1 951
Підписники
+124 години
+97 днів
+2730 день
Архів дописів
1 951
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
+1
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣
➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡
➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ
⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም።
⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።
1 951
ሬነሳንስ ት/ቤት አዲስ አበባለ6፤8 እና 12ተኛ ከፍል ተማሪዎች የትምህርት ቤቱ የመጨረሻ ሞዴል የሚሰጠው ሐሙስ (27/9/2018)፤ አርብ (28/9/2018) እና ሰኞ (1/10/2018) ዓ/ም ሲሆን ተማሪዎች ተገቢውን ዝግጅት አድርገው እንዲገኙ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ የትምህርት አይነቶችህ የሚሰጡት የሀገር እና ክልል አቀፍ ፈተና በሚሰጥበት ፕሮግራም ነው።
ት/ቤቱ
1 951
ሬነሳንስ ት/ቤት አዲስ አበባበሀገራዊ ምርጫ ምክንያት ነገ ማክሰኞ(25/9/2018) እና ዕረቡ(26/9/2018) ትምህርት አይኖርም።
ት/ቤቱ
1 951
ለ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና የኦንላይን ልምምድ ያድርጉ!
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ተፈታኞች ፈተና የሚለማመዱበት አድራሻ ይፋ አድርጓል።
ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ያለውን ሊንክ በመጠቀም፣ User Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Password በሚለው ላይ 1234 በማስገባት በዴስክቶፕ ኮምፒውተር፣ በላፕቶፕ፣ በታብሌት፣ በስልክ እና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሳሪያዎች ማንኛውንም አይነት የኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም ከነገ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ እንደሚችሉ ተገልጿል።
@AAEB
1 951
Repost from Addis Ababa Education Bureau
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
(ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሰጠው በዚህ ከተማ አቀፍ ፈተና በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
1 951
ግንቦት 5/2018 ዓ.ም
ሬነሳንስ ት/ቤት አዲስ አበባለተከበራችሁ የተማሪ ወላጆች/አሳዳጊዎች ቅዳሜ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 – 6፡30 ሰዓት የልጅዎን የትምህርት አቀባበል እና ባህሪ በማሻሻል ከፍተኛ ውጤት እንዲያስመዘግብ በወላጆችና በመምህራን መካከል በሚደረገው ውይይት (Open house program) ላይ እንዲገኙ በአክብሮት እየገለፅን በዕለቱ የ3ኛ ሩብ ዓመት ውጤት ለወላጆች የምንሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ት/ቤቱ
1 951
ሬነሳንስ ት/ቤት አዲስ አበባለ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር በተገናኘ የምናከናውነው ስራ ስላለ ነገ (ሚያዝያ 7, 2018) ለፈተና ስትመጡ ለፋይዳ የተመዘገባቹበትን ስልክ ቁጥር ሲም ካርድ የያዘ ስልክ ይዛችሁ እንድትገኙ እንገልፃለን።
ት/ቤቱ
1 951
የካቲት 25/2018 ዓ.ም ሬነሳንስ ት/ቤት አዲስ አበባለውድ የተማሪ ወላጆች መቄዶንያ የአረጋውያን በጎ አድራጎት ማህበር በተለያዩ ጊዜያት በት/ቤቱ በአካል እየተገኙ ድጋፍ እንድናደርግላቸው መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ በመሆኑም ውድ ወላጆች ለዚህ ቅንና በጎ ዓላማ እስከ ሰኞ የካቲት 30/2018 ዓ.ም ድረስ የቻላችሁትን ያክል እገዛ እንድታደርጉ በድጋሜ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ ገቢ የሚያደርጉት ልጆት በሚማርበት የት/ት እርከን ሲሆን ከዚህ በታች በተገለፀው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር ይሆናል፡፡ የኬጂ/ቅድመ 1ኛ ት/ቤት 1000733970538 የ1ኛ ና መካከለኛ ደረጃ ት/ት ቤት 1000733963933 የ2ኛ ደረጃ ት/ት ቤት 1000733976768
ት/ቤቱ
1 951
ሬነሳንስ ት/ቤት አዲስ አበባለተከበራችሁ የተማሪ ወላጆች/አሳዳጊዎች እሁድ የካቲት 22/2018 ዓ.ም የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት የተማሪዎች ውጤት የሚሰጥ ሲሆን ውድ ወላጆች በዕለቱ በተማሪዎች ስነ ምግባር፣ውጤት ና በመማር ማስተማር አጠቃላይ ሁኔታ ላይ አጭር ውይይት የሚደረግ በመሆኑ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በት/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት የውይይቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ እና የልጆትን ውጤት እንዲወስዱ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
ት/ቤቱ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
