uk
Feedback
ዳሩል ኢቅረእ • دار الإقرأ

ዳሩል ኢቅረእ • دار الإقرأ

Відкрити в Telegram

وَالسَّلَامُ عَلَىٰ مَنِ اتَّبَعَ الْهُدَىٰ {{«ሰላምም ቀጥተኛውን መንገድ በተከተለ ሰው ላይ ይኹን፡፡}}  [ ሱረቱ ጣሀ - 47 ] "ከወሰን መተላለፍና ከመንሸራተት ተጠብቆ ታማኝ የሆነውን የተቀና አቋም የተቸረ ታድሏል።!" ብዕሬን እንደ ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ ሰይፍ የሰላ አድርግልኝ🤲 ቻናሌ ላይ ስህተት ሲገኝ ቶሎ አሳውቁኝ @abuk29 https://t.me/darulekra

Показати більше
2 534
Підписники
+1424 години
+797 днів
+28830 день
Архів дописів
[ كتاب السُّنَّةِ ] (الترهيب من ترك السنة وارتكاب البدع والأهواء) ٥٩_ وعن العِرباض بن سارية رضي الله عنه؛ أنه سمع رسول الله ﷺ يقول: «لقد تركتُكم على مِثْلِ البيضاء، ليلُها كنهارِها، لا يَزيغُ عنها إلا هالكٌ». رواهُ: ابن أبي عاصم في «كتاب السّنة» بإسنادٍ حسن. قال العلامة الألباني رحمه الله: «البيضاء» أي: الملة والحجة الواضحة التي لا تقبل الشبه أصلاً، فصار حال إراد الشبه عليها كحال كشف الشبه عنها ودفعها، وإليه الإشارة بقوله: «ليلها كنهارها». 📖صحيح الترغيب والترهيب للإمام الألبانيّ(١٣٢).

سورة الكهف - القارئ: إدريس أبكر. https://t.me/darulekra

018.mp336.13 MB

044.mp38.43 MB

‏صورة من حسين عبد الله
‏صورة من حسين عبد الله

👉 አላህ ያዘዛትን አለባበስ ትታ የፋሽንና የባህል አለባበስ በመልበስ ኢስላም እንድትሸፍነው ያዘዛትን የሰውነት ክፍል ገልጣ፣ ወይም ለስሙ ያክል ብቻ ስስና ጠባብ ልብስ ተጠቅማ ከቤት የምትወጣ ሴት
👉 አላህ ያዘዛትን አለባበስ ትታ የፋሽንና የባህል አለባበስ በመልበስ ኢስላም እንድትሸፍነው ያዘዛትን የሰውነት ክፍል ገልጣ፣ ወይም ለስሙ ያክል ብቻ ስስና ጠባብ ልብስ ተጠቅማ ከቤት የምትወጣ ሴት በሄደችበት ሁሉ ወንጀለኛ ስትሆንና መላዕክትም ይረግሟታል የአላህ እና መልእክተኛው ﷺያዘዟትን ዓይነት ሙሉ ሒጃብ አድርጋ ምትንቀሳቀስ ሴት የትም፣ ምንም ላይ ሆና ዒባዳህ ላይ እንዳለች ነው የሚቆጠረው (ትክክለኛ ሒጃብ በማድረጓ ሁሌም/ የትም ሆና አጅር ታገኛለች) ይህም ትክክለኛና የተሟላ ሒጅብ አላህን  የሚያስደስት ሥራና ልክ እንደ ሰላት፣ ጾምና ሐጅ ትልቅ ወደ አላህ የሚያቃርብ ዒባዳህ በመሆኑ ነው ተገላልጦ መሄድ፣ ውበትና ፈታኝ የሰውነት አካልን ማሳየት ደግሞ አላህን የሚያስቆጣ ትልቅ ወንጀልና የሰው ልጅ ጠላት የሆነውን ሸይጣንን የሚያስደሰት ተግባርም ነው። ☞ የፈለግሽውን አይነት ልብስ እየለበሽ "ኢማን በልብ ነው" አትበይ! ይህ አባባልሽ ምሳሌው የፈተና ወረቀትሽ ምንም ሳትሰሪበት ለፈታኙ መልሰሽለት ምነው ሲልሽ "እውቀት በጭንቅላት ነው" እንደማለትሽ ነው እህቴ ሆይ የቱ ይሻልሻል?አጭር የዱንያ ቆይታ ላይ አላህ የሚወደውን ዓይነት አለባበስ ለብሶ ኣኺራህ ላይ ከአላህ ቁጣ ድኖ ጀነትን መሸለም? ወይስ ለትንሽ ጊዜ እንደፈለጉ በመሆን አላህን አስቆጥቶ ነገ ኣኺራህ ላይ መቀጣት?! ከቀልብሽ ሁኚ! ሁሉም (መልበስና መሰተሩም፣ መገላለጥና እዩኝ እዩኝ ማለቱም) ያልፋል፤ ግን አላህ ዘንድ ተፅፎ ይቀመጣል!! ☞ ሷሊህ ሴት ከሁሉም ነገር የተጠበቀች አይደለችም ነገር ግን ስትገሰፅ ትገሰፃለች ምክር ሲሰጣትም ምክሩን ተቀብላ ጌታዋን ምህረትን ጠይቃ ቶሉ ከስህተቷ ትመለስና በአዲስ መልክ ወደ ጌታዋ ትዞራለች። اللهم اجعل بنات المسلمين من الصالحات https://t.me/darulekra

⚠️❗️ ወላሂ ይህ አባባል እጅግ የሚያስፈራ ነው!❗️ ⚠️ «حقوق العباد لا تسقط بطول قيام، ولا حسن صيام، ولا بألف ختمة قرآن..» "የሰዎች ሀቅ በረጅም የለሊት ሶላት፣ ባማረ ፆም፣ ወይም ቁርኣንን ሺህ ጊዜ በማክተም አይሰረዝም..." «حقوق العباد لا تسقط إلا بعفو أصحابها.» "የሰዎች ሀቅ ሊሰረዝ የሚችለው ባለሀቆቹ (የበደልናቸው ሰዎች) አፉ ሲሉን (ይቅር ሲሉን) ብቻ ነው።" «"وعند الله تجتمع الخصوم"» "አላህ ፊትም ተከራካሪዎች (ባለሀቅ እና ባለዕዳዎች) ይሰበሰባሉ ! ✅ አጭር ማስታወሻ፡ በአላህ ሀቅ ላይ ያጠፋነውን (ለምሳሌ ሶላት ማሳለፍ፣ ፆም መተው) አላህ አዛኝ ስለሆነ በተውበት ሊምረን ይችላል። ነገር ግን የሰውን ሀቅ (የሰውን ገንዘብ መብላት፣ ስም ማጥፋት፣ ማማት፣ መበደል...) ያጠፋንበት ሰው በዱንያ ላይ ይቅር እስካላለን ድረስ አላህ አይምረንም። 🤲አላህ የሰውን ሀቅ ከመንካት ይጠብቀን!🤲 https://t.me/darulekra https://t.me/darulekra

አሁን ያለንበት ሁኔታ የሕይወታችን ማጠቃለያ አይደለም። ከዚህ ጨለማ በስተጀርባ ብሩህ ቀን እንደሚተካ ፈጽሞ አትዘንጉ። ነገ የተሻለ ይሆናል፤ አብሽሩ! መልካም ቀን https://t.me/darulekra

عَنِ ابْنِ عُمَرَ ، أَنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ كَانَ يُوتِرُ عَلَى الْبَعِيرِ. https://t.me/darulekra

   📘 ከዕለታት በአንዱ ቀን ዑርዋ ኢብኑ ዙበይር ወደ ኸሊፋው መጅሊስ ገባ። ኸሊፋው ዘንድ አንድ በሽምግልና ፊቱ የተጨማደደና ዐይኑን የታወረ አረጋዊ ተቀምጦ ነበር። ኸሊፋው ለዑርዋ "እስኪ ለዚህ ሽማግሌ ስለ ታሪኩ ጠይቀው" አለው። ዑርዋ "ሽማግሌው ሆይ! ታሪክህ ምንድን ነው?" አለው። ሽማግሌው... "ዑርዋ ሆይ! የአንዲት መንደር ነዋሪ ነበርኩኝ። በመንደሯ ከእኔ የበለጠ ሀብትም ይሁን ቤተሰብ ያለው አንድም ሰው አልነበረም። በአንዲት ምሽት ድንገተኛ ጎርፍ መጣና ሙሉ ሀብቴንና ቤተሰቦቼን ይዞብኝ ሄደ። ሌሊቱ አብቅቶ ፀሀይ ስትወጣ ዙርያዬን ብመለከት የእኔ ከምለው ነገር የቀረልኝ አንድ ልጄና አንድ ግመል ብቻ ሆነው አነኘኋቸው። ተክዤ በተቀመጥኩበት ግመሏ በርግጋ መፈርጠጥ ጀመረች። አስቁሜ ልመልሳት ከኋላዋ እየሮጥኩ መከተል ጀመርኩኝ። ቲንሽ እንደሮጥኩ ከበስተኋላዬ “አባዬ.... አባዬ” የሚል የህፃን ልጅ ጩኸት ተሰማኝ። ዞሬ ስመለከት ከጎርፍ የተረፈው የእኔው ልጅ ተኩላ አንጠልጥሎት እየሮጠ ነው። ግመሏን ትቼ ህፃኑን ተከተልኩኝ: ልደርስበትና ላስጥለው ግን አልቻልኩም። ከልጄ ተስፋ ስቆርጥ ወደ ግመሏ ተመልሼ መከተል ጀመርኩኝ። እንደምንም ደርሼበት ሊዘው ስጠጋው በእግሩ መታኝና ዐይኖቼን አፈሰሰብኝ። ይኸው እንደምታየኝ ሆኜ አረፍኩት" አለው። ዑርዋ ኢብኑ ዙበይር: "እሺ ከዚህ ሁሉ በኋላ ምንድን ነው ምትለው?" አለው....... ሽማግሌው: "በኢማን የተሞላ ልብና አላህን የሚዘክር ምላስ ለሰጠኝ አላህ ዘወትር አመሰግነዋለሁ!!" አው 📚 [سير أعلام النبلاء للذهبي] https://t.me/darulekra https://t.me/darulekra

አል ኢስራእ ወል ሚዕራጅ የሚባለው ጉዞ ከየት ወደ የት ነበር? ትክክለኛውን መልስ በመንካት የሚመጣላቹን የሰለፊዮች ቻናሉ ይቀላቀሉ።
አል ኢስራእ ወል ሚዕራጅ የሚባለው ጉዞ ከየት ወደ የት ነበር? ትክክለኛውን መልስ በመንካት የሚመጣላቹን የሰለፊዮች ቻናሉ ይቀላቀሉ።

043.mp320.17 MB

ከሁሉ የተሻለው ቀንህ፣ ከቁርኣን ጋር የኖርከው ቀን ነው። https://t.me/darulekra

، عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ مَسْعُودٍ ، قَالَ : خَرَجْنَا مَعَ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ وَنَحْنُ شَبَابٌ لَا نَقْدِرُ عَلَى شَيْءٍ، فَقَالَ : " يَا مَعْشَرَ الشَّبَابِ، عَلَيْكُمْ بِالْبَاءَةِ ؛ فَإِنَّهُ أَغَضُّ لِلْبَصَرِ، وَأَحْصَنُ لِلْفَرْجِ، فَمَنْ لَمْ يَسْتَطِعْ مِنْكُمُ الْبَاءَةَ فَعَلَيْهِ بِالصَّوْمِ ؛ فَإِنَّ الصَّوْمَ لَهُ وِجَاءٌ ". https://t.me/darulekra

🫵ከማህበራዊ ሚዲያ እብደትና ሱስ ስታገግም... በርካቶች ቀድመውህ የራቀ ጉዞ እንደተጓዙ ታያለህ። አንደኛው ቁርዓን ሲሃፍዝ፣ ሌላው መሠረታዊ የእስልምና እውቀቶችንና ልዩ ልዩ ጥበቦችን ሲቀስም አንተ ግን ስልክህ ላይ እንደተደፋህ ጊዜህ በከንቱ ያልፋል፤ ዕድሜህ ሲነጉድ እንኳ አይሰማህም። በአንተና በመቃብርህ መካከል ግን የቀረችው አንዲት እርምጃ ብቻ ልትሆን ትችላለች! https://t.me/darulekra

042.mp319.06 MB

👆👆👆ይነበብ ወሏሂ በጣም በጣም እጅግ በጣም አስተማሪ ተሪክ አንብቦቹ የተሰማቹን በኮሜንት ግለፁልኝ👇

➥ዘመናትን ተሻግረው የሰውን ልጅ በእንባ ካራጩ ታሪኾች መካከል የሰዕለባ ታሪክ አንዱ ነው።‼️ ሰዕለባ የአሏህን መልዕክተኛ (ﷺ) አብዝተው ከሚያገለግሉ የመዲና ታዳጊ ወጣቶች መካከል አንዱ ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን ነቢዩ (ﷺ) ሰዕለባን ለሆነ ጉዳይ ወደ ውጪ ይልኩታል። እርሱም የታዘዘበትን መልዕክት ይዞ በመንገድ ላይ ሳለ ከአንሷሮች መኖሪያ ቤቶች መካከል በሩ ገርበብ ብሎ የተከፈተን አንድ ቤት በአጋጣሚ አስተዋለ። ልክ በዚያው ቅፅበት በቤቱ ውስጥ ያለውን መጋረጃ ሀይለኛ ንፋስ ገልጦት ገላዋን እየታጠበች ባለች አንዲት እንስት ላይ በአጋጣሚ ዓይኑ አረፈ። ሰዕለባ በዚህ ሁኔታ እጅግ ደነግጦ መላ አካላቱ በፍርሃት ተንቀጠቀጠ። በፍጥነትም አካባቢውን ለቆ ወጣ። ነገር ግን ውስጡ ሰላም ሊያገኝ አልቻለም። በፅፅት እየተቃጠለ እንዴት እይታዬን መቆጣጠር አልቻልኩም? ረሱልን(ﷺ) ባየሁበት ዓይኔ ጭራሽ የሳቸውን መልዕክት ይዤ እየተጓዝኩ እንዴት ዓይኔ ሐራም ነገር ላይ ያርፋል? ምን አልባትም እኔ መናፍቅ ሆኜ ይሆን? እያለ ስቅስቅ ብሎ ያለቅስ ጀመር። ሐራም ባየሁበት አይኔ በድጋሚ ረሱልን(ﷺ) ማየት አይገባኝም አሏህ ይቅር እስኪለኝ አልያም መለከል መውት መጥቶ ሩሄን እስኪያወጣው በዚህ ኮረብታ ማሳለፍ ይኖርብኛል። በማለት ከመዲና ተራሮች ወደ አንዱ በመሸሽ ራሱን አገለለ። የአሏህ መልዕክተኛ (ﷺ) ለጉዳይ ልከውት ስለቆየባቸው ልጅ ማጠያየቅ ጀመሩ። ቀናቶች ተቆጠሩ ሳምንታትም አለፉ። ነገር ግን ስለ ሰዕለባ የተጠየቁ የመዲና ሰዎችን ሁሉ አናውቅም የሚል ምላሽ ብቻ ነበር የሚሰጡት። የሰዕለባ መጥፋት ያሳሰባቸው ነቢዩ(ﷺ) ዑመር ኢብኑል ኸጣብን እና ሰልማን አል ፋርሲን ከተወሰኑ ሶሀቦች ጋር አብረው እንዲፈልጉት ላኳቸው። ዑመር እና ባልደረቦቻቸውም በእግር በፈረስ በየቦታው ሲፈልጉት ቆይተው በስተመጨረሻ በመካና በመዲና መካከል ባለ አንድ ገለልተኛ ኮረብታ ላይ ደረሱ። በዚያም እረኞችን ተመልክተው ስለ ሰዕለባ አንዳንድ የአካል እና የሁኔታ ምልክቶችን በመንገር አይተውት እንደሆነ ጠየቋቸው። እረኞቹም ከዚያ ኮረብታ ስር እኛ ወተት እያለብን በነፃ የምንሰጠው አንድ ወጣት አለ፤ እዚህ ከመጣ እነሆ 40 ቀናትን አስቆጥሯል። ሌሊትም ቀንም ሳያቋርጥ በልቅሶ ያነባል፤ የዚህን ልቅሶውን ምክንያት ግን ሊነግረን ፈፅሞ አልፈቀደም አሏቸው። ዑመር እና ባልደረቦቻቸው ፀሐይ እስክትጠልቅ ድረስ በአቅራቢያው ተደብቀው የልጁን መውጣት ይጠባበቁ ጀመር። ፀሐይ ስታዘነብል ሰዕለባ ከተደበቀበት ተራራ ወጣ። እረኞቹም ምንም ሳይሉ ወተቱን አልበው ሰጡት። ነገር ግን ያ የተጠማ ወጣት ሁለት ጉንጭ እንደተጎነጨ አይኖቹ በእንባ ዘለላዎች ተሞሉ። ከውስጥ ቃጠሎው የተነሳ ወተቱን ጨርሶ መጠጣት አልቻለም። ኩባያውን መሬት ላይ ቁጭ አድርጎ ወደ ኋላው ሲዞር ዑመር እና አብረውት ያሉት ሶሃቦች ከተደበቁበት ወጥተው ያዙት። ሰዕለባም በድንጋጤ ምን ነካችሁ? ለመሆኑ የአሏህ መልዕክተኛ(ﷺ) እኔ መናፍቅ መሆኔን የሚገልጽ ወሕይ ወረደላቸው? ለዚህ ነው ልትፈልጉኝ የመጣችሁት? ሲል ጠየቃቸው። ዑመርም በጭራሽ እንዲህ አይደለም! በማለት መለሱለት። ሶሃቦቹ በልጁ ላይ በደረሰው ነገር ተጨንቀው በለቅሶ እና በረሃብ ተጎሳቁሎ የነበረውን ሰዕለባን ይዘውት ወደ መዲና ተመለሱ። ረሱል(ﷺ) ሰዕለባ ወዳለበት ቤት አቀኑ፤ አስፈቅደውም በሩን ከፍተው ገቡ። ሰዕለባ ግን ከነበረው ሃፍረት የተነሳ የነቢዩን(ﷺ) ፊት ላለማየት ሲል ፊቱን ወደ መሬት ደፍቶ አቀረቀረ። በዚህ ጊዜ ነቢ ጭንቅላቱን ቀና አድርገው በገዛ ታፋቸው ላይ አስደገፉት። ሰዕለባ ግን ያ ነቢየሏህ(ﷺ) ይህንን በወንጀል የተጨማለቀን ራስ ከሰውነትዎ ላይ ያንሱልኝ አላቸው። እሳቸውም ለመሆኑ ምን ሆንክ? ምንስ ያሰጋሃል? ሲሉ ጠየቁት። እርሱም የአሏህ ከባድ ቅጣት ያሰጋኛል ሲል መለሰ። ታዲያ ምንስ ትፈልጋለህ? አሉት፤ እርሱም የጌታዬን ሰፊ እዝነት እና ምህረት ብቻ ሲል መለሰላቸው። አዛኙ ነቢም(ﷺ) የምትፈልገውን እዝነት እንድታገኝና ከምትፈራው ቅጣት እንድትጠበቅ እኔ ራሴ ዋስ እሆንሃለሁ ሲሉ አረጋገጡለት። በዚያው ቅፅበት ሰዕለባ ያ ነቢየሏህ የጉንዳን መንጋ በደም ስሬ ውስጥ እየተግተለተለ እንደሚሄድ ዓይነት ከባድ ስሜት ይሰማኛል አላቸው። እሳቸውም ይህማ የሞት መምጣት ምልክት ነው፤ እነሆ አሁን ጌታህን ልትገናኝ ነው በማለት የሸሃዳ ቃል አስታወሱት። እርሱም ሸሃዳውን ይዞ ወደማይቀረው ዓለም ተጓዘ። የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) በጀናዛው ላይ ሰግደውበት ወደ ቀብር ቦታ በሚወስዱት ጊዜ አካሄዳቸው ልክ በጠባብ መንገድ ላይ እንደሚጓዝ ሰው በጣቶቻቸው ጫፍ ብቻ እየተራመዱ ነበር። ይህንን ያስተዋለው ዑመር መንገዱ ምንም ዓይነት ጭንቅንቅ በሌለበት ሁኔታ ለምን እንዲህ እንደሚራመዱ ጠየቃቸው። እሳቸውም ወሏሂ ያ ዑመር የሰዎች ጭንቅንቅ ሳይሆን እጅግ በጣም ብዙ መላዒኮች የሰዕለባንን ጀናዛ ለመሸኘት መንገዱን  አጨናንቀውታል። እኔም ከእነርሱ ጋር እየተጋፋሁ እንዳረግጣቸው በጥንቃቄ ተጠንቅቄ ነው እንዲህ በጣቶቼ ጫፍ የምራመደው በማለት መለሱለት። ለመሆኑ የእኛስ እይታ? አንዴ ሳይሆን በቁጥር ልናስበው በማንችለው አያሌ ጊዜያት አሏህን አላመፅንም? እይታችንን፣ ልባችንን፣ ሕይወታችንን በሀራም ድንበር ጥሰቶች አላቆሸሽንም? ታዲያ እንደዚህ ወጣት አልቅሰን ወደ አሏህ መመለስ አይጠበቅብንምን? ጌታችን አሏህ በተከበረዉ ቃሉ እንዳለው👇 ''ለነዚያ ላመኑ ሰዎች ልቦናቸው ለአሏህ ግሳፄ የሚፈራበት ጊዜ አልደረሰምን?[ሱረቱል አል ሐዲድ 65] منقول ከማስተካከያ ከተወሰኑ ጋር ✅ https://t.me/darulekra https://t.me/darulekra