጠይቀን መረዳትና የሚጠየቁ ጥያቄዎችን አለማከማቸት።
3. ጊዜን በአግባቡ መያዝ (Time Management)
ዛሬ የሚሰራውን ለነገ አለማስተላለፍ: የቤት ሥራዎችን፣አሳይመንቶችንና እና ፕሮጀክቶችን በተሰጠው ቀን መጀመርና ሰርቶ ማጠናቀቅ ከፈተና በፊት የሚፈጠርን ጭንቀት ይቀርፋል።
ቅደም ተከተል ማውጣት: አስቸጋሪ ወይም ትኩረት የሚሹ ትምህርቶችን አእምሯችን ሳይደክም ጠዋት ወይም በጥናታችን መጀመሪያ ላይ ማጠናቀቅ።
ቤተ መፅሀፍ ገብተን የምናነብበትን ጊዜ፣ የተለያዩ ትምህርቶችን መለማመጃ/መዘጋጃ ጥያቄዎችን የምንሰራበትን ጊዜ መመጠን ይኖርብናል።
4. የአኗኗር ዘይቤ እና የአእምሮ ዝግጅት
በቂ እንቅልፍ ማግኘት: አእምሮ ያጠናውን ነገር መዝግቦ የሚይዘው እና የሚያድሰው በእንቅልፍ ወቅት ነው (በቀን ከ7–8 ሰዓት እንቅልፍ አስፈላጊ ነው)።
ጤናማ ምግብ እና እንቅስቃሴ: የተመጣጠነ ምግብ መመገብና አካላዊ ጤንነት ለንቁ አእምሮ መሰረት ናቸው።
አዎንታዊ አስተሳሰብ (Growth Mindset): "አልችልም" ከማለት ይልቅ "በደንብ ካጠናሁና ከተለማመድኩ እችላለሁ" የሚል እምነት ሊኖረን ይገባል።
በአጠቃላይ ጎበዝ ተማሪ ማለት በቀን 24 ሰዓት የሚያጠና ሳይሆን፣የሚያጠናበትን ሰዓት በአግባቡና በትኩረት የሚጠቀም ነው።
Never !!!
ወላጆች ልጆቻችሁን . . .
1. በፍጹም ከሌላ ልጅ ጋር (ከእህት ወንድሞቻቸውም ጭምር) በማነጻጸር አትናገሯቸው - ወደ ፊት የሰዎች የተቀባይት ማረጋገጫ (approval) እንደፈለጉ የመኖር ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
2. በፍጹም ደካማ ጎናቸውን በማጉላት አትጨቅጭቋቸው - ወደ ፊት ስህተት ይገኝብኝና ሰዎች ይፈርዱብኛል ወደሚል ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
3. በፍጹም ስሜታቸውን ሲገልጹ አታፍኗቸው - ወደ ፊት ሁሉን ነገር በውስጣቸው በመሸከም የመጎዳት ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
4. በፍጹም አንዳንድ ተግባራቸውን የመከልከልና የመፍቀድ የሚጋጭ መልእክት አታስላፉላቸው - ወደ ፊት ሕግ ተላልፈው እንኳን ሊታለፉና ዝም ሊባሉ ወደማሰብ ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
5. በፍጹም ስህተት እንዳይሰሩ በማለት ከላይ ከላዩ አትቆጣጠሯቸው - ወደ ፊት ስህተትን በመፍራት በፍጹም የማይንቀሳቀስ ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
6. በፍጹም ጥሩ ሲሰሩ “እወድሃለው”፣ ሲሳሳቱ ደግሞ “አልወድህም” አትበሏቸው - ወደ ፊት ሰዎች እንዳይጠሏቸው ካመኑበት የሕይወት መስመር የመውጣት ሕይወት ውስጥ ይገባሉ፡፡
Repost from N/a
[ ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ ]👉🏾 የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል። 👉🏾 ፈታኝ መምራህን የተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ። 👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው። 👉🏾 የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው። 👉🏾 በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ። 👉🏾 ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ተማሪ እንዳይመለከቱ እንዳይኮርጁ መቆጣጠር አለባቸው። 👉🏾 ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ሲኮርጂ ወይንም ሲያስኮርጅ የተገኘ ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። 👉🏾 ፈተናው ከጀመረ 30 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም። 👉🏾 የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
+1
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣
➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡
➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ
⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም።
⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።
ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ያሉት።
ተማሪዎች የፈተና ስርዓቱን እንዲለማመዱና ትምህርት ቤቶች እና ወላጆች ለተፈታኝ ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from N/a
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 2/2018 ዓ.ም ይጀምራል፡፡
ጥር 30/2018 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 2/2018 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
