uz
Feedback
Ethio-Universities Salafi Community(EUSaCo)

Ethio-Universities Salafi Community(EUSaCo)

Kanalga Telegram’da o‘tish

የዚህ Community ዓላማ በመላው ሀገሪቱ የሚገኝ ሰለፊይ የዩንቨርስቲ፣ኮሌጅ እና ሌሎች የትምህርት ተቋማት ኮሚኒቲን በአንድ አስተሳስሮ ትክክለኛውን እስላማዊ አስተምህሮ ለዑማው ማድረስ ነው። ኑ ሀቅን ከባለቤቶቹ እንማር! ገንቢ አስተያየትና ጥቆማዎትን @EUSaCofeedbackBot ያድርሱን። #ኢዩሰኮ #EUSaCo

Ko'proq ko'rsatish
3 450
Obunachilar
-524 soatlar
+127 kunlar
+6430 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Taglar buluti
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Kirish va chiqish esdaliklari
---
---
---
---
---
---
Obunachilarni jalb qilish
Iyul '26
Iyul '26
+69
1 kanalda
Iyun '26
+117
0 kanalda
Get PRO
May '26
+113
0 kanalda
Get PRO
Aprel '26
+124
0 kanalda
Get PRO
Mart '26
+109
2 kanalda
Get PRO
Fevral '26
+197
11 kanalda
Get PRO
Yanvar '26
+59
1 kanalda
Get PRO
Dekabr '25
+116
13 kanalda
Get PRO
Noyabr '25
+65
1 kanalda
Get PRO
Oktabr '25
+170
9 kanalda
Get PRO
Sentabr '25
+34
2 kanalda
Get PRO
Avgust '25
+75
8 kanalda
Get PRO
Iyul '25
+61
14 kanalda
Get PRO
Iyun '25
+47
3 kanalda
Get PRO
May '25
+73
6 kanalda
Get PRO
Aprel '25
+318
35 kanalda
Get PRO
Mart '25
+77
5 kanalda
Get PRO
Fevral '25
+121
21 kanalda
Get PRO
Yanvar '25
+474
28 kanalda
Get PRO
Dekabr '24
+181
4 kanalda
Get PRO
Noyabr '24
+265
15 kanalda
Get PRO
Oktabr '24
+242
10 kanalda
Get PRO
Sentabr '24
+258
16 kanalda
Get PRO
Avgust '24
+318
13 kanalda
Get PRO
Iyul '24
+1 446
9 kanalda
Sana
Obunachilarni jalb qilish
Esdaliklar
Kanallar
20 Iyul+1
19 Iyul+2
18 Iyul+6
17 Iyul+5
16 Iyul+2
15 Iyul+5
14 Iyul+2
13 Iyul+5
12 Iyul+5
11 Iyul+2
10 Iyul+3
09 Iyul+4
08 Iyul+5
07 Iyul+4
06 Iyul+2
05 Iyul+1
04 Iyul+6
03 Iyul+1
02 Iyul+5
01 Iyul+3
Kanal postlari
ከሀገር ወደ ሀገር እየተሳደደ የሞተው የእውቀት ብርሃን! ~ የኢማም አል-ቡኻሪ የመጨረሻ ቀናት ይህ ታላቅ ሰው በሕይወታቸው ማገባደጃ ላይ በወቅቱ የነበሩ የነይሳብር የቡኻራና የሰማርቀንድ ገዢዎች ያደረሱባቸው እንግልትና ስደት እጅግ ልብ ይሰብራል። 🚫​ለምን ተሰደዱ? ​የስደትና የመከራቸው መነሻ ዋና ዋና ምክንያቶች የሚከተሉት ነበሩ፦ ¹ኛ ​ለዕውቀት ያላቸው ክብር፦ ገዢዎች ልጆቻቸውን በቤተ-መንግሥት እንዲያስተምሩ ሲጠይቋቸው ኢማሙ እንዲህ በማለት ፈቃደኛ አልሆኑም ነበር፦ العلم يؤتى ولا يذهب به للأبواب "ዕውቀት (አል-ኢልም) ወደሱ ይመጣል እንጂ ወደበሮች አይመጣም" ይህ መልስ ለእነርሱ አንገት መድፋት አለመፈለጋቸው በገዢዎች ዘንድ ጥላቻን ፈጠረ። ²ኛ ​የሕዝብ ፍቅር ፦ የኢማሙ ስም ሲገንና ሕዝቡ ሲወድዳቸው በሥልጣን ላይ የነበሩት ሰዎች በስልጣናቸው ላይ የሥነ-ልቦና ስጋት ስለተሰማቸው ቅናት ተጫናቸው። 🛤​የመጨረሻው ጉዞ ​ኢማም አል-ቡኻሪ በ62 ዓመታቸው ከነይሳቡር እንዲወጡ ታዘዙ ወደ ትውልድ ከተማቸው ቡኻራ ሲመለሱ ሕዝቡ በታላቅ ደስታና አክብሮት ተቀበላቸው ነገር ግን የነይሳቡር ገዢ በቡኻራ ገዢ ላይ ተጽዕኖ በመፍጠር ኢማሙን ከከተማዋ እንዲያስወጡ አደረጉ። ​ወታደሮች ኢማሙ በእንግዳነት ወዳረፉበት ቤት በድንገት በመምጣት "አሁን ያለ ምንም ማመንታት ከተማዋን ለቀህ ውጣ!" አሏቸው ኢማሙ ኪታቦቻቸውን እንኳ በሥርዓት ለመሰብሰብ ጊዜ አላገኙም ከከተማዋ ወጥተው በዳርቻዋ ድንኳን ተክለው ለሦስት ቀናት ኪታቦቻቸውን ሲያስተካከሉ ቆዩ ። 🛣​የሰማርቀንድ መድረሻና የመጨረሻ እስትንፋስ ​ከዚያም ወደ ሰማርቀንድ አቅጣጫ ተጓዙ ነገር ግን የሰማርቀንድ ገዢም በሰላም አላሳለፋቸውም በዚያ አቅራቢያ በምትገኝ "ኸርተንክ" በምትባል መንደር ዘመዶቻቸው ዘንድ ተጠልለው ሳለ የሰማርቀንድ ገዢዎች "ከዚህም ክልል ለቀህ ውጣ" የሚል ትእዛዝ ላኩባቸው ። ​ወቅቱ የኢድ አል-ፊጥር በዓል ዋዜማ ነበር ኢማሙ የዘመዶቻቸውን ደኅንነት በመስጋት ምንም እንኳ ሕመምና ድካም ቢሰማቸውም ወዲያውኑ ለመውጣት ወሰኑ ረዳታቸው ኢብራሂም ቢን መዐቀል ኪታቦቻቸውን በግመል ላይ ጫነላቸው ​ኢማሙ ከአልጋቸው ተነስተው በረዳታቸው ተደግፈው ወደ ግመሉ ለመራመድ ጥረት አደረጉ ሃያ እርምጃ ያህል እንደተራመዱ እጅግ አድክሟቸው ስለነበር "ትንሽ ልረፍ" ብለው በመንገድ ዳር ተቀመጡ ዓይናቸውን ዘጉ አረፉ ​ረዳታቸው ኢብራሒም ኢማሙን ለመቀስቀስ ሲሞክር ነፍሳቸው ወደ አሏህ ሄዳ ነበር ! 📌​ከታሪኩ ..... ​የኢማም አል-ቡኻሪ ሕይወት በሻዋል ወር በቀን 01 በ256 ሂጅራ ነው የሞቱት እንደ ንጉሥ በቤተ-መንግሥት ሳይሆን በአገራቸው መብት ተነፍገውና ተሰደው በመንገድ ዳር ነበር ​ዛሬ ግን ያኔ ቡኻሪን ያስወጡት የነይሳብር የቡኻራና የሰማርቀንድ ገዢዎች ስማቸው ከታሪክ መዝገብ ተሰርዟል የኢማም አል-ቡኻሪ ስም ግን በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሙስሊሞች አንደበት በየቀኑ ይነሳል። ​አላህ የኢማም አል-ቡኻሪን ሥራ ይቀበላቸው በጀነትም ከነቢዩ (ﷺ) ጎን ያኑራቸው። ​ join #telegram ቻናል https://t.me/abuabdurahmen

2
አሁን እየሰራ ነው! ሙሓደራ ቀጥታ ስርጭት👌 💺 ከሸይኽ ዐ/ሀሚድ አንጋፋ ተማሪዎች መካከል የሆነው ኡስታዝ ሰይፈዲን ቢን ሳኒ ከወላይታ «ሀፊዘሁላሁ ተዓላ» ይከታተሉ👇👇 https://t.me/EUSaCochannel?livestream ከ«አል’ወሰጢያ» መድረሳ
50
3
ሙሓደራ ቀጥታ ስርጭት👌 💺 ከሸይኽ ዐ/ሀሚድ አንጋፋ ተማሪዎች መካከል የሆነው ኡስታዝ ሰይፈዲን ቢን ሳኒ ከወላይታ «ሀፊዘሁላሁ ተዓላ» ይከታተሉ👇👇 ከ«አል’ወሰጢያ» መድረሳ
93
4
አስደሳች ዜና ለመላው አዲስ አበባ ስልጤ ሰፈር ሙስሊም ነዋሪዎች! 🎁 በመድረሳችን «አል’ወሰጢያ» እጅግ አጓጊ እና ደማቅ ፕሮግራም ከክቡር እንግዳ ጋር ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል። ↪️ ተጋባዥ እንግዳች
አስደሳች ዜና ለመላው አዲስ አበባ ስልጤ ሰፈር ሙስሊም ነዋሪዎች! 🎁 በመድረሳችን «አል’ወሰጢያ» እጅግ አጓጊ እና ደማቅ ፕሮግራም ከክቡር እንግዳ ጋር ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል። ↪️ ተጋባዥ እንግዳችን፦ 💺 ከሸይኽ ዐ/ሀሚድ አንጋፋ ተማሪዎች መካከል የሆነው ኡስታዝ ሰይፈዲን ቢን ሳኒ ከወላይታ «ሀፊዘሁላሁ ተዓላ» ⌚️ ፕሮግሯሙ ለዛሬ ሐሙስ ማታ ሐምሌ 9/ 2018 አ እ ማታ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ ድረስ ነው።  «ስለዚህ ለራሳችን ዝግጁ ሆነን ለሌላውም ይህንን ሰበር ዜና በፍጥነት እንድታደርሱ አደራ እንላለን።» 🕌 አድራሻችን አዲስ አበባ በተለምዶ ስልጤ ሰፈር ከሸምሱ ሬስቶራንት በኩል ባለው ቂያስ 25 ሜትር ገባ ብለን እንገኛለን። «ክብሯን እና ክቡራት የሰለፍያ አስተምሮ ቻናል እና ግሩፕ ባልተቤቶች በሙሉ ይህንን መልእክት እንድታሰራጩ ለሌ እንወዳለን!» https://t.me/AbraribnAwal https://t.me/AbraribnAwal
279
5
👉  ከጭንቅህ መውጣት ካልቻልክ አላህን መፍራትህን ፈትሽ ! ‏قال شيخ الاسلام ابن تيمية – رحمه الله –: " إن اللَّه ضمن للمتقين أن يجعل لهم مخرجاً ممّا يضيق على الناس ، وأن يرزقهم من حيث لايحتسبون ، فإذا لم يحصل ذلك دل على أن في التّقوى خَلَلاً ، فليستغفر اللَّه وليتب إليه ".               الفتاوى ٨/ ٥٢٦     ➡️   ከሸይኹል ኢስላም አስገራሚ ንግግሮች ውስጥ የሚከተለው ይገኝበታል : – " አላህ እሱን ለሚፈሩ ሰዎች በሶዎች ላይ ከሚጠብ ነገር መውጫ ሊያደርግላቸው ካላሰቡትም ቦታ ሊረዝቃቸው ዋስትና ሰጥቷል ።    ይህ ነገር ካልተገኘ አላህን በመፍራት ላይ ክፍተት መኖሩን ያመለክታል ። አላህን ምህረት ጠይቆ ወደርሱ ይመለስ "። http://t.me/bahruteka
425
6
በዲን ያልታነጸ ሺህ ግዜ ቢማር ያው ጃሂል ነው‼️ 🎙አሸይኽ ዐብዱልሀሚድ አል-ለተሚይ (ሀፊዘሁላህ) @aaussj
428
7
♦️| አዲስ ሙሓደራ ከ"ملتقى" ቁ.023 ● ርእስ፦ ሸይኽ ዐብዱል-ሐሚድ በሚያውቋቸውና በማያውቋቸው ሰዎች መሃከል⁉️ 🎙ኡስታዝ ዐብዱል-ቃዲር አዳማ -ሐፊዞሁ'ሏህ- 🕌 በሰለፊዮች መገናኛ ግሩፕ የተደረገ ሙሓደራ! 🗓 ሐምሌ 3 - 2018 || የመገናኛው ግሩፕ፦ t.me/Multeqa_Ahlissuneh t.me/Multeqa_Ahlissuneh
504
8
🔷ሰው የሚወደሰው ሐቅ ስለያዘ ብቻና ብቻ ነው ሐፊዝ ብን አብዱል በር - ረሂመሁሏህ - እንዲህ አለ :- "የአሏህ መልእክተኛ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - ባልደረቦች በእውነት ካልሆነ በቀር ማንንም አያወድሱም ፤ በሀቅ ካልሆነ በቀር ማንንም አያሞግሱም ፤ ለዚህ ዓለም ጊዜያዊ ጥቅም ፍላጎት፣ በወገንተኝነት (አድሎአዊነት) ወይም በፍርሃት (ተቀያ) ምክንያት አይደለም (ሰውን የሚያወድሱት)።" الإستذكار (١٢٤/٢٦) https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة
527
9
🔖 ልዩ የደዕዋ ፕሮግራም! — እነሆ ዛሬ ጁሙዓ ሐምሌ 3 - 2018 «በሰለፊዮች መገናኛ» ግሩፕ እንደ ወትሮው የደዕዋ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል!። 💺ተጋባዥ እንግዶቻችን፦ 🎙ኡስታዝ ዐብዱል-ቃዲር አዳ
🔖 ልዩ የደዕዋ ፕሮግራም! — እነሆ ዛሬ ጁሙዓ ሐምሌ 3 - 2018 «በሰለፊዮች መገናኛ» ግሩፕ እንደ ወትሮው የደዕዋ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል!። 💺ተጋባዥ እንግዶቻችን፦ 🎙ኡስታዝ ዐብዱል-ቃዲር አዳማ -ሐፊዞሁ'ሏህ- ● ርእስ፦ ሸይኽ ዐብዱል-ሐሚድ በሚያውቋቸውና በማያውቋቸው ሰዎች መሃከል⁉️ ● ርእስ፦ የሐዲሥ አልቀበል ባዮች አደጋ! 🎙ኡስታዝ አብራር አወል ከአዲስአበባ -ሐፊዞሁ'ሏህ- || ግጥም ይኖረናል -ኢንሻአ'ሏህ- ⏰ ሰዓት ፦ ከምሽቱ በኢትዮ 3:00 በሱዑዲያ 9:00 በኢማራት 10:00 አይለፋችሁ!። #የመገናኛውን_ግሩፕ_ተቀላቀሉ👇 https://t.me/Multeqa_Ahlissuneh https://t.me/Multeqa_Ahlissuneh
561
10
ለአሏህ እጅ ማጽደቅና አህባሽ ~ join #telegram ቻናል https://t.me/abuabdurahmen
383
11
እስካሁን በሰለፊይ መሻይኽ እና አስታዞች ተቀርተው በ"Sakinah App" የተዘጋጁ አፕሊኬሽኖችን እናጋራችሁ!!  እናንተም መቅራት የምትፈልጉትን ኪታብ ስም በመጫን አፕሊኬሽኑን ማግኘት ትችላላችሁ!! ↪️  የኪታቡ ስም፦  ሸርሁ ኡሱሊ አሲታህ       🎙በኡስታዝ ሰዕድ ዐብዱለጢፍ                  አላህ ይጠብቀዉ ↪️ የኪታቡ ስም፦ ኪታቡ ተውሂድ ሊል ኢማም መሀመድ ኢብን ዐብዲልወሃብ       🎙በኡስታዝ ሰዕድ ዐብዱለጢፍ                  አላህ ይጠብቀዉ ↪️ የኪታቡ ስም፦ ኹላሶቱ ኑሪል የቂን      🎙 ኡስታዝ አቡ አነስ ሙሐመድ አሚን አላህ ይጠብቀው ↪️የኪታቡ ስም፦ ሚንሓጅ አል ፊርቀቱ ናጂያህ      🎙ኡስታዝ ኪርማኒ አቡ ሀሰን አላህ ይጠብቀው ↪️ የኪታቡ ስም፦ አስባቡ ሰባት ዓላ መንሀጅ ሰለፊ ሷሊህ      🎙ኡስታዝ ሰዕድ ዐብዱለጢፍ                  አላህ ይጠብቀዉ ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፍይ ይሁኑ! 📢 መሰል  ቂርአቶችን በአፕ ለማሰራት የሚከተለውን አድራሻ ይጠቀሙ👇👇👇 @aaussjfeedback_bot @sakinah_app
720
12
قيـل لابـن الـمـبارك : ما خير مـا أعطـي الـرجـل ؟ قـال : غريزة عقــل قيـل : فإن لم يكـن .. قـال : أدب حــــــــــــــسـن . قيـل : فإن لم يكـن .. قال : أخ صالح يسـتشيــره . قيـل : فإن لم يكـن .. قال : صمـت طـويـــــــــــل قيـل : فإن لم يكـن .. قـال: مـوت عـاجــــــــــل. (روضة العقلاء 34)
838
13
♦️| አዲስ ሙሓደራ ከ"ملتقى" ቁ.019 ● ርእስ፦ ግዜን በአግባቡ መጠቀም! 🎙ኡስታዝ ሰይፉዲን ሣኒ ከወላይታ -ሐፊዞሁ'ሏህ- 🕌 በሰለፊዮች መገናኛ ግሩፕ የተደረገ አሳሳቢ ሙሓደራ! 🗓 ሰኔ 5 - 2018 || የመገናኛው ግሩፕ፦ t.me/Multeqa_Ahlissuneh t.me/Multeqa_Ahlissuneh
855
14
🎉Congratulations🎉 ⚜️ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ጊዜያቶች በኋላ ለዚህ ያበቃን አሏህ ላቅ ያለ ምስጋና ይገባዋል!! አልሃምዱሊላህ! ✨ በኢትዮጵያ የምትገኙ ተመራቂ ሰለፊዮች በሙሉ እንኳን ደ
🎉Congratulations🎉 ⚜️ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ጊዜያቶች በኋላ ለዚህ ያበቃን አሏህ ላቅ ያለ ምስጋና ይገባዋል!! አልሃምዱሊላህ! ✨ በኢትዮጵያ የምትገኙ ተመራቂ ሰለፊዮች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ። 📖 የተማርነዉን እዉቀት አሏህ በሚወደዉ መልኩ ኡማዉን ለማገልገል ልናዉለዉ ይገባል!! 👉በት/ት ላይ ያላችሁ ደግሞ በዲን እና በዱንያ የተሻለ ነገር ይዞ ለማዉጣት ጥረት እንድታደርጉ እንዲሁም እኛ ያጣናቸዉን ነገሮች አሳክታችሁ እንድትወጡ አደራ ለማለት እወዳለሁ። 🎉ألف مبروك التخرج🎉 🎓Congratulations🎓 🎆እንኳን ደስ አላችሁ🎆 ✍️አቡ አብዱረህማን (አብዱሰላም) ከባ/ዳር https://t.me/BDU_Selefiyah_Students https://t.me/BDU_Selefiyah_Students
891
15
💡ፆመኛ ሲያፈጥር የሚለው ዱዓ!💡   <======================> 🥛ذَهَبَ الظَّمَأُ وَابْتَلَّتِ الْعُرُوْقُ وَثَبَتَ اْلأَجْرُ إِنْ شَاءَ اللهُ. 🥛ዘሀበ ዞመኡ ወበተለቲል ዑሩቁ ወሰበተል አጅሩ ኢንሻ አላህ                 💈ትርጉም፦ «ጥም ተወገደ የደም ሥር ተብላላ የአላህ ፈቃድ ከሆነ ምንዳውም ፀደቀ ማለት ነው»። ➩ሌላም፦ ➴➴➴➴➴ 🥛اَللَّهُمَّ إِنِّيْ أَسْأَلُكَ بِرَحْمَتِكَ الَّتِيْ وَسِعَتْ كُلَّ شَيْءٍ أَنْ تَغْفِرَ لِيْ. 🥛አላሁመ ኢኒ አሰአሉከ ቢረህመቲከ ለቲ ወሲዓት ኩለ ሸይኢን አን ተግፊረሊ     💈ትርጉም፦ አላህ ሆይ! ምህረትን ትለግሰኝ ዘንድ ሁሉንም ነገር ባዳረሰችው እዝነትህ እማፀንሐለሁ። 📱⇘⇘⇘⇘⇘ https://t.me/Durusu_Abu_Anes https://t.me/Durusu_Abu_Anes https://t.me/Durusu_Abu_Anes
727
16
🔶#የኻሊድ ክብሮምን ዝንባሌ ግልፅ ማድረግ፣ ከጥመቱ ማስጠንቀቅና ቁርኣኒይ ከሚባሉት ጠማማ ተጣሪ (ሰባኪዎች) መሆኑን ማጋለጥ 🔶በአዲስ አበባ አል- ወሰጢየህ መርከዝ እና መድረሳ የተደረገ ሙሐደራ። 🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ) 📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ 👇👇👇 🌐 https://t.me/shakirsultan
567
17
እንዲሁ በጣም የሚያስገርመው ፡  አንዳንድ ሴቶች እና ወንዶች ከአጅነብይ (ከባእድ) ጋር በማውራት የሚስተዋለው ቸልተኛነት ነው፡፡ አስገዳጅ ነገር ሳይገጥም አጅነብይ የሆነችውን ሴት ያወራታል ፣  ያሳስቃታል እርሷም ታሳስቀዋለች በንግግሯ ይደሰታል፡፡ አንዳንድ ሴቶችም አስገዳጅ ነገር  ሳይገጥም አጅነብይ ከሆነ ወንድ ጋር ያወራሉ፡፡ በለሰለሰ ቃላት ፣  ደስ የሚል ቃል ወደርሱ ትወረውራለች፡፡  በልቡ በሽታ ያለበት ሰው ይከጅላል፡፡ በተለይም በማህበራዊ ድረ ገጽ፡፡  በትክክለኛ ሐዲስ የአላህ መልክተኛ - ዓለይሂሶለቱ ወሰላም - እንዲህ ብለዋል :- إن المرأة عورة ، فإذا خرجت استشرفها الشيطان “ሴት አውረት (አካሏ ሁሉ መታየት የማይገባት) ነች ፣ (በአደባባይ) ከወጣች ሸይጧን ይቀርባታል” ሙስሊም በሶሂህ ሐዲስ  የሚከተለውን ዘግቧል ፡ إن المرأة تقبل في صورة شيطان ، وتدبر في صورة شيطان “ሴት ስትመጣ በሸይጧን ምስል ትመጣለች፡፡ ስትሄድም በሸይጧን ምስል ትሄዳለች፡፡” ሁሉም ሙስሊም አላህን ሊፈራ ግዴታ አለበት፡፡ ባለትዳሮች ሚስጢራቸውን በአደባባይ ማሰራጨት ሳይሆን ችግራቸውን ከቤተሰብ ጋር ሆነው በትእግስት እና በጥበብ ተወያይተው መፍታት አለባቸው፡፡  ሙስሊም ወንድሜ ሆይ!   በአንተ እና በሚስትህ መካከል አለመግባባት ከተከሰተ ከማንም ጋር ግንኙነት አታድርግ ቤተሰቦችህ እንዲገኙ በማድረግ  በጥበብ ፣  በትግስት ፣  በዱዓ መፍታት ትችላለህ፡፡ ለአንተ ቅርብ እና አዛኞች የአንተ እና የሚስትህ ቤተሰቦች በመሆናቸው በመካከላችሁ ተገኝተ  ጉዳያችሁን እንዲፈቱ  አድርግ፡፡ ይህ ካልተሳካ ወደሸሪዓ ዳኞች ጉዳዩን አቅርብ፡፡  ይህ ነው አላህ የሚወድልህ ፣ የሚስትህን ሚስጢር አትበትን ፣ በቁርዓን እና በሐዲስ ጉዳይህን ፍታ - በዱንያና በአኼራ ስኬታማ  ትሆናለህና፡፡ ሙስሊም እህቴ ሆይ!  ከባልሽ ጋር አለመግባባት ከተከሰተ  አላህን ፍሪ ፣ ታገሽ  ፣ ባልሽን በመልካም ታዘዥ፡፡  አላህ ከፍ ያደርግሻል፡፡  ከአንች ዘንድ ያለውን ይወድልሻል፡፡ የሂዎትሽ ሁኔታ ካልተስተካከለ ቤተሰቦችሽን አማክሪ እንጅ ከዚያም ከዚህም ጋር አትገናኝ - ከአላህ ቁጣ ላይ ትወድቂያለሽና፡፡ በባልና በሚስት ጉዳይ ፈትዋ የሚሰጡ ሰዎች አላህን ይፍሩ፡፡ በሁለቱ መካከል በተፈጠረው ጉዳይ የተሰጣቸውን የሸሪዓ ድንበር ሊያውቁ ይገባል፡፡ ፈትዋ የሚሰጡ ሰዎች በባልና ሚስት እርቅ ጉዳይ ከቤተሰቦች የበለጡ አይደሉም፡፡ አላህ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡ ባለትዳሮችን ባልና ሚስትን በማስማማት አላህ በቁርዓኑ ያወሳው ቤተሰብን ነው፡፡  ባለትዳሮችን መምከር ፣  ሸሪዓዊ ህጉን ግልጽ ማድረግ የሚከለክል ነገር የለውም፡፡  በፍች ጉዳይ ግን የአንዱን ወገን ብቻ መስማትና ጣልቃ መግባት ተገቢ አይደለም፡፡  የሰዎችን ቤት ሚስጢራቸውንም መከታትልና መፈተሽ አይፈቀድም፡፡ ይህ የቆሻሻ ልቦች በሽታ ነው፡፡ ሙስሊሞች ከእንዲህ አይነቱ መጽዳት ግዴታ አለባቸው፡፡  ነብዩ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - እንዲህ ብለዋል:- يا معشر من آمن بلسانه ولم يدخل الإيمان قلبه ، لا تغتابون المسلمين ، ولا تتبعوا عوراتهم ، فإنه من تتبع عورة أخيه المسلم ، تتبع الله عورته ، ومن تتبع الله عورته ، يفضحه ولو في جوف بيته  “በምላሳችሁ ያመናችሁ ፣ እምነት በልባችሁ ያልገባ ሰዎች ሆይ! ሙስሊሞችን አትሙ ፣ ነውራቸውንም አትከታተሉ ፣ የሙስሊም ወንድሙን ነውር የሚከታተል የእርሱን ነውር አላህ ይከታተለዋል፡፡ የእርሱን ነውር አላህ የተከታተለው በቤቱ ውስጥ እንኳ ቢሆን ያጋልጠዋል፡፡” ሸይኽ ብን ኡሰይሚን - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ጥያቄ ተጠየቁ ፡ “የቤቶቻቸውን  ጉዳይ ፣ ስለትዳራቸው ሒዎት ፣ ከባሎቻቸው ጋር ያለውን ጉዳይ ለቅርብ ዘመዶቻቸው ፣  ለጓደኞቻቸው ማውራትና ማሰራጨት በአንዳንድ ሴቶች ላይ ይበዛል፡፡  ከእነዚህ ወሬዎች ከፊሉ የቤት ሚስጢር ናቸው፡፡  ባል እንዲወራ አይፈልግም፡፡ ባል ይህን የቤት ሚስጢር  አንድም ሰው እንዲያውቅ አይፈልግም፡፡ ሚስጢርን ከቤት ውጭ  በማሰራጨት ወይም ለአንዳንድ የቤት ሰዎች በማውራት ላይ የተሰማሩ  ሴቶች ፍርድ ምንድን ነው? መልስ ፡  የቤትን ወሬ ፣ የትዳር ሂዎታቸውን ለቅርብ ዘመድ ፣ ለጓደኛ የሚያወሩ አንዳንድ ሴቶች ይህ ተግባራቸው ሐራም ነው፡፡ ማንኛዋም ሴት  የቤቷን ሚስጢር ወይም ከባሏ ጋር ያለውን ሁኔታ ለአንድም አካል ማውራት ወይም ማሰራጨት አይገባትም፡፡  አላህ የሚከተለውን ተናግሯል ፡ - فَالصَّالِحَاتُ قَانِتَاتٌ حَافِظَاتٌ لِّلْغَيْبِ بِمَا حَفِظَ اللَّهُ ۚ                    “መልካሞቹ ሴቶች (ለባሎቻቸው) ታዛዦች ፣ አላህ ባስጠበቀው (እንዲጠበቅ ባዘዘው) ነገር ሩቅን (ባሎቻቸው በሌሉበት አፍረተ ገላቸውን ፣ ንብረታቸውን ...) ጠባቂዎች  ናቸው፡፡”  (ኒሳእ : 35) ነብዩ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - የሚከተለውን ተናግረዋል :- شر الناس منزلة عند الله يوم القيامة الرجل يفضي إلى المرآة وتفضي إليه ثم ينشر سرها" “የትንሳኤ ቀን ከአላህ ዘንድ መጥፎ ሰው ብሎ ማለት ባል ለሚስቱ ሚስጢር ይነግራታል ፣ ሚስት ለባሏ ሚስጢር ትነግረዋለች ከዚያም ሚስጢሯን የሚያሰራጭ ነው፡፡” انتهى من فتاوى إسلامية (211212\3)    በዶክተር ሸይኽ ሁሰይን ብን ሙሐመድ  https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة
896
18
🔷ከአንዳንድ የሐበሻ ሰዎች የሚስተዋለው አስቀያሚ ባህሪ የባልና የሚስትን ሚስጢር ማሰራጨት ክቡር በሆነችው የመካ ከተማ የክፍለ ዘመንን ሩብ የሚቃረብ ቆይታ አድርጊያለሁ - አሏህ ልቅና ይስጣት፡፡ ከፍ ያለ ምስጋናም ለአላህ ይገባው፡፡  የሱዑዲ ፣ የየመን ፣ የኩዌት ፣ የአልጀሪያ ፣ የህንድ ፣ የቱኒዚያ ፣ የፓኪስታን ፣ የሱዳንና የሌላም አገር ዜግነት ካላቸው ምርጥ ሰለፍይ ወንድሞች ጋር ተዋውቂያለሁ፡፡ ልክ በእኛ ቤት እንደሚከሰተው በእነርሱም ቤት በባልና ሚስት መካከል ግጭት ፣ አለመግባባት ይከሰታል፡፡  ከእነርሱ መካከል ሚስቱን የፈታ ፣  ከሚስቱ ጋር የተለያየም አለ፡፡ እንዲህ አይነቱን ድርጊት ቤት ይቁጠረው ፤ በተለይም ከሱዑዲ ዜጎች ዘንድ አዲስ ነገር  አይደለም፡፡  በጣም የሚገርመኝ ባል ከሚስቱ ጋር ያለውን አለመግባባትም ይሁን የቤት ሚስጢራቸውን ይፋ ሲያደርጉ አለማወቄ ነው፡፡ ግጭት ከተፈጠረም ባል ሚስቱን ይመክራል ፣ አላህ ባዘዘው መሰረት  ስርዓት በማስያዝ ላይ ይሰማራል፡፡ አላህ በተከበረው ቁርዓን እንዲህ ብሏል :- وَاللَّاتِي تَخَافُونَ نُشُوزَهُنَّ فَعِظُوهُنَّ وَاهْجُرُوهُنَّ فِي الْمَضَاجِعِ وَاضْرِبُوهُنَّ ۖ                     “እነዚያንም ማመጸቸውን የምታውቁትን ገስጿቸው፡፡ (ግሰጻው ካላስተካከላቸው) ከምኝታዎችም ተለዩዋቸው፡፡ (ከመኝታ መለየታችሁ ካላስተካከላቸው)  ምቱዋቸውም (ጉዳት ሳታደርሱ)፡፡”  (ኒሳእ ፡  35)   ሚስት ተመክራ ወደትክክለኛው ጎዳና ፣ ወደአቅሏ መመለስ ካልቻለችና በአመጸኝነቷ ከቀጠለች  የሁለቱ ባልና ሚስት ቤተሰቦች ጣልቃ ይገባሉ፡፡ ቤተሰቦች ጉዳዩን ካልፈቱትና እርቅ ካልመጣ ጉዳያቸውን ወደሸሪዓ ፍርድ ቤት ይወስዱታል፡፡ በፍርድ ቤቱ ውስጥ የምክክር ኮሚቴ የሚባል አለ፡፡ ኮሚቴው እንዲስማሙ የምክር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ይህ ካልሆነ  ጉዳያቸው ወደፍርድ ቤት ቀርቦ ከብዙ ጥናት ፣ ክርክር ፣ ምክር በኋላ ፍርድ ቤቱ አላህ በሚከተለው አንቀጽ በተናገረው መሰረት   የመጨረሻ ሸሪዓዊ ብይን ይሰጣል፡፡ وَإِن يَتَفَرَّقَا يُغْنِ اللَّهُ كُلًّا مِّن سَعَتِهِ ۚ وَكَانَ اللَّهُ وَاسِعًا حَكِيمًا “ቢለያዩም (ቢፋቱ) ፣ አላህ ሁሉንም በችሮታው ያከብራቸዋል፡፡ አላህም ችሮታው ሰፊ ፣ ጥበበኛ ነው፡፡” (ኒሳእ ፡ 130) ይህ ነው በሱዑዲ የተመለከትሁት የአሊሞችና የሙፍቲዎች ሚና በሁለት ባለትዳሮች መካከል አለመግባባት ከተከሰተ መምከር እንጅ ጦላቅ እንዲወድቅ  ብይን መስጠት የለባቸውም - ምክንያቱም ይህ ባልና ሚስቶች በአካል ተገኝተው እነርሱን ማድመጥ ፣ ከዚያም ብይን መስጠት ይፈልጋልና፡፡ በዚህ ምክንያት የሱኡዲ ኡለሞች ለምሳሌ ፡ - ኢብን ባዝ ፣ ኢብን ኡሰይሚን ፣ ፈውዛን  እና ሌሎችም ኡለሞች እንዲሁም የሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ በባል እና ሚስት አለመግባባት ፣ ጦላቅን በመጠል  ዙሪያ  ጥያቄ ሲቀርብላቸው ፣ ሸሪዓዊ የሆነውን ህግጋት ማብራራት ፣  የምክር አገልግሎት መስጠት ፣ ጉዳያቸውን ወደሸሪዓ ፍርድ ቤት ዳኞች እንዲያቀርቡ መምከር  እንጅ  በፍጹም ፈትዋ አይሰጡም፡፡ በጣም የሚገርመው አንዳንድ የሐበሻ ሰዎች … አንድ ባል ከሚሰቱ ጋር ከተጋጨ ሚስጢሯን ላለፊ አግዳሚው ሁሉ በአደባባይ ያሰራጫል፡፡ ሚስቱም እንደዚሁ የባሏን ሚስጢር ለጎረቤት ፣ ለጓደኛ ፣ በየመድረሳው ታሰራጫለች፡፡ በዚህ ምክንያት በመካከላቸው ቂምና ጥላቻ ይወለዳል፡፡  ሁለቱም አንዱ አንዱን ለመበቀል ይፈልጋሉ፡፡ ሁለቱም ሐቁ ከእኔ ጋር ነው ብለው ይሞግታሉ፡፡  ችግራቸውን ለመፍታት  ከቁርዓንና ከሐዲስ ህግ ጋር በተቃረኑ ጊዜ  አላህ ከማይወደው ተግባር ለይ ይወድቃሉ፡፡ ሱናን መቃረን ለልቦና ጭንቀት ፣ ለነፍስ አለመረጋጋት  ምክንያት ይሆናል፡፡   አንዲት ሴት ከባሏ ጋር የተፈጠረውን አለመግባባት በስልክ ነግራኝ ነበር፡፡ የባሏን ችግር ለብዙ ወንዶችና ሴቶች እንዳወራች አመነችልኝ - ሱብሃን አላህ -  ይህች ሴት - ተቆጣጣሪዋ አላህ ሲሆን - ከደጋግ ሰለፍይ ሴቶች መካከል ናት ብዬ እገምታለሁ፡፡    “አንች ሀራም ከሆነው አሜት ወድቀሻል ፤  የአላህና የረሱልን ህግ ጥሰሻል ፣  የባልና ሚስት ችግር መፍትሄው በባል እጅ ነው ፤ እርሱ ካልፈታው  ሁሴን ወይም ሌላው ሳይሆን አላህ እንደነገረን ከሁለቱም ወገን ቅርብ ዘመዶች ጣልቃ ይገባሉ፡፡  وَإِنْ خِفْتُمْ شِقَاقَ بَيْنِهِمَا فَابْعَثُوا حَكَمًا مِّنْ أَهْلِهِ وَحَكَمًا مِّنْ أَهْلِهَا إِن يُرِيدَا إِصْلَاحًا يُوَفِّقِ اللَّهُ بَيْنَهُمَا ۗ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلِيمًا خَبِيرًا                             (እናንተ አማኞች!) የመካከላቸውንም (የባልና የሚስትን) ጭቅጭቅ ብታውቁ ፤ ከቤተሰቦቹ ሽማግሌን ፣ ከቤተሰቦቿም ሽማግሌን ላኩ፡፡ (ሽማግሌዎቹ) ማስታረቅን ቢሹ አላህ በመካከላቸው (ባልና ሚስትን) ያስማማል - አላህ ግልጽን ዐዋቂ ፣ ውስጥንም ዐዋቂ ነውና፡፡  (ኒሳእ ፡ 35) ችግሩ ከአቅም በላይ ከሆነ - ከተገኘ ወደሸሪአ ፍርድ ቤት መመለስ ነው” አልኳት፡፡ በጣም የደነገጥኩት ደግሞ በሁለቱ ግጭት መካከል አጅነብይ ወንድ ጣልቃ ገብቶ ባሏ ለእርሷ ያወራውን ለአጅነብዩ  እንደምትናገር ፣ እርሷ ለባሏ ያወራችውን ባል ለዚህ አጅነብይ እንደሚናገር በነገረችኝ ጊዜ ነው -  ሱብሃን አላህ - መፍትሄ ሰጭ የሆነውን ሱና በመቃረናቸው ምክንያት በባልና ሚስጥ መካከል ጥላቻው ቂሙ ጨመረ፡፡  እኔም ገሰጽኋት ፣ በአላህ አስፈራራኋት ፣ የባሏን ሚስጢር ከማሰራጨት መቆጠብ እንዳለባት ፣ ባሏን በመልካም መታዘዝ እንዳለባት - ከዚህ አልፎ ነገሩ በጣም የሚያጨናንቃት ከሆነ  ከቤተሰቦቿ ጋር እንድትገናኝ መከርኋት፡፡  ይህ ቆሻሻ የሆነ ባህል በሐበሻ ምድር በሙስሊሞች መካከል ከየት መጦ እንደገባ አላውቅም፡፡ ከእምነት ቁርጠኝነት ማነስና በመቀላቀል የመጣ ችግር ነው ብየ እገምታለሁ፡፡ በጣም የሚያስገርመው ነገር ፡  አንዳንድ ፈተና ላይ የወደቁ በሰዎች ጉዳይ  ጣልቃ የሚገቡ  ፊት ለፊት የምናያቸው ሰዎች አሉ፡፡ በማይመለከታቸው ጉዳይ ለሚስት ስለባሏ  የግብረስጋ ግንኙነትና ጥንካሬ  ይጠይቃሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ሚስት በባል ላይ እንድታምጽ ፣  ቀልቧ በእርሱ ላይ  እንዲሻክር ያደርጋሉ፡፡በቀላሉ ያበላሹዋታል ፤  ባሏን እንድትፈታ ያነሳሳሉ፡፡ ነብዩ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - እንዲህ ብለዋል  ፡ ليس منا من خبب امرأة على زوجها “ሚስት በባል ላይ (እንድታምጽ) የሚያነሳሳ (የሚያበላሽ) ከእኛ አይደለም” ይህ ፈተና ላይ የወደቀ ጠያቂ የሸይጧን ስራ አስፈጻሚ ነው፡፡ በማንኛውም ሁኔታ በባለትዳሮች መካከል ነፍሱን ጣልቃ ሊያስገባ  አይገባውም፡፡  ከእርሱ መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ አንዲት ሴት - ለማንም አካል ሳይሆን - ባሏ የግብረ ስጋ ግንኙነት የማድረግ አቅሙ እንደሌለው ለሸሪዓ ዳኛ ብቻ መናገር ትችላለች፡፡  አንድም አካል ስለዚህ ጉዳይ ሊጠይቃት አየገባም፡፡ ይህ ከስነ ምግባር እጥረትና ከእምነት ቁርጠኝነት ድክመት ነው፡፡ 
667
19
በወንድማችን አቡበከር የሰርግ ፕሮግራም ላይ የተደረገ አንገብጋቢ ሙሓደራ! 🎤 በኡስታዝ ኑራዲስ(አቡል-በያን) ሀፊዘሁላህ ይደመጥ👌
902
20
​بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ ​🚨 አስቸኳይ የጥንቃቄና የማስጠንቀቂያ መልዕክት ከባህር ዳር አባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጅድ! 🚨 ​ውድና የተከበራችሁ የዲናችን እህትና ወንድሞች፤ በአሁኑ ሰዓት የባህር ዳር አባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጅድን የቴሌግራም ግሩፑን ስም፣ዲስክሪፕሽን (Description)  ጽሁፎችን እና ከዚህ በፊት የተለቀቁ ፖስቶችን እንደ ግብአት ተጠቅሞ፣ የተለየ የሐሰት ግሩፕ እና አካውንት ከፍቶ ሰዎችን እያታለለ ብር የሚሰበስብ አጭበርባሪ ግለሰብ እንዳለ ደርሰንበታል። ​ይህ አካል ከቢላል መስጅድ አስተዳደርም ሆነ ከኮሚቴው ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው እና የግል ጥቅሙን የሚያሳድድ አጭበርባሪ ነው። ስለሆነም መላው ሙስሊም ማህበረሰብ የሚከተሉትን ነጥቦች ተገንዝቦ ራሱንና ዲኑን ከማጭበርበር እንዲጠብቅ በጥብቅ እናሳስባለን፡ ​1️⃣ ትክክለኛ እና ሕጋዊ የባንክ አካውንቶቻችን፡ ለባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 11 (አባይ ማዶ) በኢትዮጵያ አህሉሱና እስላማዊ ማህበር ስር ላለው ለቢላል መስጅድ ግዢ እና ግንባታ ማሰባሰቢያ የሚውሉ እውቅና ያላቸው አካውንቶች እነዚህ ብቻ ናቸው፦ ​📌 ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000-742-45-45-45 📌 አቢሲኒያ ባንክ፦ 245566778 📌 ሂጅራ ባንክ፦ 1000-927-373-0001 👥 የአካውንት ስም፦ አሊ ሙሀመድ ፣ ጀማል ሙሀመድ እና አህመድ እስማን ​⚠️ እጅግ በጣም አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ ከነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት ሶስት የባንክ አካውንቶች እና በጋራ ከተከፈቱት ከእነ አሊ ሙሀመድ፣ ጀማል ሙሀመድ እና አህመድ እስማን ስሞች ውጭ ምንም አይነት ሌላ አካውንት የሌለን መሆኑን በድጋሚ እናረጋግጣለን! ​2️⃣ ፍፁም ሊታወቁና ሊጠነቀቁ የሚገቡ የሐሰት መረጃዎች፡ ❌ አብደላ አወል አባቦር (Abidela Awol Ababor) የሚባል ሰው በኮሚቴው ውስጥ የለም! ልጁ ወደ ግሩፑ ሲገቡ ራሱን በዚህ ግሩፕ ስም እያስተዋወቀ እና የራሱን አካውንት በመለጠፍ እያጭበረበረ ይገኛል። 👌👌👌በቢላል መስጅድ ስም በአብደላ አወል አባቦር ስም የተከፈተ ምንም አይነት አካውንት የለም! ​❌ የአዋሽ ባንክ አካውንት ፍፁም የለንም! ይህ አጭበርባሪ አካል በአዋሽ ባንክ አካውንት ከፍቶ ገንዘብ እየሰበሰበ ይገኛል። እኛ ግን በአዋሽ ባንክ ምንም አይነት አካውንት የሌለን መሆኑን ህዝቡ በደንብ እንዲያውቅና እርግጠኛ እንዲሆን እንፈልጋለን። ​✅ የሜምበር (አባላት) ቁጥር ልዩነት፦ ትክክለኛው የቢላል መስጅድ ግሩፓችን በአሁኑ ሰዓት 16,045 (አስራ ስድስት ሺህ አርባ አምስት) ሜምበር አለው (ይህ ቁጥር አባላት ሲገቡና ሲወጡ መጠኑ ከፍና ዝቅ ሊል ይችላል)። የዚህ አጭበርባሪ ግሩፕ ግን 3 ሺህ አካባቢ ብቻ አባላት ያሉት በመሆኑ በዚህ የቁጥር ልዩነት በቀላሉ መለየት ትችላላችሁ። ​3️⃣ ለተጨማሪ መረጃ እነዚህን የኮሚቴ ስልክ ቁጥሮች ይጠቀሙ፡ ማንኛውንም መረጃ ለማጣራትና ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ በሚከተሉት የእውነተኛው ኮሚቴ ስልክ ቁጥሮች ላይ በነፃነት መደወል ይችላሉ፦ 📞 0918720696 - አሊ ሙሀመድ 📞 0918702221 - ጀማል ሙሀመድ(Dr) 📞 0920257036 - ሰኢድ መህሙድ (telegram owner) ​4️⃣ የበኩላችሁን አድርጉ (ሪፖርት አድርጉ)፦ ይህን የሐሰት አካውንት ወይም ግሩፕ ስታዩ ወዲያውኑ "Report" በማድረግ እንዲዘጋ አድርጉ። ይህንን የማስጠንቀቂያ መልዕክትም ለሌሎች እህትና ወንድሞች በማጋራት (Share በማድረግ) የአጭበርባሪዎችን ሴራ እንድታከሽፉ በአላህ ስም እንጠይቃለን። ​💎 የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ​«مَنْ رَأَى مِنْكُمْ مُنْكَرًا فَلْيُغَيِّرْهُ بِيَدِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِلِسَانِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِقَلْبِهِ، وَذَلِكَ أَضْعَفُ الإِيمَانِ» (رواه مسلم) ​"ከእናንተ መካከል መጥፎ ነገርን (ወንጀልን) ያየ ሰው በእጁ ይለውጠው(ይከልክለው)፤ ካልቻለ በምላሱ (በንግግሩ/በጽሁፉ)፤ ካልቻለ በልቡ (ይጥላው)፤ ይህም ከኢማን ሁሉ በጣም ደካማው ነው።" (ሙስሊም ዘግበውታል) ​የባህር ዳር አባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጅድ ግዢና ግንባታ አስተባባሪ ኮሚቴ
781