የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
Відкрити в Telegram
#ሪስቶሬሽን ማለት ማፍረስ ማለት አይደለም ፤ ይልቁን የፈረሰውን መገንባት፣ መልሶ ማቆም ማለት ነው። MEKETE DEBAY TADESSE
Показати більше845
Підписники
+224 години
+67 днів
+2930 день
Архів дописів
መልካም እሁድ
ሮሜ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤
⁶ ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን፤ የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና።
ጸሎት
የእግዚአብሔርን ፍቃድ ማወቅ እና ከእግዚአብሔር ጋር ማውራት እንጂ የሰውን ፍቃድ ማስፈፀሚያ አይደለም ። እግዚአብሔር ሁሉ በፍቃዱ ይምራችሁ።🧎🧎🧎🧎🧎♀🧎♂
መዝሙር 96
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ለእግዚአብሔር አዲስ ምስጋናን አመስግኑ፤ ምድር ሁሉ፥ እግዚአብሔርን አመስግኑ።
² እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ባርኩ፥ ዕለት ዕለትም ማዳኑን አውሩ።
³ ክብሩን ለአሕዛብ ተኣምራቱንም ለወገኖች ሁሉ ንገሩ፤
⁴ እግዚአብሔር ታላቅ ምስጋናውም ብዙ ነውና፥ በአማልክትም ሁሉ ላይ የተፈራ ነውና።
⁵ የአሕዛብ አማልክት ሁሉ አጋንንት ናቸውና፤ እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ።
የእግዚአብሔር ጽድቅ
ጽድቅ:-Greek: δικαιοσύνη
Transliteration: dikaiosýnē
Pronunciation: dik-ah-yos-oo'-nay
Justification mean to justified before God
righteousness,meaning to right before God
የእግዚአብሔር ጽድቅ የሚለው ቃል ሁሉ ቃላት አሉት
¹የእግዚአብሔር ²ጽድቅ የሚገለጸው ‒የጽድቅ ምንጭ እግዚአብሔር መሆኑን ነው ።
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃል ኪዳነ ወልድ ክፍሌ
እንዳስቀመጡት ጽድቅ ማለት ’'በእግዚአብሔር ፉት ያለምንም ነውር መታየት ማለት ነው'' ።
የእግዚአብሔር ጽድቅ ማለት የእግዚአብሔር ፍጹም ቅድስና፣ ቅንነት፣ እና ከኃጢአት የነጻ ማንነት መገለጫ ነው። ይህንን ጽድቅ በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ማየት እንችላለን፦
ባህሪው: እግዚአብሔር በነገሩ ሁሉ ፍጹም፣ ጻድቅ እና እውነተኛ ፈራጅ ነው።
ስጦታው (የእምነት ጽድቅ): በሰው ልጆች ላይ የሚገኘውን ኃጢአት በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት በማስወገድ፣ ለእኛ እንደ ስጦታ የሚሰጠን የጽድቅ አቋም ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው፤ ሰው በራሱ መልካም ሥራ ወይም የሕግን ትእዛዝ በመፈጸም መጽደቅ አይችልም፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ጽድቅ የሚገኘው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ ነው። ስለዚህም ኃጢአተኛው በክርስቶስ ሥራ በጸጋ ጻድቅ ሆኖ ይታወጃል።
እንደ ፊልጵስዩስ 3፥8-9
“አዎን፥ በእውነት ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጥ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ጌታዬ እውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቈጥራለሁ፤ ስለ እርሱ ሁሉን ተጐዳሁ፥ ክርስቶስንም አገኝ ዘንድ፥ በክርስቶስም በማመን ያለው ጽድቅ ማለት በእምነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ያለው ጽድቅ እንጂ ከሕግ ለእኔ ያለው ጽድቅ ሳይሆንልኝ፥ በእርሱ እገኝ ዘንድ ሁሉን እንደ ጕድፍ እቈጥራለሁ፤”
— ፊልጵስዩስ 3፥8-9
ሰው የሚጸድቀው በክርስቶስ በማመን እንጂ በህግ ስራ አይደለም ማለት ነው ።ይሄ ጽድቅ በክርስቶስ አምኖ በመቀበል ብቻ እንጂ ህግ በመጠበቅ አይገኝም ።
ፈል 3:8-9
በእምነት ይሆን ጽድቅ ።
እምነት :-Greek: πίστις
Transliteration: pístis
Pronunciation: pis'-tis
በተመሳሳይ በኢየሱስ ማመን እርሱ መኖሩን በአእምሮ ከመቀበል ያለፈ ነው፡፡ እንዲያድነን እምነታችንን በእርሱ ላይ መጣል ነው፡፡ ለእርሱ ራሳችንን አሳልፈን መስጠት ነው፡፡ እግዚአብሔር በልጁ በኩል እዳችንን በመክፈል ይቅርታን እንደሰጠን እናምናለን፤ የከፈለንንም ክፍያ እንቀበላለን ማለታችን ነው፡፡ ክርስቶስንም ለመከተል ፍቃደኝነታችንን እየገለፅን ነው፡፡
የእግዚአብሔር ጽድቅ እና የሰው ዘር
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰውን በራሱ አምሳል ለክብር እና ለዓላማ ፈጠረው። ሰው የእግዚአብሔር ወዳጅ እና ያለ ኃጢአት ስለነበረ፣ እግዚአብሔር እየመጣ ሁልጊዜ ያነጋግረው ነበር። ሰው ፈቃድ ያለው ፍጥረት ስለሆነ ፈቃዱን ተጠቅሞ ለእግዚአብሔር እንዲገዛ፣ እግዚአብሔርን እንዲያከብርና እንዲያመልክ አግዚአብሔር ስውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፤ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ ነገር ግን መልካሙንና ክፉውን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና ዘፍ 2:16-17፡፡ በሰይጣን ተታለው ያንን ፍሬ በበሉ ጊዜ በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ላይ አመጹ። አዳም ትሞታለህ በተባለው መሰረት ወዲያው በስጋ አልሞተም ነገር ግን ከእግዚአብሔር በመንፈስ ተለየ (በመንፈስ ሞተ)፤ ሞት ማለት መለየት ነውና። የሕይወት ምንጭ ከሆነው ከእግዚአብሔር ተለየ (ሞተ)። ከኤደን ገነት ከመገኘቱ አባረራቸው እንዲሁም ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ሕብረት ተቋረጠ። በዚህ ምንክያት ኃጢአት በአንድ ሰው ምክንያት ወደ ዓለም ገባ። ሞት የኃጢአት ውጤት ነውና በኃጢአት ም ምክንያት ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ። ሮሜ 3:23 እንዲሁም ሁሉ ኃጢአትን ሰርተዋል የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሏቸዋል ይላል። በአንዱ አዳም አለመታዘዝ ሁሉ ሐጢያተኛ ሆነ ከእግዚአብሔር ክብር ጎደለ። ከዛን ግዜ ጀምሮ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ታላቅ ቁጣ ሥር ነው ያለው። የሰው ልጅ የእግዚአብሔር ጠላት ሆነ። በኃጢአተኝነታቸውና በዓመፃቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቍጣ ከሰማይ ይገለጣልና (ሮሜ 1:18)፡፡
✍✍አገልጋይ መከተ ደባይ
Repost from የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
Repost from የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
መነጠቅ መቼ ነው የሚሆነው፣ ከታላቁ መከራ ከመነጠቅ ጋር በተያያዘ
ክፍል ሁለት ....2
በዛሬዋ በቤተ ክርስቲያን፤ የመነጠቅ ጊዜ ጉዳይ ከታላቁ መከራ ጋር በተያያዘ አንደኛው እጅጉን አወዛጋቢው ጉዳይ ነው። ሦስቱ ዋነኛ አመለካከቶች አሉ፡፡ እነርሱም :- 1) ቅድመ-ታላቁ መከራ (ከታላቁ መከራ በፊት የሚሆን መነጠቅ [pre-tribulation])፣ 2) ማዕከላዊ ታላቁ መከራ (በታላቁ መከራ መሀከል ወይም በዚያ አካባቢ የሚሆን ታላቁ መከራ [mid- tribulation])፣ እና 3) ድኅረ-ታላቁ መከራ (በታላቁ መከራ መጨረሻ ላይ የሚሆን መነጠቅ [post- tribulation]) ናቸው። አራተኛው አመለካከት፣ ከቁጣ-በፊት በሚል ይታወቃል፣ ይህም ከማዕከላዊ ታላቁ መከራ አቋም መጠነኛ ማሻሻያ ያለው ነው። ከሁሉ አስቀድሞ ግን በመጀመሪያ፣ የመከራውን ዓላማ መገንዘብ ጠቃሚ ነው።
እንደ ዳንኤል 9፡27 ሱባዔ “ሰባት” (ሰባት ዓመት) አለ፣ ይህም ገና የሚመጣ ነው። የዳንኤል አጠቃላይ ትንቢት፣ የሰባ ሰባቶች (ዳንኤል 9፡20-27) የሚናገረው ስለ እስራኤል ሕዝብ ነው። እሱም፣ እግዚአብሔር አትኩሮቱን በተለይ በእስራኤል ላይ የሚያደርግበት ጊዜ ነው። የሰባት ሱባኤ መከራ የግድ መሆን ያለበት እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር በተለይ የሚያደርገው ነው። ይህም ማለት ቤተ ክርስቲያን አትኖርም ማለትን አያመለክትም፣ ቤተ ክርስቲያን በዚያን ሰዓት በምድር ላይ ለመኖሯ ጥያቄ ያስነሣል እንጂ።
ቀዳሚው የመነጠቅ ምንባብ በቅዱስ ቃሉ ውስጥ 1ነተሰሎንቄ 4፡13-18 ነው። እሱም የሚያስረግጠው በሕይወት ያሉት አማኞች ሁሉ፣ ከሞቱት አማኞች ጋር፣ ጌታ ኢየሱስን በአየር እንደሚቀበሉትና ለዘላለም ከእሱ ጋር እንደሚሆኑ ነው። መነጠቅ እግዚአብሔር የራሱን ሕዝብ ከምድር ላይ የሚወስድበት ነው። ከጥቂት ቁጥሮች በኋላ፣ በ1 ተሰሎንቄ 5፡9፣ ጳውሎስ ይላል፣ “እግዚአብሔር ለቁጣ አልመረጠንምና፣ ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ደኅንነትን ለመቀበል እንጂ።” የራዕይ መጽሐፍ በቀዳሚነት ስለ ታላቁ መከራ ጊዜና ሰዓት በቀዳሚነት የተናገረ፣ ትንቢታዊ መልእክት ነው፣ እግዚአብሔር ቁጣውን በምድር ላይ እንዴት እንደሚያፈስ፣ በታላቁ መከራ ጊዜ ይታያል። እሱም የማይጣጣም ይመስላል፣ እግዚአብሔር አማኞች ቁጣውን እንደማይቀበሉና ቀጥሎም በታላቁ መከራ ይሣቀዩ ዘንድ በምድር ላይ አይተዋቸውም። ሐቁ፣ እግዚአብሔር ክርስቲያኖችን ከቁጣ ለማዳን የሰጠው ተስፋ ባጭሩ የራሱን ሕዝብ ከምድር ላይ ለመውሰድ ቃል የገባው እነዚያን ሁለት ሁነቶች አያይዞ ለማስኬድ ይሆናል።
ሌለኛው የመነጠቅ ጊዜ ወሳኝ አንቀጽ ራዕይ 3፡10 ላይ ያለው ነው፣ ይሄውም ክርስቶስ አማኞችን “ከፈተና ሰዓት” ሊያድናቸው ቃል የገባበት ነው፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለው በሁለት ነገሮች ነው። አንድም፣ ክርስቶስ አማኞችን በፈተና መሐል ሊጠብቃቸው መቻሉን፣ ወይም አማኞችን ከፈተና መሐል ሊያወጣ መቻሉን ነው። ሆኖም፣ አማኞች ከምን እንደሚጠበቁ ተስፋ እንደተሰጠ መገንዘብ ጠቃሚ ነው። እሱ ፈተና ብቻ አይደለም፣ ግን የፈተና “ሰዓት” ነው። ክርስቶስ አማኞችን ሊጠብቅ ቃል ገብቷል፣ ፈተናውም ታላቁ መከራ ተብሎ የሚታወቀው ነው። የ1 ተሰሎንቄ 5፡9 ፍቺ፣ እና የራዕይ 3፡10 ትርጓሜ ሁሉ ግልጽ የሆነ ድጋፋቸውን የሚሰጡት ለቅድመ-ታላቁ መከራ አቋም ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በጥሬውና በቋሚነት ከተተረጎመ፣ ቅድመ-ታላቁ መከራ አቋም እጅግ የተሻለው መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው ትርጓሜ ነው።
👆👆👆👆👆👆👆
✍በአገልጋይ መከተ ደባይ
ክፍለ ሦስት ---3
ይቀጥላል ........
Repost from የዲጂታል ወንጌል ስርጭት።
ንጥቀት ምንድነው ?
ክፍል አንድ .....1
ንጥቀት የሚለውን ቃል በቃለ እግዚብሔር ውስጥ አናገኘውም፡፡ ነገር ግን የትምህርቱ መሠረት ሐሳብ በግልጽ አለ፡፡ ንጥቀት (Rapture) የሚለው ቃል ከLatin የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜውም ''መወሰድ፣ ማጓጓዝ፣ በኃይል/ በግድ መውሰድ'' ማለት ነው፡፡
👆👆👆👆👆👆
የቤተክረስቲያን ንጥቀት እግዚአብሔር በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ አምኖ ያንቀላፉትን (በሥጋ የሞቱትን) እና በሕይወት ያሉትን አማኞችን፤ በዓለም ላይ በጽድቅ ለመፍረድ በሚመጣበት ጊዜ ሊመጣ ካለው ከታላቁ መከራ አስቀድሞ በኃይሉ ''ነጥቆ'' የሚወስድበት ክስተት ነው፡፡ የንጥቀት ምንባብ ለመጀመሪያ ጊዜ የተነሳባቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች 1ኛ ተስ 4፡13-18 እና 1ኛ ቆሮ 15፡50-54 ናቸው፡፡ እግዚአብሔር በክርስቶስ አምነው ያንቀላፉትን ሁሉ ያነሳቸዋል፣ የከበረ ሰውነትንም ይሰጣቸዋል፣ ከምድርም ይወስዳቸዋል፤ በሕይወት ያሉትንም ከእነርሱ ጋር በተመሳሳይ ሰዓት አብሯቸው ሙት የሆነውን ስጋቸውን በመለወጥና አዲሱን የከበረ ሰውነት በመስጠት ይወስዳቸዋል፡፡ ''ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤ ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።'' (1ኛ ተሰ 4፡16-17)፡፡
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
ንጥቀት ቅጽበታዊ የሆነ የሰውነት ልውውጥን ያካትታል፤ ይህም ሰውነታችን ዳግም ኢ-ሙታዊ በመሆን ዘላለምን እንዲመጥን ነው፡፡ ''ወዳጆች ሆይ፥ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ዳሩ ግን ቢገለጥ እርሱ እንዳለ እናየዋለንና እርሱን እንድንመስል እናውቃለን'' (1ኛ ዮሐ 3፡2)፡፡ ንጥቀት ከክርስቶስ ዳግም ምጻት ይለያል፡፡ በንጥቀት ወቅት ጌታ ከእኛ ጋር ለመገናኘት በአየር በደመናት ይመጣል (1ኛ ተስ 4፡17)፡፡ ይህን ሚስጢር ዓለም (በወንጌል የማያምኑ) አታውቅም፡፡ ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ ዓለም ሁሉ ያየዋል፡፡ በመምጣቱም እግሮቹ በኢየሩሳሌም ትይዩ በምሥራቅ በኩል ባለው በደብረ ዘይት ላይ ይቆማሉ፤ በዚህም ምድር ትንቀጠቀጣለች፣ የእግዚአብሔርም ጠላቶች ይሸነፋሉ (ዘካ 14፡3-4)፡፡
የንጥቀት አስተምህሮ በብሉይ ኪዳን ውስጥ አንድም ቦታ አልተጠቀሰም፣ ለዚህም ነው ሐዋሪያው ጳውሎስ ንጥቀትን ''ሚስጢር'' ብሎ የጠራውና ዳሩ ግን አሁን ተገልጧል ነው ያለው፡፡ ''እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበተ ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።'' (1ኛ ቆሮ 15፡51-52)፡፡
የቤተክርስቲያን ንጥቀት ሁላችንም በጉጉት የሚንጠብቀውና ተስፋ የሚናደርገው የክብር ክስተት ነው፡፡ በዚያን ጊዜ ሁላችንም ከኃጢአት ነጻ እንሆናለን፡፡ ለዘላለም በእግዚአብሔር መገኘት (ሓልዎት) ውስጥ እንኖራለን፡፡ በዚህ አስተምህሮ ጉዳይ ብዙ ክርክር እንዳለ ግልጽ ነው፡፡ ምንም እንኳ ክርክሮች ብበዙም ይህ ለእግዚአብሔር ጉዳይ አይደለም፡፡ ይልቅ እግዚአብሔር በዚህ ቃል እርስ በርሳችን እንዲንጽናና ይሻል (1ኛ ተሰ 4፡18)፡፡
👆👆👆👆👆👆👆👆
✍ በ አገልጋይ መከተ ደባይ
ክፍለ ሁለት -----2
ይቀጥላል
የለሁም ክርስቶስ ሃለፊነት ወንጌልን መመስከር ነው ።
ሮሜ 10
⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
¹⁰ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
¹¹ መጽሐፍ፦ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
¹² በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
¹³ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
የለሁም ክርስቶስ ሃለፊነት ወንጌልን መመስከር ነው ።
ሮሜ 10
⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
¹⁰ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
¹¹ መጽሐፍ፦ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
¹² በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
¹³ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
በጎችና ፍየሎች
ጻድቃን በበግ ኃጥአን በፍየል ለምን ይመሰላሉ፡፡ ጻድቃን በበግ ኃጥአን በፍየል ለምን ተመሰሉ ቢባል የበጎች ተፈጥሮ ከጻድቃን ሥራ ጋር የፍየል ተፈጥሮ (ግብር) ከኃጥአን ጋራ ስለሚመሳሰል ነው፡፡ በጎች በደጋ እንጂ በቆላ አይኖሩም፡፡ ተስማሚያቸው ደጋ ነው ጻድቃን በመከራ ሥጋ እንጂ በተድላ ደስታ ለመኖር ሲሉ ኃይማኖታቸውን ክደው በምግባር ብልሹነት አይገኙም፡፡ ፍየሎች በቆላ እንጂ በደጋ አይኖሩም፤ ኃጥአንም በተድላ ደስታ ለመኖር ሲሉ ኃይማኖታቸውን በወርቅ በብር ይለውጣሉና፡፡
በጎች እረኛቸው ባሰማራቸው ሥፍራ ጸንተው ይኖራሉ፡፡ ጻድቃንም እረኛቸው ክርስቶስ ባሰማራቸው በአንዲት ኃይማኖት (እምነት) ጸንተው ይኖራሉ፡፡ ፍየሎች እረኛቸው ባሰማራቸው ቦታ ጸንተው እንደማይኖሩ ኃጥአንም እንዲሁ በኃይማኖት ጸንተው መኖር አይቻላቸውምና፡፡ በጎች ጥቂት ሳር ካገኙ ተፋቅረው አብረው ይበላሉ ጻድቃንም ያለቻቸውን ተካፍለው ይኖራሉና፡፡ ፍየሎች ግን ሣር ቅጠሉ ሞልቶ ለሁላቸው ሲበቃ ሳለ ይጣላሉ፡፡ ኃጥአንም ሀብት ንብረት ተትረፍርፎላቸው ለወገናቸው አያካፍሉም፡፡ ለገንዘብ ብለው እርስ በእርሳቸው ይጣላሉ ዘለው የሌላውን ሀብት ንብረት ለማግኘት ሲሉ የማይገባ ሥራ ይሠራሉና፡፡
የበጎች ላታቸው የተከደነ ሐፍረተ ሥጋቸው የተሸፈነ ነው፡፡ የጻድቃንም ኃጢአታቸው በሰው ዘንድ የተጋለጠ አይደለም፡፡ ኃጢአት ቢሰሩ ሌላ ሰው ሳይሰናከልባቸው ንስሐ ይገባሉ፡፡ የፍየሎች ላታቸው የተሰቀለ ሐፍረተ ሥጋቸው የተጋለጠ ነው፡፡ የኃጢአተኞችም ሥራ በሰው ዘንድ የተጋለጠ ለሚሰሩት እኩይ ሥራ የማያፍሩ በየአደባባዩ ኃጢአትን የሚፈጽሙ ናቸውና፡፡ በጎች አቀርቅረው እንጂ አሻቅበው አያዩም ጻድቃንም ሁልጊዜ ዕለተ ሞታቸውን በማሰብ ወደ አፈር እንደሚመለሱ እያሰቡ በትህትና ሕይወታቸውን ይመራሉ፡፡ ሀብት’ ንብረት’ ዕውቀት እያላቸው ራሳቸውን ዝቅ ያደርጋሉ፡፡ ፍየሎች አሻቅበው ነው የሚያዩት አንገታቸውን ያንጠራራሉ ኃጥአንም ደካማ ሆነው ሳሉ ብርቱ ነን ይላሉ ባገኙበት ሀብት ዕውቀት ይመካሉ ትዕቢተኞች ናቸው፡፡ ትሕትና በእነርሱ ዘንድ የበታችነት ምልክት ነው፡፡
ከበጎች ውስጥ አንዲቱ ተኩላ ቢነጥቃት ሁለተኛ ወደዚያ ቦታ ተመልሰው አይመጡም፡፡ ጻድቃንም እኩይ ሞት ከእነርሱ አንዱን ከወሰደ ነገም የእነርሱ ተራ እንደሆነ ተረድተው ከኃጢአት ሥራቸው በንስሐ ይመለሳሉ ወደ እግዚአብሔር ይቀርባሉ፡፡ ፍየሎች ግን ከመካከላቸው ነብር አንዲቱን ቢወስድ ለጊዜው ደንብረው ይሄዳሉ፡፡ ኋላ ግን ተመልሰው እዚያው ቦታ ይመጣሉ ኃጥአንም ከመካከላቸው አንዱ ሳያስቡት በሞት ቢወሰድ ለጊዜው ደንግጠው ከኃጥአት ሥራቸው ይታቀባሉ በኋላ ግን የሞተው ሰው ከህሊናቸው ሲጠፋና የዓለም ሁኔታ ሲማርካቸው ወደ ኃጢአት ግብራቸው ይመለሳሉና፡፡
የመጨረሻው ፍርድ።
ሁሉም እንደየሠራው የሚያገኝበት የመጨረሻው ቀን ፍርድ አለ፡፡ ይህም ከጌታችን ምጽአትና ያንቀላፉት ሁሉ ከተነሱ በኋላ ይከናወናል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹የሚጥለኝ ቃሌንም የማይቀበለው እርሱ የሚፈርድበት አለው፤ እኔ የተናገርሁት ቃል እርሱ በመጨረሻው ቀን ይፈርድበታል›› (ዮሐ 12፡48) በማለት ሰው በመጨረሻው ቀን የሰማው የእግዚአብሔር ቃል እንደሚፈርድበት ተናግሯል፡፡ እንዲሁም ‹‹እኔ እላችኋለሁ፥ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል›› (ማቴ 12፡36) ብሎ ዛሬ ለምንናገራቸው ከንቱ ነገሮች ሁሉ በዚያ በፍርድ ቀን መልስ የምንሰጥበት ይሆናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ ስለመጨረሻው ቀን ፍርድ ሲናገር ‹‹ሌላ መጽሐፍም ተከፈተ እርሱም የሕይወት መጽሐፍ ነው፤ ሙታንም በመጻሕፍት ተጽፎ እንደ ነበረ እንደ ሥራቸው መጠን ተከፈሉ›› (ራዕ 20፡11-15) በማለት ሁሉም እንደ ሥራው የሚከፈልበት ፍርድ መሆኑን መስክሯል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ሰለዚህ ቀን ‹‹መልካም ቢሆን ወይም ክፉ እንዳደረገ፥ እያንዳንዱ በሥጋው የተሠራውን በብድራት ይቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ በፍርድ ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናልና›› (2ኛ ቆሮ 5፡10) ብሏል፡፡ እንዲሁም ለአቴና ሰዎች ‹‹ቀን ቀጥሮአልና፥ በዚያም ቀን ባዘጋጀው ሰው እጅ በዓለሙ ላይ በጽድቅ ሊፈርድ አለው፤ ስለዚህም እርሱን ከሙታን በማስነሣቱ ሁሉን አረጋግጦአል›› (ሐዋ 17፡31) በማለት እውነትን መስክሮላቸዋል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንም ስለዚች ቀን ‹‹እግዚአብሔር ሥራን ሁሉ የተሰወረውንም ነገር ሁሉ፥ መልካምም ቢሆን ክፉም ቢሆን፥ ወደ ፍርድ ያመጣዋልና›› (መክ 12፡14) ብሏል፡፡ ገነትና ሲኦል ጊዜያዊ የነፍሳት መቆያ ናቸው፡፡
ዘላለማዊ ትንሣኤ
መድኃኔዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቀደመው ለአባታችን ለአዳም በገባው ቃልኪዳን መሠረት፤ በአይሁድ እጅ መከራ መስቀልን ከተቀበለ በኋላ ነፍሱን በራሱ ስልጣን አሳልፎ ሰጠ፡፡ ከዚያም በኋላ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ መስፍኑ ጲላጦስን አስፈቅደው ከመስቀል አውርደው ዮሴፍ ራሱ ባሰራው መቃብር በንጹህ በፍታt ገንዘው ቀበሩት፡፡ ሲሄዱም ጸሐፍት ፈሪሳውያንና መስፍኑ በመቃብሩ ላይ ማኅተማቸውንና ጠባቂዎችን አኖሩ (ማቴ 27÷57-66 ማር 15÷42 ሉቃ 23÷50 ዮሐ 19÷38-42) ፡፡ ጌታቸን በሦስተኛው ቀን እሁድ በእኩለ ሌሊት መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በታላቅ ኃይል ሞትንና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ፡፡ ይጠብቁ የነበሩ ጠባቂዎችም ደንግጠው ተበታተኑ በመቃብሩ ዙሪያ ቅዱሳን መላዕክት ታዩ (ማቴ 28÷1-15 ማር 16÷11-15 ሉቃ 24÷1-43 ዮሐ 20÷1-25 1ኛ ቆሮ 15-1 ሮሜ 6÷9-15)፡፡ ለሰው ልጆች ዘላለማዊ ትንሣኤ በኩር የሆነው የክርስቶስ ትንሣኤ ነው፡፡ በመጨረሻው ቀን ሁላችን የምንነሳው ትንሣኤ እንዲሁ ዳግመኛ ሞት የሌለበት ዘላለማዊ ትንሣኤ ነው፡፡
ፊተኛው ትንሣኤ:- በዚኛው ትንሣኤ የሚነሡት ጻድቃን የሚወርሱት መንግሥተ ሰማያትን ነው፡፡ ሲነሡም ብርሃን ለብሰው ብርሃን ተጎናጽፈው እንደ ፀሐይ እያበሩ ነው፡፡ (ራዕ 21÷1-5 ፤ 2ተኛ መቃ 13÷8-14)፡፡ ከዳግም ምጽዓት በኋላ የማይቆጠር እድሜ እንኖራለን ማለት ነው፡፡
ኋለኛው ትንሣኤ:- ይህን ትንሣኤ የሚነሡት ሰዎች በዚህች ምድር ሳሉ እግዚአብሔርን ሲበድሉ በክህደት በምንፍቅና የሚኖሩ የትንሣኤ ልቡና ያላገኙ እና ባጠቃላይ በወንጌል ያላመኑ ሰዎች የሚነሱት ትንሣኤ ነው፡፡ የኋለኛውን ትንሣኤ የሚነሱት ኃጥአን የግብር አባታቸውን ሰይጣንን መስለው ለዘላለም በማይጠፋበት በገሃነመ እሳት ውስጥ ይኖራሉ፡፡ (ማቴ 13÷42፣50፤ 22÷13፤025÷30)
የሙታን አነሳስ፡- “የሞትህ ተነሥ” የሚል አዋጅ በመላእክት አለቃ በቅዱስ መልአክ ይታወጃል፡፡ ጌታ ራሱ በትዕዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምጽ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና (1ና ተሰ 4÷16)፡፡ በምድር ላይ ስንኖር እንዳለው በሚበሰብስ ሥጋ ሳይሆን ዘላለማዊ በሆነው ሥጋ በክርስቶስ ያመንን ሁላችን እንነሳለን፡፡
መድኃኔዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቀደመው ለአባታችን ለአዳም በገባው ቃልኪዳን መሠረት፤ በአይሁድ እጅ መከራ መስቀልን ከተቀበለ በኋላ ነፍሱን በራሱ ስልጣን አሳልፎ ሰጠ፡፡ ከዚያም በኋላ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ መስፍኑ ጲላጦስን አስፈቅደው ከመስቀል አውርደው ዮሴፍ ራሱ ባሰራው መቃብር በንጹህ በፍታ ገንዘው ቀበሩት፡፡ ሲሄዱም ጸሐፍት ፈሪሳውያንና መስፍኑ በመቃብሩ ላይ ማኅተማቸውንና ጠባቂዎችን አኖሩ (ማቴ 27÷57-66 ማር 15÷42 ሉቃ 23÷50 ዮሐ 19÷38-42) ፡፡ ጌታቸን በሦስተኛው ቀን እሁድ በእኩለ ሌሊት መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በታላቅ ኃይል ሞትንና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ፡፡ ይጠብቁ የነበሩ ጠባቂዎችም ደንግጠው ተበታተኑ በመቃብሩ ዙሪያ ቅዱሳን መላዕክት ታዩ (ማቴ 28÷1-15 ማር 16÷11-15 ሉቃ 24÷1-43 ዮሐ 20÷1-25 1ኛ ቆሮ 15-1 ሮሜ 6÷9-15)፡፡ ለሰው ልጆች ዘላለማዊ ትንሣኤ በኩር የሆነው የክርስቶስ ትንሣኤ ነው፡፡ በመጨረሻው ቀን ሁላችን የምንነሳው ትንሣኤ እንዲሁ ዳግመኛ ሞት የሌለበት ዘላለማዊ ትንሣኤ ነው፡፡
ፊተኛው ትንሣኤ:- በዚኛው ትንሣኤ የሚነሡት ጻድቃን የሚወርሱት መንግሥተ ሰማያትን ነው፡፡ ሲነሡም ብርሃን ለብሰው ብርሃን ተጎናጽፈው እንደ ፀሐይ እያበሩ ነው፡፡ (ራዕ 21÷1-5 ፤ 2ተኛ መቃ 13÷8-14)፡፡ ከዳግም ምጽዓት በኋላ የማይቆጠር እድሜ እንኖራለን ማለት ነው፡፡
ኋለኛው ትንሣኤ:- ይህን ትንሣኤ የሚነሡት ሰዎች በዚህች ምድር ሳሉ እግዚአብሔርን ሲበድሉ በክህደት በምንፍቅና የሚኖሩ የትንሣኤ ልቡና ያላገኙ እና ባጠቃላይ በወንጌል ያላመኑ ሰዎች የሚነሱት ትንሣኤ ነው፡፡ የኋለኛውን ትንሣኤ የሚነሱት ኃጥአን የግብር አባታቸውን ሰይጣንን መስለው ለዘላለም በማይጠፋበት በገሃነመ እሳት ውስጥ ይኖራሉ፡፡ (ማቴ 13÷42፣50፤ 22÷13፤025÷30)
የሙታን አነሳስ፡- “የሞትህ ተነሥ” የሚል አዋጅ በመላእክት አለቃ በቅዱስ መልአክ ይታወጃል፡፡ ጌታ ራሱ በትዕዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምጽ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና (1ና ተሰ 4÷16)፡፡ በምድር ላይ ስንኖር እንዳለው በሚበሰብስ ሥጋ ሳይሆን ዘላለማዊ በሆነው ሥጋ በክርስቶስ ያመንን ሁላችን እንነሳለን፡፡
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
