cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

EPS (Ethio-Parents' school)

Ethio-Parent's School Student Resource Center

Більше
Рекламні дописи
8 943
Підписники
+824 години
+307 днів
+10930 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

ለገርጂ፣ ጉለሌ እና ጉርድሾላ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤቶች የነባር ተማሪዎች ወላጆች በሙሉ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ባወጣው ዓመታዊ የትምህርት ካሌንደር መሠረት የ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የነባር እና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ከሰኔ 28 እስከ ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡ኆኅተ ጥበብ አክሲዮን ማህበር(ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት)
Показати все...
Andaregachew1: 🫶ለ6ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መብቶችና እና ግዴታዎች 👉ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት  አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት። 👉ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል። 👉በመጨረሻም የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት  የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል። 👉ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፍ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)። 👉ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ 👉የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል። 👉ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት  የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ። 👉እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ። 👉ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ  ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል። 👉ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል። ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም። 👉ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው። ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም። 👉ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም። ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት   እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። 👉ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል። 👉ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል። 👉ማየት ለተሳነው እና ድጋፍ የሚሹ ተፈታኝ የፈተናውን ጥያቄዎች የሚያነብለትና የሚሰጣቸውን መልሶች የሚያጠቁርለት ፈታኝ በግሉ እንዲመደብለት ይደረጋል። 👉ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ የሚችሉት በቅድሚያ ትም/ቤት በተመዘገበበት ጣቢያ እንጂ የፈተና ጣቢያ ቀይረው ሊፈተኑ አይችሉም። ✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️ ለተፈታኞች የተከለከሉ ነገሮች የግል ስልክ (Mobile phone)፣ ታብሌት፣ የጆሮ ማዳመጫ (earphone) እና ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣የእጅ ሰአት፣ ማንኛውም የግል ጽዳት ማስጠበቂያ ሆነ ማስዋቢያ ቁሳቁስ፣ ማንኛውም ዕቃ ለመያዣነት የሚያገለግል ቦርሳ/እቃም የያዘ ቦርሳ፣ ማንኛውም ስለት ነክ ነገርና ብረት መልካም የፈተና ዝግጅት! Please let us share these important messages to parents 🙏 🫶ለ6ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መብቶችና እና ግዴታዎች 👉ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት  አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት። 👉ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል። 👉በመጨረሻም የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት  የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል። 👉ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፍ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)። 👉ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ 👉የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል። 👉ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት  የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ። 👉እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ። 👉ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ  ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል። 👉ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል። ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም። 👉ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው። ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም። 👉ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም። ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት   እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። 👉ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል። 👉ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል። 👉ማየት ለተሳነው እና ድጋፍ የሚሹ ተፈታኝ የፈተናውን ጥያቄዎች የሚያነብለትና የሚሰጣቸውን መልሶች የሚያጠቁርለት ፈታኝ በግሉ እንዲመደብለት ይደረጋል። 👉ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ የሚችሉት በቅድሚያ ትም/ቤት በተመዘገበበት ጣቢያ እንጂ የፈተና ጣቢያ ቀይረው ሊፈተኑ አይችሉም። ✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️ ለተፈታኞች የተከለከሉ ነገሮች የግል ስልክ (Mobile phone)፣ ታብሌት፣ የጆሮ ማዳመጫ (earphone) እና ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣የእጅ ሰአት፣ ማንኛውም የግል ጽዳት ማስጠበቂያ ሆነ ማስዋቢያ ቁሳቁስ፣ ማንኛውም ዕቃ ለመያዣነት የሚያገለግል ቦርሳ/እቃም የያዘ ቦርሳ፣ ማንኛውም ስለት ነክ ነገርና ብረት መልካም የፈተና ዝግጅት!
Показати все...
የ2015ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የፈተና አስተዳደር ማስፈጸሚያ ሰነድ የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች 1.የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ 2.በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ 3.ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ 4.ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ 5. በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ 6) ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ 7.ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ 8.መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ 9. ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
Показати все...
አክሲዮን ለመሸጥ በድጋሚ የወጣ ማስታወቂያ ኆኅተ ጥበብ አክሲዮን ማህበር አዳዲስ አክሲዮኖችን በማውጣት ለነባርና አዲስ ለሚገዙ ባለአክሲዮኖች በመሸጥ ላይ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ለሦስተኛ ጊዜ የተራዘመው የመሸጫው የጊዜ ገደብ የካቲት 17ቀን 2016 ዓ.ም ያበቃ ቢሆንም የማህበሩ ዳይሬክተሮች ቦርድ ሽያጩ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲራዘም የወሰነ ስለሆነ ለመግዛት የምትፈልጉ ዘወትር በሥራ ሰዓት ገርጂ በሚገኘው የማህበሩ ጽ/ቤት በመቅረብ አክሲዮኖችን ለመግዛት የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡ የኆኅተ ጥበብ አክሲዮን ማህበር የዲሬክተሮች ቦርድ
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
reminder
Показати все...
ግንቦት 02 ቀን 2016 ዓ.ም ለተከበራችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች የ2016ዓ.ም የ4ተኛዉ ሩብ ዓመት የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ከሚያዝያ 21 ቀን 2016ዓ.ም እስከ ግንቦት 5 ቀን 2016ዓ.ም ወይም April, 29/2024-May13/2024 እንደሆነ ይታወቃል፡፡በመሆኑም መደበኛ የመክፈያ ጊዜዉ ከመጠናቀቁ በፊት ለተጨማሪ ወጪ/ቅጣት/ እና ካላስፈላጊ እንግልት እንዳይዳረጉ ክፍያዉን በወቅቱ እንዲከፍሉ ከታላቅ ትህትና ጋር እናሳስባለን፡፡ ት/ቤቱ
Показати все...
በገርጂ፣ ጉለሌ፣ እና ጉርድ ሾላ ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤቶች ልጆቻችሁን በማስተማር ላይ ለምትገኙ የተማሪ ወላጆች/አሳዳጊዎች በሙሉ የ2016 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የአራተኛው ሩብ ዓመት የትምህርት አገልግሎት የመክፈያ ጊዜ የሚጠናቀቀው ግንቦት 05 ቀን 2016 ዓ.ም ( May 13/2024) ስለሆነ የተሰጠው ጊዜ ከመጠናቀቁ በፊት ክፍያውን እንድታከናውኑ አበክረን እናሳስባለን፡፡ ኆኅተ ጥበብ አ.ማ(ኢትዮ-ፓረንትስ ት/ቤት)
Показати все...
school fee notice.docx0.13 KB
school fee.docx0.13 KB
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.