uk
Feedback
Ethio-Universities Salafi Community(EUSaCo)

Ethio-Universities Salafi Community(EUSaCo)

Відкрити в Telegram

የዚህ Community ዓላማ በመላው ሀገሪቱ የሚገኝ ሰለፊይ የዩንቨርስቲ፣ኮሌጅ እና ሌሎች የትምህርት ተቋማት ኮሚኒቲን በአንድ አስተሳስሮ ትክክለኛውን እስላማዊ አስተምህሮ ለዑማው ማድረስ ነው። ኑ ሀቅን ከባለቤቶቹ እንማር! ገንቢ አስተያየትና ጥቆማዎትን @EUSaCofeedbackBot ያድርሱን። #ኢዩሰኮ #EUSaCo

Показати більше
3 437
Підписники
+124 години
+127 днів
+4630 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
липень '26
липень '26
+34
в 0 каналах
червень '26
+117
в 0 каналах
Get PRO
травень '26
+113
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+124
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+109
в 2 каналах
Get PRO
лютий '26
+197
в 11 каналах
Get PRO
січень '26
+59
в 1 каналах
Get PRO
грудень '25
+116
в 13 каналах
Get PRO
листопад '25
+65
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '25
+170
в 9 каналах
Get PRO
вересень '25
+34
в 2 каналах
Get PRO
серпень '25
+75
в 8 каналах
Get PRO
липень '25
+61
в 14 каналах
Get PRO
червень '25
+47
в 3 каналах
Get PRO
травень '25
+73
в 6 каналах
Get PRO
квітень '25
+318
в 35 каналах
Get PRO
березень '25
+77
в 5 каналах
Get PRO
лютий '25
+121
в 21 каналах
Get PRO
січень '25
+474
в 28 каналах
Get PRO
грудень '24
+181
в 4 каналах
Get PRO
листопад '24
+265
в 15 каналах
Get PRO
жовтень '24
+242
в 10 каналах
Get PRO
вересень '24
+258
в 16 каналах
Get PRO
серпень '24
+318
в 13 каналах
Get PRO
липень '24
+1 446
в 9 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
10 липня+3
09 липня+4
08 липня+5
07 липня+4
06 липня+2
05 липня+1
04 липня+6
03 липня+1
02 липня+5
01 липня+3
Дописи каналу
Repost from N/a
🔖 ልዩ የደዕዋ ፕሮግራም! — እነሆ ዛሬ ጁሙዓ ሐምሌ 3 - 2018 «በሰለፊዮች መገናኛ» ግሩፕ እንደ ወትሮው የደዕዋ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል!። 💺ተጋባዥ እንግዶቻችን፦ 🎙ኡስታዝ ዐብዱል-ቃዲር አዳ
🔖 ልዩ የደዕዋ ፕሮግራም! — እነሆ ዛሬ ጁሙዓ ሐምሌ 3 - 2018 «በሰለፊዮች መገናኛ» ግሩፕ እንደ ወትሮው የደዕዋ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል!።
💺ተጋባዥ እንግዶቻችን፦
🎙ኡስታዝ ዐብዱል-ቃዲር አዳማ -ሐፊዞሁ'ሏህ- ● ርእስ፦ ሸይኽ ዐብዱል-ሐሚድ በሚያውቋቸውና በማያውቋቸው ሰዎች መሃከል⁉️ ● ርእስ፦ የሐዲሥ አልቀበል ባዮች አደጋ! 🎙ኡስታዝ አብራር አወል ከአዲስአበባ -ሐፊዞሁ'ሏህ- || ግጥም ይኖረናል -ኢንሻአ'ሏህ-ሰዓት ፦ ከምሽቱ በኢትዮ 3:00 በሱዑዲያ 9:00 በኢማራት 10:00 አይለፋችሁ!። #የመገናኛውን_ግሩፕ_ተቀላቀሉ👇 https://t.me/Multeqa_Ahlissuneh https://t.me/Multeqa_Ahlissuneh

2
ለአሏህ እጅ ማጽደቅና አህባሽ ~ join #telegram ቻናል https://t.me/abuabdurahmen
166
3
እስካሁን በሰለፊይ መሻይኽ እና አስታዞች ተቀርተው በ"Sakinah App" የተዘጋጁ አፕሊኬሽኖችን እናጋራችሁ!!  እናንተም መቅራት የምትፈልጉትን ኪታብ ስም በመጫን አፕሊኬሽኑን ማግኘት ትችላላችሁ!! ↪️  የኪታቡ ስም፦  ሸርሁ ኡሱሊ አሲታህ       🎙በኡስታዝ ሰዕድ ዐብዱለጢፍ                  አላህ ይጠብቀዉ ↪️ የኪታቡ ስም፦ ኪታቡ ተውሂድ ሊል ኢማም መሀመድ ኢብን ዐብዲልወሃብ       🎙በኡስታዝ ሰዕድ ዐብዱለጢፍ                  አላህ ይጠብቀዉ ↪️ የኪታቡ ስም፦ ኹላሶቱ ኑሪል የቂን      🎙 ኡስታዝ አቡ አነስ ሙሐመድ አሚን አላህ ይጠብቀው ↪️የኪታቡ ስም፦ ሚንሓጅ አል ፊርቀቱ ናጂያህ      🎙ኡስታዝ ኪርማኒ አቡ ሀሰን አላህ ይጠብቀው ↪️ የኪታቡ ስም፦ አስባቡ ሰባት ዓላ መንሀጅ ሰለፊ ሷሊህ      🎙ኡስታዝ ሰዕድ ዐብዱለጢፍ                  አላህ ይጠብቀዉ ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፍይ ይሁኑ! 📢 መሰል  ቂርአቶችን በአፕ ለማሰራት የሚከተለውን አድራሻ ይጠቀሙ👇👇👇 @aaussjfeedback_bot @sakinah_app
337
4
قيـل لابـن الـمـبارك : ما خير مـا أعطـي الـرجـل ؟ قـال : غريزة عقــل قيـل : فإن لم يكـن .. قـال : أدب حــــــــــــــسـن . قيـل : فإن لم يكـن .. قال : أخ صالح يسـتشيــره . قيـل : فإن لم يكـن .. قال : صمـت طـويـــــــــــل قيـل : فإن لم يكـن .. قـال: مـوت عـاجــــــــــل. (روضة العقلاء 34)
516
5
♦️| አዲስ ሙሓደራ ከ"ملتقى" ቁ.019 ● ርእስ፦ ግዜን በአግባቡ መጠቀም! 🎙ኡስታዝ ሰይፉዲን ሣኒ ከወላይታ -ሐፊዞሁ'ሏህ- 🕌 በሰለፊዮች መገናኛ ግሩፕ የተደረገ አሳሳቢ ሙሓደራ! 🗓 ሰኔ 5 - 2018 || የመገናኛው ግሩፕ፦ t.me/Multeqa_Ahlissuneh t.me/Multeqa_Ahlissuneh
591
6
🎉Congratulations🎉 ⚜️ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ጊዜያቶች በኋላ ለዚህ ያበቃን አሏህ ላቅ ያለ ምስጋና ይገባዋል!! አልሃምዱሊላህ! ✨ በኢትዮጵያ የምትገኙ ተመራቂ ሰለፊዮች በሙሉ እንኳን ደ
🎉Congratulations🎉 ⚜️ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ጊዜያቶች በኋላ ለዚህ ያበቃን አሏህ ላቅ ያለ ምስጋና ይገባዋል!! አልሃምዱሊላህ! ✨ በኢትዮጵያ የምትገኙ ተመራቂ ሰለፊዮች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ። 📖 የተማርነዉን እዉቀት አሏህ በሚወደዉ መልኩ ኡማዉን ለማገልገል ልናዉለዉ ይገባል!! 👉በት/ት ላይ ያላችሁ ደግሞ በዲን እና በዱንያ የተሻለ ነገር ይዞ ለማዉጣት ጥረት እንድታደርጉ እንዲሁም እኛ ያጣናቸዉን ነገሮች አሳክታችሁ እንድትወጡ አደራ ለማለት እወዳለሁ። 🎉ألف مبروك التخرج🎉 🎓Congratulations🎓 🎆እንኳን ደስ አላችሁ🎆 ✍️አቡ አብዱረህማን (አብዱሰላም) ከባ/ዳር https://t.me/BDU_Selefiyah_Students https://t.me/BDU_Selefiyah_Students
644
7
💡ፆመኛ ሲያፈጥር የሚለው ዱዓ!💡   <======================> 🥛ذَهَبَ الظَّمَأُ وَابْتَلَّتِ الْعُرُوْقُ وَثَبَتَ اْلأَجْرُ إِنْ شَاءَ اللهُ. 🥛ዘሀበ ዞመኡ ወበተለቲል ዑሩቁ ወሰበተል አጅሩ ኢንሻ አላህ                 💈ትርጉም፦ «ጥም ተወገደ የደም ሥር ተብላላ የአላህ ፈቃድ ከሆነ ምንዳውም ፀደቀ ማለት ነው»። ➩ሌላም፦ ➴➴➴➴➴ 🥛اَللَّهُمَّ إِنِّيْ أَسْأَلُكَ بِرَحْمَتِكَ الَّتِيْ وَسِعَتْ كُلَّ شَيْءٍ أَنْ تَغْفِرَ لِيْ. 🥛አላሁመ ኢኒ አሰአሉከ ቢረህመቲከ ለቲ ወሲዓት ኩለ ሸይኢን አን ተግፊረሊ     💈ትርጉም፦ አላህ ሆይ! ምህረትን ትለግሰኝ ዘንድ ሁሉንም ነገር ባዳረሰችው እዝነትህ እማፀንሐለሁ። 📱⇘⇘⇘⇘⇘ https://t.me/Durusu_Abu_Anes https://t.me/Durusu_Abu_Anes https://t.me/Durusu_Abu_Anes
511
8
🔶#የኻሊድ ክብሮምን ዝንባሌ ግልፅ ማድረግ፣ ከጥመቱ ማስጠንቀቅና ቁርኣኒይ ከሚባሉት ጠማማ ተጣሪ (ሰባኪዎች) መሆኑን ማጋለጥ 🔶በአዲስ አበባ አል- ወሰጢየህ መርከዝ እና መድረሳ የተደረገ ሙሐደራ። 🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ) 📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ 👇👇👇 🌐 https://t.me/shakirsultan
375
9
እንዲሁ በጣም የሚያስገርመው ፡  አንዳንድ ሴቶች እና ወንዶች ከአጅነብይ (ከባእድ) ጋር በማውራት የሚስተዋለው ቸልተኛነት ነው፡፡ አስገዳጅ ነገር ሳይገጥም አጅነብይ የሆነችውን ሴት ያወራታል ፣  ያሳስቃታል እርሷም ታሳስቀዋለች በንግግሯ ይደሰታል፡፡ አንዳንድ ሴቶችም አስገዳጅ ነገር  ሳይገጥም አጅነብይ ከሆነ ወንድ ጋር ያወራሉ፡፡ በለሰለሰ ቃላት ፣  ደስ የሚል ቃል ወደርሱ ትወረውራለች፡፡  በልቡ በሽታ ያለበት ሰው ይከጅላል፡፡ በተለይም በማህበራዊ ድረ ገጽ፡፡  በትክክለኛ ሐዲስ የአላህ መልክተኛ - ዓለይሂሶለቱ ወሰላም - እንዲህ ብለዋል :- إن المرأة عورة ، فإذا خرجت استشرفها الشيطان “ሴት አውረት (አካሏ ሁሉ መታየት የማይገባት) ነች ፣ (በአደባባይ) ከወጣች ሸይጧን ይቀርባታል” ሙስሊም በሶሂህ ሐዲስ  የሚከተለውን ዘግቧል ፡ إن المرأة تقبل في صورة شيطان ، وتدبر في صورة شيطان “ሴት ስትመጣ በሸይጧን ምስል ትመጣለች፡፡ ስትሄድም በሸይጧን ምስል ትሄዳለች፡፡” ሁሉም ሙስሊም አላህን ሊፈራ ግዴታ አለበት፡፡ ባለትዳሮች ሚስጢራቸውን በአደባባይ ማሰራጨት ሳይሆን ችግራቸውን ከቤተሰብ ጋር ሆነው በትእግስት እና በጥበብ ተወያይተው መፍታት አለባቸው፡፡  ሙስሊም ወንድሜ ሆይ!   በአንተ እና በሚስትህ መካከል አለመግባባት ከተከሰተ ከማንም ጋር ግንኙነት አታድርግ ቤተሰቦችህ እንዲገኙ በማድረግ  በጥበብ ፣  በትግስት ፣  በዱዓ መፍታት ትችላለህ፡፡ ለአንተ ቅርብ እና አዛኞች የአንተ እና የሚስትህ ቤተሰቦች በመሆናቸው በመካከላችሁ ተገኝተ  ጉዳያችሁን እንዲፈቱ  አድርግ፡፡ ይህ ካልተሳካ ወደሸሪዓ ዳኞች ጉዳዩን አቅርብ፡፡  ይህ ነው አላህ የሚወድልህ ፣ የሚስትህን ሚስጢር አትበትን ፣ በቁርዓን እና በሐዲስ ጉዳይህን ፍታ - በዱንያና በአኼራ ስኬታማ  ትሆናለህና፡፡ ሙስሊም እህቴ ሆይ!  ከባልሽ ጋር አለመግባባት ከተከሰተ  አላህን ፍሪ ፣ ታገሽ  ፣ ባልሽን በመልካም ታዘዥ፡፡  አላህ ከፍ ያደርግሻል፡፡  ከአንች ዘንድ ያለውን ይወድልሻል፡፡ የሂዎትሽ ሁኔታ ካልተስተካከለ ቤተሰቦችሽን አማክሪ እንጅ ከዚያም ከዚህም ጋር አትገናኝ - ከአላህ ቁጣ ላይ ትወድቂያለሽና፡፡ በባልና በሚስት ጉዳይ ፈትዋ የሚሰጡ ሰዎች አላህን ይፍሩ፡፡ በሁለቱ መካከል በተፈጠረው ጉዳይ የተሰጣቸውን የሸሪዓ ድንበር ሊያውቁ ይገባል፡፡ ፈትዋ የሚሰጡ ሰዎች በባልና ሚስት እርቅ ጉዳይ ከቤተሰቦች የበለጡ አይደሉም፡፡ አላህ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡ ባለትዳሮችን ባልና ሚስትን በማስማማት አላህ በቁርዓኑ ያወሳው ቤተሰብን ነው፡፡  ባለትዳሮችን መምከር ፣  ሸሪዓዊ ህጉን ግልጽ ማድረግ የሚከለክል ነገር የለውም፡፡  በፍች ጉዳይ ግን የአንዱን ወገን ብቻ መስማትና ጣልቃ መግባት ተገቢ አይደለም፡፡  የሰዎችን ቤት ሚስጢራቸውንም መከታትልና መፈተሽ አይፈቀድም፡፡ ይህ የቆሻሻ ልቦች በሽታ ነው፡፡ ሙስሊሞች ከእንዲህ አይነቱ መጽዳት ግዴታ አለባቸው፡፡  ነብዩ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - እንዲህ ብለዋል:- يا معشر من آمن بلسانه ولم يدخل الإيمان قلبه ، لا تغتابون المسلمين ، ولا تتبعوا عوراتهم ، فإنه من تتبع عورة أخيه المسلم ، تتبع الله عورته ، ومن تتبع الله عورته ، يفضحه ولو في جوف بيته  “በምላሳችሁ ያመናችሁ ፣ እምነት በልባችሁ ያልገባ ሰዎች ሆይ! ሙስሊሞችን አትሙ ፣ ነውራቸውንም አትከታተሉ ፣ የሙስሊም ወንድሙን ነውር የሚከታተል የእርሱን ነውር አላህ ይከታተለዋል፡፡ የእርሱን ነውር አላህ የተከታተለው በቤቱ ውስጥ እንኳ ቢሆን ያጋልጠዋል፡፡” ሸይኽ ብን ኡሰይሚን - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ጥያቄ ተጠየቁ ፡ “የቤቶቻቸውን  ጉዳይ ፣ ስለትዳራቸው ሒዎት ፣ ከባሎቻቸው ጋር ያለውን ጉዳይ ለቅርብ ዘመዶቻቸው ፣  ለጓደኞቻቸው ማውራትና ማሰራጨት በአንዳንድ ሴቶች ላይ ይበዛል፡፡  ከእነዚህ ወሬዎች ከፊሉ የቤት ሚስጢር ናቸው፡፡  ባል እንዲወራ አይፈልግም፡፡ ባል ይህን የቤት ሚስጢር  አንድም ሰው እንዲያውቅ አይፈልግም፡፡ ሚስጢርን ከቤት ውጭ  በማሰራጨት ወይም ለአንዳንድ የቤት ሰዎች በማውራት ላይ የተሰማሩ  ሴቶች ፍርድ ምንድን ነው? መልስ ፡  የቤትን ወሬ ፣ የትዳር ሂዎታቸውን ለቅርብ ዘመድ ፣ ለጓደኛ የሚያወሩ አንዳንድ ሴቶች ይህ ተግባራቸው ሐራም ነው፡፡ ማንኛዋም ሴት  የቤቷን ሚስጢር ወይም ከባሏ ጋር ያለውን ሁኔታ ለአንድም አካል ማውራት ወይም ማሰራጨት አይገባትም፡፡  አላህ የሚከተለውን ተናግሯል ፡ - فَالصَّالِحَاتُ قَانِتَاتٌ حَافِظَاتٌ لِّلْغَيْبِ بِمَا حَفِظَ اللَّهُ ۚ                    “መልካሞቹ ሴቶች (ለባሎቻቸው) ታዛዦች ፣ አላህ ባስጠበቀው (እንዲጠበቅ ባዘዘው) ነገር ሩቅን (ባሎቻቸው በሌሉበት አፍረተ ገላቸውን ፣ ንብረታቸውን ...) ጠባቂዎች  ናቸው፡፡”  (ኒሳእ : 35) ነብዩ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - የሚከተለውን ተናግረዋል :- شر الناس منزلة عند الله يوم القيامة الرجل يفضي إلى المرآة وتفضي إليه ثم ينشر سرها" “የትንሳኤ ቀን ከአላህ ዘንድ መጥፎ ሰው ብሎ ማለት ባል ለሚስቱ ሚስጢር ይነግራታል ፣ ሚስት ለባሏ ሚስጢር ትነግረዋለች ከዚያም ሚስጢሯን የሚያሰራጭ ነው፡፡” انتهى من فتاوى إسلامية (211212\3)    በዶክተር ሸይኽ ሁሰይን ብን ሙሐመድ  https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة
761
10
🔷ከአንዳንድ የሐበሻ ሰዎች የሚስተዋለው አስቀያሚ ባህሪ የባልና የሚስትን ሚስጢር ማሰራጨት ክቡር በሆነችው የመካ ከተማ የክፍለ ዘመንን ሩብ የሚቃረብ ቆይታ አድርጊያለሁ - አሏህ ልቅና ይስጣት፡፡ ከፍ ያለ ምስጋናም ለአላህ ይገባው፡፡  የሱዑዲ ፣ የየመን ፣ የኩዌት ፣ የአልጀሪያ ፣ የህንድ ፣ የቱኒዚያ ፣ የፓኪስታን ፣ የሱዳንና የሌላም አገር ዜግነት ካላቸው ምርጥ ሰለፍይ ወንድሞች ጋር ተዋውቂያለሁ፡፡ ልክ በእኛ ቤት እንደሚከሰተው በእነርሱም ቤት በባልና ሚስት መካከል ግጭት ፣ አለመግባባት ይከሰታል፡፡  ከእነርሱ መካከል ሚስቱን የፈታ ፣  ከሚስቱ ጋር የተለያየም አለ፡፡ እንዲህ አይነቱን ድርጊት ቤት ይቁጠረው ፤ በተለይም ከሱዑዲ ዜጎች ዘንድ አዲስ ነገር  አይደለም፡፡  በጣም የሚገርመኝ ባል ከሚስቱ ጋር ያለውን አለመግባባትም ይሁን የቤት ሚስጢራቸውን ይፋ ሲያደርጉ አለማወቄ ነው፡፡ ግጭት ከተፈጠረም ባል ሚስቱን ይመክራል ፣ አላህ ባዘዘው መሰረት  ስርዓት በማስያዝ ላይ ይሰማራል፡፡ አላህ በተከበረው ቁርዓን እንዲህ ብሏል :- وَاللَّاتِي تَخَافُونَ نُشُوزَهُنَّ فَعِظُوهُنَّ وَاهْجُرُوهُنَّ فِي الْمَضَاجِعِ وَاضْرِبُوهُنَّ ۖ                     “እነዚያንም ማመጸቸውን የምታውቁትን ገስጿቸው፡፡ (ግሰጻው ካላስተካከላቸው) ከምኝታዎችም ተለዩዋቸው፡፡ (ከመኝታ መለየታችሁ ካላስተካከላቸው)  ምቱዋቸውም (ጉዳት ሳታደርሱ)፡፡”  (ኒሳእ ፡  35)   ሚስት ተመክራ ወደትክክለኛው ጎዳና ፣ ወደአቅሏ መመለስ ካልቻለችና በአመጸኝነቷ ከቀጠለች  የሁለቱ ባልና ሚስት ቤተሰቦች ጣልቃ ይገባሉ፡፡ ቤተሰቦች ጉዳዩን ካልፈቱትና እርቅ ካልመጣ ጉዳያቸውን ወደሸሪዓ ፍርድ ቤት ይወስዱታል፡፡ በፍርድ ቤቱ ውስጥ የምክክር ኮሚቴ የሚባል አለ፡፡ ኮሚቴው እንዲስማሙ የምክር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ይህ ካልሆነ  ጉዳያቸው ወደፍርድ ቤት ቀርቦ ከብዙ ጥናት ፣ ክርክር ፣ ምክር በኋላ ፍርድ ቤቱ አላህ በሚከተለው አንቀጽ በተናገረው መሰረት   የመጨረሻ ሸሪዓዊ ብይን ይሰጣል፡፡ وَإِن يَتَفَرَّقَا يُغْنِ اللَّهُ كُلًّا مِّن سَعَتِهِ ۚ وَكَانَ اللَّهُ وَاسِعًا حَكِيمًا “ቢለያዩም (ቢፋቱ) ፣ አላህ ሁሉንም በችሮታው ያከብራቸዋል፡፡ አላህም ችሮታው ሰፊ ፣ ጥበበኛ ነው፡፡” (ኒሳእ ፡ 130) ይህ ነው በሱዑዲ የተመለከትሁት የአሊሞችና የሙፍቲዎች ሚና በሁለት ባለትዳሮች መካከል አለመግባባት ከተከሰተ መምከር እንጅ ጦላቅ እንዲወድቅ  ብይን መስጠት የለባቸውም - ምክንያቱም ይህ ባልና ሚስቶች በአካል ተገኝተው እነርሱን ማድመጥ ፣ ከዚያም ብይን መስጠት ይፈልጋልና፡፡ በዚህ ምክንያት የሱኡዲ ኡለሞች ለምሳሌ ፡ - ኢብን ባዝ ፣ ኢብን ኡሰይሚን ፣ ፈውዛን  እና ሌሎችም ኡለሞች እንዲሁም የሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ በባል እና ሚስት አለመግባባት ፣ ጦላቅን በመጠል  ዙሪያ  ጥያቄ ሲቀርብላቸው ፣ ሸሪዓዊ የሆነውን ህግጋት ማብራራት ፣  የምክር አገልግሎት መስጠት ፣ ጉዳያቸውን ወደሸሪዓ ፍርድ ቤት ዳኞች እንዲያቀርቡ መምከር  እንጅ  በፍጹም ፈትዋ አይሰጡም፡፡ በጣም የሚገርመው አንዳንድ የሐበሻ ሰዎች … አንድ ባል ከሚሰቱ ጋር ከተጋጨ ሚስጢሯን ላለፊ አግዳሚው ሁሉ በአደባባይ ያሰራጫል፡፡ ሚስቱም እንደዚሁ የባሏን ሚስጢር ለጎረቤት ፣ ለጓደኛ ፣ በየመድረሳው ታሰራጫለች፡፡ በዚህ ምክንያት በመካከላቸው ቂምና ጥላቻ ይወለዳል፡፡  ሁለቱም አንዱ አንዱን ለመበቀል ይፈልጋሉ፡፡ ሁለቱም ሐቁ ከእኔ ጋር ነው ብለው ይሞግታሉ፡፡  ችግራቸውን ለመፍታት  ከቁርዓንና ከሐዲስ ህግ ጋር በተቃረኑ ጊዜ  አላህ ከማይወደው ተግባር ለይ ይወድቃሉ፡፡ ሱናን መቃረን ለልቦና ጭንቀት ፣ ለነፍስ አለመረጋጋት  ምክንያት ይሆናል፡፡   አንዲት ሴት ከባሏ ጋር የተፈጠረውን አለመግባባት በስልክ ነግራኝ ነበር፡፡ የባሏን ችግር ለብዙ ወንዶችና ሴቶች እንዳወራች አመነችልኝ - ሱብሃን አላህ -  ይህች ሴት - ተቆጣጣሪዋ አላህ ሲሆን - ከደጋግ ሰለፍይ ሴቶች መካከል ናት ብዬ እገምታለሁ፡፡    “አንች ሀራም ከሆነው አሜት ወድቀሻል ፤  የአላህና የረሱልን ህግ ጥሰሻል ፣  የባልና ሚስት ችግር መፍትሄው በባል እጅ ነው ፤ እርሱ ካልፈታው  ሁሴን ወይም ሌላው ሳይሆን አላህ እንደነገረን ከሁለቱም ወገን ቅርብ ዘመዶች ጣልቃ ይገባሉ፡፡  وَإِنْ خِفْتُمْ شِقَاقَ بَيْنِهِمَا فَابْعَثُوا حَكَمًا مِّنْ أَهْلِهِ وَحَكَمًا مِّنْ أَهْلِهَا إِن يُرِيدَا إِصْلَاحًا يُوَفِّقِ اللَّهُ بَيْنَهُمَا ۗ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلِيمًا خَبِيرًا                             (እናንተ አማኞች!) የመካከላቸውንም (የባልና የሚስትን) ጭቅጭቅ ብታውቁ ፤ ከቤተሰቦቹ ሽማግሌን ፣ ከቤተሰቦቿም ሽማግሌን ላኩ፡፡ (ሽማግሌዎቹ) ማስታረቅን ቢሹ አላህ በመካከላቸው (ባልና ሚስትን) ያስማማል - አላህ ግልጽን ዐዋቂ ፣ ውስጥንም ዐዋቂ ነውና፡፡  (ኒሳእ ፡ 35) ችግሩ ከአቅም በላይ ከሆነ - ከተገኘ ወደሸሪአ ፍርድ ቤት መመለስ ነው” አልኳት፡፡ በጣም የደነገጥኩት ደግሞ በሁለቱ ግጭት መካከል አጅነብይ ወንድ ጣልቃ ገብቶ ባሏ ለእርሷ ያወራውን ለአጅነብዩ  እንደምትናገር ፣ እርሷ ለባሏ ያወራችውን ባል ለዚህ አጅነብይ እንደሚናገር በነገረችኝ ጊዜ ነው -  ሱብሃን አላህ - መፍትሄ ሰጭ የሆነውን ሱና በመቃረናቸው ምክንያት በባልና ሚስጥ መካከል ጥላቻው ቂሙ ጨመረ፡፡  እኔም ገሰጽኋት ፣ በአላህ አስፈራራኋት ፣ የባሏን ሚስጢር ከማሰራጨት መቆጠብ እንዳለባት ፣ ባሏን በመልካም መታዘዝ እንዳለባት - ከዚህ አልፎ ነገሩ በጣም የሚያጨናንቃት ከሆነ  ከቤተሰቦቿ ጋር እንድትገናኝ መከርኋት፡፡  ይህ ቆሻሻ የሆነ ባህል በሐበሻ ምድር በሙስሊሞች መካከል ከየት መጦ እንደገባ አላውቅም፡፡ ከእምነት ቁርጠኝነት ማነስና በመቀላቀል የመጣ ችግር ነው ብየ እገምታለሁ፡፡ በጣም የሚያስገርመው ነገር ፡  አንዳንድ ፈተና ላይ የወደቁ በሰዎች ጉዳይ  ጣልቃ የሚገቡ  ፊት ለፊት የምናያቸው ሰዎች አሉ፡፡ በማይመለከታቸው ጉዳይ ለሚስት ስለባሏ  የግብረስጋ ግንኙነትና ጥንካሬ  ይጠይቃሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ሚስት በባል ላይ እንድታምጽ ፣  ቀልቧ በእርሱ ላይ  እንዲሻክር ያደርጋሉ፡፡በቀላሉ ያበላሹዋታል ፤  ባሏን እንድትፈታ ያነሳሳሉ፡፡ ነብዩ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - እንዲህ ብለዋል  ፡ ليس منا من خبب امرأة على زوجها “ሚስት በባል ላይ (እንድታምጽ) የሚያነሳሳ (የሚያበላሽ) ከእኛ አይደለም” ይህ ፈተና ላይ የወደቀ ጠያቂ የሸይጧን ስራ አስፈጻሚ ነው፡፡ በማንኛውም ሁኔታ በባለትዳሮች መካከል ነፍሱን ጣልቃ ሊያስገባ  አይገባውም፡፡  ከእርሱ መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ አንዲት ሴት - ለማንም አካል ሳይሆን - ባሏ የግብረ ስጋ ግንኙነት የማድረግ አቅሙ እንደሌለው ለሸሪዓ ዳኛ ብቻ መናገር ትችላለች፡፡  አንድም አካል ስለዚህ ጉዳይ ሊጠይቃት አየገባም፡፡ ይህ ከስነ ምግባር እጥረትና ከእምነት ቁርጠኝነት ድክመት ነው፡፡ 
574
11
በወንድማችን አቡበከር የሰርግ ፕሮግራም ላይ የተደረገ አንገብጋቢ ሙሓደራ! 🎤 በኡስታዝ ኑራዲስ(አቡል-በያን) ሀፊዘሁላህ ይደመጥ👌
864
12
​بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ ​🚨 አስቸኳይ የጥንቃቄና የማስጠንቀቂያ መልዕክት ከባህር ዳር አባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጅድ! 🚨 ​ውድና የተከበራችሁ የዲናችን እህትና ወንድሞች፤ በአሁኑ ሰዓት የባህር ዳር አባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጅድን የቴሌግራም ግሩፑን ስም፣ዲስክሪፕሽን (Description)  ጽሁፎችን እና ከዚህ በፊት የተለቀቁ ፖስቶችን እንደ ግብአት ተጠቅሞ፣ የተለየ የሐሰት ግሩፕ እና አካውንት ከፍቶ ሰዎችን እያታለለ ብር የሚሰበስብ አጭበርባሪ ግለሰብ እንዳለ ደርሰንበታል። ​ይህ አካል ከቢላል መስጅድ አስተዳደርም ሆነ ከኮሚቴው ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው እና የግል ጥቅሙን የሚያሳድድ አጭበርባሪ ነው። ስለሆነም መላው ሙስሊም ማህበረሰብ የሚከተሉትን ነጥቦች ተገንዝቦ ራሱንና ዲኑን ከማጭበርበር እንዲጠብቅ በጥብቅ እናሳስባለን፡ ​1️⃣ ትክክለኛ እና ሕጋዊ የባንክ አካውንቶቻችን፡ ለባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 11 (አባይ ማዶ) በኢትዮጵያ አህሉሱና እስላማዊ ማህበር ስር ላለው ለቢላል መስጅድ ግዢ እና ግንባታ ማሰባሰቢያ የሚውሉ እውቅና ያላቸው አካውንቶች እነዚህ ብቻ ናቸው፦ ​📌 ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000-742-45-45-45 📌 አቢሲኒያ ባንክ፦ 245566778 📌 ሂጅራ ባንክ፦ 1000-927-373-0001 👥 የአካውንት ስም፦ አሊ ሙሀመድ ፣ ጀማል ሙሀመድ እና አህመድ እስማን ​⚠️ እጅግ በጣም አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ ከነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት ሶስት የባንክ አካውንቶች እና በጋራ ከተከፈቱት ከእነ አሊ ሙሀመድ፣ ጀማል ሙሀመድ እና አህመድ እስማን ስሞች ውጭ ምንም አይነት ሌላ አካውንት የሌለን መሆኑን በድጋሚ እናረጋግጣለን! ​2️⃣ ፍፁም ሊታወቁና ሊጠነቀቁ የሚገቡ የሐሰት መረጃዎች፡ ❌ አብደላ አወል አባቦር (Abidela Awol Ababor) የሚባል ሰው በኮሚቴው ውስጥ የለም! ልጁ ወደ ግሩፑ ሲገቡ ራሱን በዚህ ግሩፕ ስም እያስተዋወቀ እና የራሱን አካውንት በመለጠፍ እያጭበረበረ ይገኛል። 👌👌👌በቢላል መስጅድ ስም በአብደላ አወል አባቦር ስም የተከፈተ ምንም አይነት አካውንት የለም! ​❌ የአዋሽ ባንክ አካውንት ፍፁም የለንም! ይህ አጭበርባሪ አካል በአዋሽ ባንክ አካውንት ከፍቶ ገንዘብ እየሰበሰበ ይገኛል። እኛ ግን በአዋሽ ባንክ ምንም አይነት አካውንት የሌለን መሆኑን ህዝቡ በደንብ እንዲያውቅና እርግጠኛ እንዲሆን እንፈልጋለን። ​✅ የሜምበር (አባላት) ቁጥር ልዩነት፦ ትክክለኛው የቢላል መስጅድ ግሩፓችን በአሁኑ ሰዓት 16,045 (አስራ ስድስት ሺህ አርባ አምስት) ሜምበር አለው (ይህ ቁጥር አባላት ሲገቡና ሲወጡ መጠኑ ከፍና ዝቅ ሊል ይችላል)። የዚህ አጭበርባሪ ግሩፕ ግን 3 ሺህ አካባቢ ብቻ አባላት ያሉት በመሆኑ በዚህ የቁጥር ልዩነት በቀላሉ መለየት ትችላላችሁ። ​3️⃣ ለተጨማሪ መረጃ እነዚህን የኮሚቴ ስልክ ቁጥሮች ይጠቀሙ፡ ማንኛውንም መረጃ ለማጣራትና ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ በሚከተሉት የእውነተኛው ኮሚቴ ስልክ ቁጥሮች ላይ በነፃነት መደወል ይችላሉ፦ 📞 0918720696 - አሊ ሙሀመድ 📞 0918702221 - ጀማል ሙሀመድ(Dr) 📞 0920257036 - ሰኢድ መህሙድ (telegram owner) ​4️⃣ የበኩላችሁን አድርጉ (ሪፖርት አድርጉ)፦ ይህን የሐሰት አካውንት ወይም ግሩፕ ስታዩ ወዲያውኑ "Report" በማድረግ እንዲዘጋ አድርጉ። ይህንን የማስጠንቀቂያ መልዕክትም ለሌሎች እህትና ወንድሞች በማጋራት (Share በማድረግ) የአጭበርባሪዎችን ሴራ እንድታከሽፉ በአላህ ስም እንጠይቃለን። ​💎 የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ​«مَنْ رَأَى مِنْكُمْ مُنْكَرًا فَلْيُغَيِّرْهُ بِيَدِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِلِسَانِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِقَلْبِهِ، وَذَلِكَ أَضْعَفُ الإِيمَانِ» (رواه مسلم) ​"ከእናንተ መካከል መጥፎ ነገርን (ወንጀልን) ያየ ሰው በእጁ ይለውጠው(ይከልክለው)፤ ካልቻለ በምላሱ (በንግግሩ/በጽሁፉ)፤ ካልቻለ በልቡ (ይጥላው)፤ ይህም ከኢማን ሁሉ በጣም ደካማው ነው።" (ሙስሊም ዘግበውታል) ​የባህር ዳር አባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጅድ ግዢና ግንባታ አስተባባሪ ኮሚቴ
781
13
የምቀኝነትና የድግምት መብዛት ምክንያቶች ——— ታላቁ ዓሊምና ፈቂህ የሆኑት ሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል'ዑሰይሚን (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- “በዚህ በመጨረሻው ዘመን ውስጥ በሰዎች ላይ ድግምትና ምቀኞች… መሰል ችግሮች የበዙበት ምክንያት ① አላህን ከማውሳት በመዘናጋታቸው ነው። ② አሸናፊና የላቀ በሆነው አላህ ላይ ያላቸው መመካት በመዳከሙ ነው። ③ በሸሪዓ የመጡትን የመከላከያ አዝካሮች መጠቀማቸው አናሳ በመሆኑ ነው። አለያማ እኛ እናውቃለን በሸሪዓ የመጡ የመከላከያ አዝካሮች የእጁጅና መእጁጅ ከተገደቡበት ግድብ በላይ ከልካይ መጠበቂያ እንደሆነ እናውቃለን። የሚያስቆጨው ነገር ብዙ ሰዎች ስለነዚህ አውራዶች አያውቁም፣ ያወቀው በብዛት ይዘናጋል፣ አለያም አዝካሮችን ሲያነብ በችለተኛ (ልቡ ሌላ ቦታ ሆኖ ነው)። ይህ ሁሉም ጉድለት ነው። ሰዎች በሸሪዓ የመጡ መጠበቂያ አዝካሮችን በአግባቡ ቢጠቀሙ ከብዙ ሸሮች ሠላም ይሆኑ ነበር። አላህን ዓፊያና ሠላምን እንጠይቀዋለን!!።”  [ተፍሲር ጁዝእ ዐመ ገፅ 358] ✍🏻ትርጉም:- ኢብን ሽፋ #Join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f
3
14
የምቀኝነትና የድግምት መብዛት ምክንያቶች ——— ታላቁ ዓሊምና ፈቂህ የሆኑት ሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል'ዑሰይሚን (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- “በዚህ በመጨረሻው ዘመን ውስጥ በሰዎች ላይ ድግምትና ምቀኞች… መሰል ችግሮች የበዙበት ምክንያት ① አላህን ከማውሳት በመዘናጋታቸው ነው። ② አሸናፊና የላቀ በሆነው አላህ ላይ ያላቸው መመካት በመዳከሙ ነው። ③ በሸሪዓ የመጡትን የመከላከያ አዝካሮች መጠቀማቸው አናሳ በመሆኑ ነው። አለያማ እኛ እናውቃለን በሸሪዓ የመጡ የመከላከያ አዝካሮች የእጁጅና መእጁጅ ከተገደቡበት ግድብ በላይ ከልካይ መጠበቂያ እንደሆነ እናውቃለን። የሚያስቆጨው ነገር ብዙ ሰዎች ስለነዚህ አውራዶች አያውቁም፣ ያወቀው በብዛት ይዘናጋል፣ አለያም አዝካሮችን ሲያነብ በችለተኛ (ልቡ ሌላ ቦታ ሆኖ ነው)። ይህ ሁሉም ጉድለት ነው። ሰዎች በሸሪዓ የመጡ መጠበቂያ አዝካሮችን በአግባቡ ቢጠቀሙ ከብዙ ሸሮች ሠላም ይሆኑ ነበር። አላህን ዓፊያና ሠላምን እንጠይቀዋለን!!።”  [ተፍሲር ጁዝእ ዐመ ገፅ 358] ✍🏻ትርጉም:- ኢብን ሽፋ #Join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f
496
15
አስደሳች ዜና👇 👉 ለእውቀት ፈላጊዎች በሙሉ 🔎 እነሆ በስልጤ ዞን በስልጢ ወረዳ በመነሀራ ከተማ ሸይኽ ዘይኑ የሚሰጥ አዲስ ደርስ ሊጀምር መሆኑን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው። የሚቀሩ ኪታቦች+1
አስደሳች ዜና👇 👉 ለእውቀት ፈላጊዎች በሙሉ 🔎 እነሆ በስልጤ ዞን በስልጢ ወረዳ በመነሀራ ከተማ ሸይኽ ዘይኑ የሚሰጥ አዲስ ደርስ ሊጀምር መሆኑን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው። የሚቀሩ ኪታቦች 1, አዱሩስ አልሙሒመህ ሊዓመቲል ኡመህ የሸይኽ ኢብን ባዝ 2, አሱል አስሰላሳ የሸይኽ ሙሀመድ ኢብን አብዱል ወሃብ 3, ኪታቡ አትተውሂድ የሸይኽ ፈውዛን 4, ፊርቀቱ አንናጅያ የሙሀመድ ኢብን ጀሚል ዘይኑ 5, ሸርህ አቂደቱል ዋስጥያ የሸይኽ ፈውዛን 6, ኡምደቱ አልአህካም የሸይኽ አብዱል غንይ 7, ኢርሻድ የሸይኽ ፈውዛን 8, ፈትሁል መጂድ 9, ሸርሁ አስሱነህ የሸይኽ ፈውዛን 👉 ሌሎች ደርሶችም ይኖራሉ 🗓 ደርስ የሚጀምርበት ቀን 👉 ዙልሂጃ 29/1447 👉 ሰኔ 8/2018 📍አድራሻ፦ ከወራቤ 12km ወደ ቡታጅራ በሚወስደው አልከሶን እንዳለፋችሁ  ወይም ከቡታጅራ 33km ወደ ወራቤ በሚወስደው  ቅበት ከተማን እንዳለፋችሁ ከጦራ መስመር ምትመጡ እሎስን እንዳለፋችሁ በምትገኘዋ ከተማ (መናሀሪያ) ነው። 🌐 ተጨማሪ ጥቆማዎችን ለማግኘት እንዲሁም የተለያዩ መረጃዎችን ለመለዋወጥ የቴሌግራም ግሩፓችን join በማለት ይቀላቀሉ 👇👇👇 https://t.me/+FsV1zmJcpMZjMjFk ለበለጠ መረጃ :- 1, ሙከሚል  +251921420111 2, ከይሬ          +251920973908 3, ሙባረክ   +251939455342 ♨️ ማሳሰቢያ :- 1, ቀሪኣ ከበቂ በላይ ነው እና በሁሉም አቅጣጫዎች ተጓዳኝ ዒባዳዎችን የምንፈጽምባቸው መስጂዶች አሉ 2, የደርስ ቋንቋ በአማርኛ ነው። ♻️ ሁሉም ይህ መልዕክት የደረሳቹ ሰለፍዮች እንዲሁም የቻናል እና የግሩፕ ባለቤቶች  ላልሰሙት በማሰማት እና ላልደረሳቸው በማዳረስ ወደኸይር እንድታመላክቱ መልዕክታችን ነው።
518
16
بسم الله الرحمن الرحيم 🔊ኸድር (አለይሂ ሰላም) ሞተዋል❗️ ✏️ ቁርኣንና ሀዲስ ያለው ምርጥ ህዝብ እንዴት ተረትና ቅዠት ይከተላል ⁉️ ✏️ ሱፊያ = የሳሊሆች ጠላት ✏️ ሳሊሆችን የሚወድ አሏህን ብቻ ያምልክ ❗️ 🎤 አቡ ሀመዊያ https://t.me/joinchat/AAAAAEP0OfkzzNtGHLxVeQ
627
17
✅ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ↪️ የፊታችን እሁድ 30/09/2018 የወንድማችንን አቡበክር ሙሀመድ የጋብቻ ፕሮገራም ምክንያት በማድርግ አጓጊ እና ወሳኝ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተናል። 🪑 ተጋባዥ እን
✅ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ↪️ የፊታችን እሁድ 30/09/2018  የወንድማችንን አቡበክር ሙሀመድ የጋብቻ ፕሮገራም ምክንያት በማድርግ አጓጊ እና ወሳኝ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተናል። 🪑 ተጋባዥ እንግዶቻችን        👇👇👇 🎙 ኡስታዝ ኑር አዲስ ✅ أهمية الزواج 🎙 ኡስታዝ ዶክተር ሸምሱ ✅ التوحيد لشرك 🎙 ኡስታዝ ሙሐመድ ሸምሴ ✅حقوق الوالدين. 🎙 ኡስታዝ ኸድር ✅ الصلاة 🎙 ኡስታዝ አቡ ሙዓዝ ✅ المنهج الصحيحة 👉 አድራሻ ፦ ቅበት ከተማ አስተዳደር በቢላል መስጂድ
1 167
18
✅ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ↪️ የፊታችን እሁድ 30/09/2018 የወንድማችንን አቡበክር ሙሀመድ የጋብቻ ፕሮገራም ምክንያት በማድርግ አጓጊ እና ወሳኝ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተናል። 🪑 ተጋባዥ እን
✅ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ↪️ የፊታችን እሁድ 30/09/2018  የወንድማችንን አቡበክር ሙሀመድ የጋብቻ ፕሮገራም ምክንያት በማድርግ አጓጊ እና ወሳኝ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተናል። 🪑 ተጋባዥ እንግዶቻችን        👇👇👇 🎙 ኡስታዝ ኑር አዲስ ✅ أهمية الزواج 🎙 ኡስታዝ ዶክተር ሸምሱ ✅ التوحيد لشرك 🎙 ኡስታዝ ሙሐመድ ሸምሴ ✅حقوق الوالدين. 🎙 ኡስታዝ ኸድር ✅ الصلاة 🎙 ኡስታዝ አቡ ሙዓዝ ✅ المنهج الصحيحة 👉 አድራሻ ፦ ቅበት ከተማ አስተዳደር በቢላል መስጂድ
1
19
🔷 የዓለም ጥፋት በመሃይምነት ነው !     የዚህች ምድር ውበት ሰላምና ብልፅግና በዲን እውቀት ሲሆን ጥፋትና ውድቀቱ በጅህልና መሆኑን ታላቁ ሊቅ ኢብኑል ቀይም እንዲህ በማለት ያስረዳናል  : – يقول ابن القيم – رحمه الله – " ولم يوجب الله سبحانه على الأمة إلا بما فيه حفظ دينها ودنياها وصلاحها في معاشها ومعادها ، وبإهمالها ذلك تضيع مصالحها وتفسد أمورها،  فما خراب العالم إلا بالجهل،  وما عمارته إلا بالعلم ، وإذا ظهر العلم في بلد أو محلة قل الشر في أهلها، وإذا خفي العلم هناك ظهر الشر والفساد ، ومن لم يعرف هذا فهو ممن لم يجعل الله له نورا، قال : الإمام أحمد – رحمه الله – " ولو لا العلم كان الناس كالبهائم " وقال :  " الناس أحوج إلى العلم منهم إلى الطعام والشراب ، لأن الطعام والشراب يحتاج إليه في اليوم مرتين أو ثلاثة، والعلم يحتاج إليه في كل وقت "           إعلام الموقعين  ( 2/238 ) " አላህ በኡማው ላይ ዲኑንም ዱንያውንም መኖረያውንም መመለሻውንም  የሚጠብቅለትን ገር እንጂ ግድ አላደረገበትም ። ይህንን ችላ በማለቱ ጥቅሙን አጥቷል ጉዳዩም ይበላሻል ።  የዓለም ጥፋት በመሃይምነት እንጂ በሌላ አይደለም ። ማማሩም በዒልም እንጂ በሌላ አይደለም ። ዒልም በአንድ ሀገር ወይም ቦታ ከተስፋፋ በህብረተሰቡ ውስጥ ተንኮል ይቀንሳል ። እዛ ቦታ ዒልም ከተደበቀ ክፋትና ጥፋት ይንሰራፋል ። ይህን የማያውቅ አላህ ብርሃን ያላደረገለት ሰው ነው ። ኢማሙ አሕመድ እንዲህ ብለዋል : – " እውቀት ባይኖር ኖሮ ሰው እንደ እንሰሳ ነበር "  በሌላ ቦታም እንዲህ ብለዋል : – " ሰዎች እውቀት ከምግብና መጠጥ በላይ ያስፈልጋቸዋል ። ምክንያቱም እነዚህ በቀን አንድ ወይም ሁለት ጊዜ ያስፈልጋሉ እውቀት ግን ሁሌም ያስፈልጋል ። " አላህ በእውቀት ብርሃን ቀልባቸውን ካበራላቸው ባሮቹ ያድርገን ። http://t.me/bahruteka
594
20
🚫ከቁርኣኒዮች እንጠንቀቅ!🚫 🎙 በዶክተር ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁላህ) ⏲ [Clip: 3:29 Minutes] @semirEnglish
553