uk
Feedback
Abu hasenet

Abu hasenet

Відкрити в Telegram

((በአንደበትህ መጣራት ባትችል በሰው አንደበት ተጣራ)) እንዳያመልጥዎ የተለያዩኢስላማዊ 📌ዳእዋቶች 📌ንጽጽሮች 📌 አስፈላጊ ዜናዋች እምንለቅበት ቻናል ነው ለሁሉ ተደራሽ እንዲሆን ሼር በማድረግ በአቅምዎ ዳዕዋ ውን ያስፋፉ🙏 ለትብብሮ እናመሰግናለን ✔️

Показати більше
692
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
-1630 день
Архів дописів
ኢሥላም የተስፋፋው በሰይፍ ነው እያላችሁ ስትቀጥፉ አልነበረም እንዴ? ታዲያ ኢሥላም ወደ ኢትዮጵያ የገባው ለምን በነጋዴዎች አማካኝነት ሆነ? ለምን በሰይፍ አልሆነም? እንደው እውነታው ሌላ የእናንተ
ኢሥላም የተስፋፋው በሰይፍ ነው እያላችሁ ስትቀጥፉ አልነበረም እንዴ? ታዲያ ኢሥላም ወደ ኢትዮጵያ የገባው ለምን በነጋዴዎች አማካኝነት ሆነ? ለምን በሰይፍ አልሆነም? እንደው እውነታው ሌላ የእናንተ ቅጥፈት ሌላ😁
✍ ሙከሚል ሙሥሊም ልጅ
https://t.me/mukamil12

በነገራችን ላይ ክርስትያኖች ሙሥሊሞችን ለማጥቃትና ለማጥፋት ከየትኛውም ሐገር ሆነ ሐይማኖት ጋር ትብብር ያደርጋሉ! ለዚህ ሁነኛ ምሳሌ በኢማሙ አህመድ(አህመድ ግራኝ) ጊዜ የተደረገውን ማየት በቂ ነው! ክርስትያኖች ኢማሙ አህመድን ለመዋጋትና ሙሥሊሞችን ለማጥፋት ከ ፖርቹጋል ጋር አንድ ሆነው ነበር። በዛን ጊዜ ፖርቹጋላዊያን የካቶሊክ እምነት ተከታይ ነበሩ ዛሬ በኢትዮጵያ የተስፋፋው የካቶሊክ እምነት ዋና መሰረቱም ያ ጦርነት ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሙሥሊሞችን ለማጥፋት ከማንም ሐገር ከየትኛውም ሐይማኖት ጋር ትተባበራለች። ዛሬ ላይ እንኳን ልብ ብላችሁ ከተመለከታችሁ እስራኤል በፍልስጥኤማውያን ላይ የምታደርገውን ጭፍጨፋ በግልጽ ድል ለእስራኤል እያሉ ሲደግፉ ትመለከታላችሁ።
✍ ሙከሚል ሙሥሊም ልጅ
https://t.me/mukamil12

ያለቀሰ ሁሉ ተበዳይ መስሏችሁ ከሆነ ተሳስታችኋል! የዩሱፍን ወንድሞች ተመልከት በዳዮቹ እነርሱ ሆነው ሲያበቁ ወደ አባታቸው ሲመለሱ ግን ተበዳይ ለመምሰል እያለቀሱ ነበር የመጡት። እናም ያለቀሰ ሁሉ ተበዳይ አይደለም።😊 وَجَاءُوا أَبَاهُمْ عِشَاءً يَبْكُونَ (📗ሱረቱ ዩሱፍ - 16) አባታቸውንም በምሽት እያለቀሱ መጡት፡፡
✍ሙከሚል ሙሥሊም ልጅ
https://t.me/mukamil12

✨መካ ግርማ ሞገስ ያላት ውብ ከተማ ስትሆን መዲና ደግሞ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ምድር ናት። 🌹 አንደኛዋ በፍርሀትና በናፍቆት ስታንቀጠቅጥ፣ ሌላኛዋ ደግሞ በደስታና በሰላም ታክማለች። 👉መካ
✨መካ ግርማ ሞገስ ያላት ውብ ከተማ ስትሆን መዲና ደግሞ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ምድር ናት። 🌹 አንደኛዋ በፍርሀትና በናፍቆት ስታንቀጠቅጥ፣ ሌላኛዋ ደግሞ በደስታና በሰላም ታክማለች። 👉መካ የጉዞው መጀመሪያ ስትሆን መዲና ደግሞ የነፍስ ማረፊያ መጠጊያ ናት። የመካና የመዲና ለሊቶች ልዩ ውበት አላቸው። ለሊቱ ሲገሰግስና የሰማዩ ድምቀት ሲጨምር የመስጂዱ ነጫጭ እምነበረድ ወለሎች በብርሀን ይንፀባረቃሉ? በ ሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን በዝምታና በተመሰጥኦ ዱዐ ሲያደርጉ ከተሞቹ በሰላም እቅፍ ውስጥ ይረጋሉ። 👉ወደነዚህ ከተሞች የተጓዘና የአየሩን ጠረን ያሸተተ ሰው አካሉ ይመለስ ይሆናል እንጂ ልቡ ግን እዚያው ለዘላለም ቀርቶ ይኖራል። 🤲🤲አላህዋ! ዳር ቆመን ታዛቢ ብቻ አታድርገን። ሩህ ጀሰዳችን ለትዕዛዝህ የሰላ ባሮችህ አድርገኸን እኛንም ከቤትህ ከደጃፍህ አመላልሰን። "ኑ" የምትለንን ቀን ቅርብ አድርገውና ሀጅ ዑምራውን፣ መካ መዲናውን፣ሚና ሙዝደሊፋውን ወፍቀን ያረብ....... አሰላሙ አለይኩም መሰዓል ኸይር ወዳጆቼ?

አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ! / ሰላም ጤና ይስጥልኝ! 🌸 የቤተሰብ፣ የጋብቻ እና የውርስ ጉዳዮች በማንኛውም ጊዜ ሊያጋጥሙን የሚችሉ የዕለት ተዕለት የሕይወታችን አካል ናቸው። ታዲያ በ
አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ! / ሰላም ጤና ይስጥልኝ! 🌸 የቤተሰብ፣ የጋብቻ እና የውርስ ጉዳዮች በማንኛውም ጊዜ ሊያጋጥሙን የሚችሉ የዕለት ተዕለት የሕይወታችን አካል ናቸው። ታዲያ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ መብትና ግዴታዎን በምን ያህል ደረጃ ያውቃሉ? 🤔 ይህን ክፍተት የሚሞላ እና ራስዎን ከተጠያቂነት እንዲጠብቁ የሚረዳ ወሳኝ የሕግ መጽሐፍ እነሆ ተዘጋጅቶሎታል! 📚✨ 📩 መጽሐፉን ለማዘዝ ወይም ለማማከር በዚህ የቴሌግራም አድራሻዬ ያግኙኝ👇 👉 @Hikmetulahbedredin

አንድ ጀግና ላስተዋዉቃችሁ! በየጦር ሜዳው የጣዖት አምላኪዎችን አንገት ቀንጥሶ ከአፈር ጋር በመቀላቀል ረገድ አቻ ያልተገኘለት ጀግና ተዋጊ ነው። የአሏህንና የነቢዩን 🤍 ጠላቶች በማሸበር ወደር ያል
አንድ ጀግና ላስተዋዉቃችሁ! በየጦር ሜዳው የጣዖት አምላኪዎችን አንገት ቀንጥሶ ከአፈር ጋር በመቀላቀል ረገድ አቻ ያልተገኘለት ጀግና ተዋጊ ነው። የአሏህንና የነቢዩን 🤍 ጠላቶች በማሸበር ወደር ያልተገኘለትም ጀግና ነዉ። ወደ ጦር ሜዳ ሲገባ ጭንቅላቱ ላይ የሚጠመጥማትን ቀይ አማይማ የተመለከተ ከሀዲ በሙሉ በፍርሃት ይንቀጠቀጥ ነበር። ግና አንድ መሰረታዊ የሆነ ትልቅ ችግር ነበረበት፤ ሁልጊዜም የአልኮል መጠጥ ይጠጣል፣ ጭንብስ ብሎም ይሰክራል። የአሏህን ሕግ በተደጋጋሚ እየጣሰ ስለሚያስቸግር በአደባባይ ብዙ ጊዜ ተገርፏል። ከዚህ አስከፊ ድርጊቱና ሱሱ ባለመላቀቁ ምክንያት በመጨረሻ በእግረ ሙቅ ተጠፍሮ በግዞት ወደ እስር ቤት ተወርውሮ ነበር። ዕለቱ የቃዲሲያ ዘመቻ እየተካሄደ የነበረበት ወቅት ነበር። አቡ ሚህጀን የታሰረው ጦርነቱ ከሚካሄድበት ሜዳ እጅግ ሳይርቅ በቅርብ ርቀት ላይ ነበር። ከታሰረበት ሆኖ የፈረሶችን ማሽካካት እና የሰይፎች ግጭት ሲሰማ መታሰሩንና ከትግሉ መራቁን አምርሮ ጠላው። ከተጋጋለው ጦር መሀል ገብቶ የአሏህን ጠላቶች አንገት በሰይፍ መሸልቀቅን እና ለአሏህ ዲን መዋጋትን በእጅጉ ናፈቀ። ከአይኖቹ እምባን እያረገፈ ውስጡ ክፉኛ ተረበሸ፤ የጂሃድ ፍቅር እንደ ነበልባል እያንገበገበ አላስችል ቢለው የታሰረበትን ክፍል በር በሀይል ደብድቦ ለጦር አዛዡ ለሰዕድ ኢብን አቢ ወቃስ 🤎 ባለቤት መልዕክት ላከ። እንዲህም አላት በአሏህ ይሁንብሽ! ካቴናዬን ፈተሽ የጦር መሳሪያና የሰዕድን ፈረስ አዘጋጅተሽ የናፈቅኩትን ጂሃድ እንድካፈል አድርጊኝ። ወደ ካፊሮች መሃል ገብቼ እፋለም ዘንድ እርጂኝ፤ በሕይወት ከተረፍኩ ራሴ መጥቼ የእስር ቤቱን በር በላዬ ላይ እከረችማለሁ፤ እግሬንም መልሼ እታሰራለሁ ሲል ተማፀናት። የጦር መሪው ሚስት የአቡ ሚህጂን እውነተኛ የጂሃድ ቁርጠኝነት ተመልከታ ፈረስና ሰይፍ ሰጥታ ለቀቀችው። አቡ ሚህጀንም ማንነቱን ለመሸፈን ፊቱን በጨርቅ ሸፍኖ ልክ እንደ መብረቅ ወደ ጦር ሜዳው መሃል ሰፈረ። በዚያን ወቅት ካፊሮች የበላይነትን ለመቆጣጠር ቀርበዋል። የሙስሊሙም ጦር ተዳክሞ ነበር። በዚህ አስጨናቂ ቅጽበት አቡ ሚህጀን ከመሃላቸው ተከሰተ፤ ጠላትን እየበተነ አንዱን በአንዱ ላይ አነባበረው። ድል ወዲያውኑ ወደ ሙስሊሞች ማዘንበል ጀመረ። የካፊርን ደም የተጠማው አቡ ሚህጀን የአሏህንና የሙስሊሙን ጠላቶች እንደ ቅጠል አረገፋቸው፤ ከፊቱ የቀረበውን የጠላት ጦር አንገት እየቀነጠሰ ወደ መሃል ገሰገሰ። የሙስሊሙ ጦር አዛዥ ሰዕድ 🤎 የዚህን ተዋጊ ጀግንነት እየተመለከተ እንዲህ በፅናት የአሏህን ጠላቶች አመድ የሚያደርገው ይህ ፈረስና ተዋጊ ማን ነው? ሲል ጠየቀ። የሚያውቀው ሰው ግን ጠፋ፤ ሰዕድም በመገረም ፈረሱ የኔን ፈረስ በልቃዕን ይመስላል። የአጠቃቁ ስልቱ ደግሞ የአቡ ሚህጀንን ይመስላል። ነገር ግን አቡ ሚህጀን የታሰረ በመሆኑ እርሱ ሊሆን አይችልም አለ። ጦርነቱ በሙስሊሞች ድል አድራጊነት መጠናቀቁን የተመለከተው አቡ ሚህጀን በገባው ቃል መሰረት ሳይዘገይ ተመልሶ ወደ እስር ቤቱ ገባና በጦርነት የደከሙ እግሮቹንና እጆቹን በካቴና ጠፍሮ አሰራቸው። ሰዕድ 🤎 ከጦር ሜዳ ወደ ቤቱ ሲመለስ ሚስቱ ዛሬ ውጊያው እንዴት ነበር? በማለት ጠየቀችው። ሰዕድም መጀመሪያ ላይ የሽንፈት ማቅ ልንከናነብ ቀርበን ነበር፤ አሏህ ግን ሳናስበው አንድ ጀግና የጦር ተዋጊ ላከልንና ያ የመነመነ የድል ተስፋችን ወደ እኛ ተቀልብሶ ለማሸነፍ ቻልን። አቡ ሚህጀንን አስሬው ባልሄድ ኖሮ ያ ጀግና ተፋላሚ እርሱ ነው ብዬ እጠረጥር ነበር በማለት ተናገረ። ሚስቱም በአሏህ ይሁንብኝ ያ ተዋጊ ራሱ አቡ ሚህጀን ነው ብላ የተከሰተውን በሙሉ አስረዳችው። በሁኔታው በእጅጉ የተደሰተው ሰዕድ ወዲያውኑ አቡ ሚህጀንን አስጠርቶ ካቴናውን እየፈታ በአሏህ ይሁንብኝ ከአሁኗ ሰዓት ጀምሬ አላስርህም፣ አልገርፍህም፤ በነፃ ለቅቄሃለሁ አለው። አቡ ሚህጀንም ቀጠል በማድረግ በአሏህ ይሁንብኝ እኔም ከዛሬ ጀምሬ አልኮል አልቀምስም፣ አልሰክርም በማለት መለሰ። ከዛች ቀን ጀምሮ አቡ ሚህጀን መጠጥን ፈፅሞ በመተው አሏህን ከሚፈሩ ታላላቅ ሙጃሂዶች አንዱ ሆኖ ዘለቀ። t.me/IbnuHashm

የአቡ ጃዕፈር አል ወራክ የልጅ ልጅና የኢስላማዊቷ አንደሉስ የፅናት ተምሳሌት የሆነች ትጉህ ሙጃሂድ ነበረች። ከአባቷ የወረሰችው ጥልቅ ንባብና የዕውቀት ፍቅር ከነቤተመፅሕፍቱ የተሰጣት ትልቅ አደራ ነ
የአቡ ጃዕፈር አል ወራክ የልጅ ልጅና የኢስላማዊቷ አንደሉስ የፅናት ተምሳሌት የሆነች ትጉህ ሙጃሂድ ነበረች። ከአባቷ የወረሰችው ጥልቅ ንባብና የዕውቀት ፍቅር ከነቤተመፅሕፍቱ የተሰጣት ትልቅ አደራ ነበር። ገና በልጅነቷ የካቶሊክ መስቀላውያን ወታደሮች የእስልምናን መብራት ለማጥፋት ቁርዓንን፣ ኢስላማዊ የታሪክ መጻሕፍትን እና በሙስሊም ሳይንቲስቶች የተቀመሩ የምርምር ውጤቶችን በግራናዳ የረምላ አደባባይ ላይ በግፍ ሲያቃጥሉ በዓይኗ ተመልክታ በቁጭት አድጋለች። ሰሊማ በአንደሉስ ከነበሩት ጥቂት የበሰሉ ሴት ምሁራን መካከል አንዷ ናት። በተለይም በሕክምናው ዘርፍ የላቀ ብቃት የነበራት ሊቅ ነበረች። በገዛ ቤቷ ውስጥ ለሕሙማን የሚሆኑ መድሃኒቶችን የምታመርትበት የራሷ የሆነ የላቦራቶሪ ክፍል ሳይቀር ነበራት። የክርስትና እምነት በአንደሉስ ምድር ላይ በሀይል እንዲሰፍን ተደርጎ ሙስሊሞችን በግድ የማክፈር የኢንክዊዚሽን ዘመቻ ሲጀመር ባለቤቷ ሰዐድ አል ማሊቂ አቋሙን ያልሸጠ ሙጃሂድ በመሆኑ ከመስቀላውያኑ አደን በመሸሽ ቀን ቀን በምስጢር ይሸሸግ ነበር። ሌሊት ሌሊት በድብቅ ወደ ቤቱ በመምጣት ከባለቤቱ ከሰሊማ ጋር ይገናኛል። ጥንቆላና ድግምት ትሰራለች፤ ሌሊት ሌሊት በአየር ላይ እየበረረች ከሰይጣን ጋር ዝሙት ትፈፅማለች፤ ከእርሱም አርግዛለች በሚል ክስ በቁጥጥር ሥር አዋሏት። በመቀጠልም አሰቃቂ ውሳኔዎችን በሚያስተላልፈውና የጭካኔ ማዕከል በነበረው መሐኪመ ተፍቲሽ በአንደሉስ ቤተ ክርስቲያን ፍርድ ቤት ፊት ለፊት አቆሟት። በችሎቱም ላይ በነቢዩ 🤍 የእስራእ ወል ሚዕራጅ ጉዞ አምናለች፤ ከሰይጣንም አርግዛለች በሚል ከንቱ ሰበብ የስቅላትና የሞት ፍርድ ተወሰነባት። ከታሰረችበት እስር ቤት ውስጥ በህይወትና በሞት መካከል ሆና ታጣጥራለች። እርግጫውና ዱላው ከመደፈሯ ጋር ተደማምሮ የመጨረሻ እስትንፋሷ ላይ ተቃርባለች። ጌታዬ አሏህ ነው በማለቷ ብቻ በመስቀላዊያን ወታደሮች ተደፍራለች። በሆዷ ውስጥ ከሐላል ባለቤቷ ያገኘችውን ፅንስ ተሸክማ ሳለች በጀርባዋ አስተኝተው ሆዷን በስለታማ ከስክስና በደንዳና ዱላ ይመቷት ያዙ። ከዓይኗ ኩልል ብሎ የሚወርደው የሕመም ዕንባ ከአፏ ከሚፈሰው የደም ጎርፍ ጋር ተቀላቅሎ ከንፈሯን አርሶታል። ከማህፀኗ ውስጥ ፅንሱ እየተቆራረጠ ሲወጣ አቅሟን ሙሉ በሙሉ አሳጣት። ወታደሮች ግን በዚህ አላበቁም፤ በትከሻቸው ተሸክመው የሽንት ቤት መቀመጫ ቀዳዳ ላይ በአፏ አስተኟት። በእጃቸው በያዙት ስለታማ ቢላ እጅግ በሚዘግን ሁኔታ ጡቷን ቆረጧት። በዚህ ሁሉ የስቃይ ጣር ውስጥ ሆና እስትንፋሷ ሊቋረጥ አፋፍ ላይ በደረሰበት ጊዜ አንገቷን ወደ ላይ አቅንታ በደካማ ድምፅ ''ጌታዬ ሆይ! በዚህች ምድር ላይ በሕይወት የመቆየቴ ብቸኛ ምክንያት አንተን ማምለክና መገዛት ነበር፤ ግና የሚገባህን ያህል ሳልገዛህ ቀረሁ በማለት ተናገረች። ስለ አሏህ ብቸኛ ተመላኪነትና ረሱልም የአሏህ መልዕክተኛ መሆናቸውን መስክራ ሩኋ ከጀሰዷ ተላቀቀ። የአንደሉሷን ሸሂድ ሰሊማ ቢንት ጃዕፈርን አሏህ ጀነተል ፍርደውስ ወራሽ ያድርጋት! t.me/IbnuHashm‌‌

photo content

በሐራም ግንኙነት ውስጥ ብዙ ነገሮችን ታጣለህ። ገንዘብህን፣ ግዜህን ከዛም ወንጀል ላይ ትወድቃለህ። አላህ ይጠብቀን🤲

አንደሉስ → የዛሬዋ ስፔን‼ ================ (በአውሮፓ እምብርት ያበራችው የኢስላም ፀሐይ እና የጠፋችው ውብ ገፅታ!) || ✍️ «የአይቤሪያን ልሳነ ምድር ታሪክና ባህል ለመረዳት የሚሞክር
አንደሉስ → የዛሬዋ ስፔን‼ ================ (በአውሮፓ እምብርት ያበራችው የኢስላም ፀሐይ እና የጠፋችው ውብ ገፅታ!) || ✍️ «የአይቤሪያን ልሳነ ምድር ታሪክና ባህል ለመረዳት የሚሞክር ማንም ሰው፣ ያንን 'አስደናቂ የሆነውን ኢስላማዊ ትሩፋት' ከግምት ውስጥ ሳያስገባ ማለፍ አይችልም!» - (ሪቻርድ ፍሌቸር፣ 'ኢስላማዊቷ ስፔን' በተሰኘው መጽሐፉ) 🖊 ዛሬ ስፔን እና ፖርቱጋል ብለን የምንጠራቸው ሀገራት፣ ከአንድ ሺህ ዓመታት በፊት በአውሮፓ የጨለማ ዘመን (Dark Ages) ውስጥ ብቸኛዋ የበራች የብርሃን ደሴት ነበሩ። ስሟ "አንደሉስ" (Al-Andalus) ይባላል። ይህች ምድር ከ711 እ.ኤ.አ እስከ 1492 እ.ኤ.አ ለስምንት መቶ ዓመታት በእስልምና አስተዳደር ስር የነበረች፣ ዓለም ያየቻት እጅግ ስልጡን፣ የሳይንስ፣ የፍትሕ እና የመቻቻል ማማ ነበረች። እስኪ የዚችን የጠፋችና የተረሳች ታሪከኛ ምድር የተወሰኑ ገጽታዎች እንቃኝ፦ 1⃣ ታሪካዊው መግቢያ፡ የጧሪቅ ኢብኑ ዚያድ ድል! ⚔️፦ 🎀 በ711 እ.ኤ.አ ታላቁ የኡመውያ ኸሊፋ አል-ወሊድ ኢብኑ ዐብዱልመሊክ ባዘዘው መሠረት፣ ጀግናው የጦር አዛዥ ጧሪቅ ኢብኑ ዚያድ 7,000 የሚጠጉ ወታደሮቹን ይዞ ወደ አይቤሪያ ልሳነ-ምድር ተሻገረ። ያ ተሻግሮ ያረፈበት ትልቅ ተራራ እስከ ዛሬ ድረስ በስሙ "ጀበለ-ጥ'ጧሪቅ" (Gibraltar) ተብሎ ይጠራል። 🖊 በዚያን ጊዜ ስፔንን ይገዛ የነበረው ጨቋኙ የቪዚጎዝ (Visigothic) ንጉስ ሮደሪክ (Roderic) ነበር። ጧሪቅ ኢብኑ ዚያድ በጓዳሌት ጦርነት (Battle of Guadalete) የሮደሪክን ግዙፍ ጦር ድል በማድረግ፣ አብዛኛውን የስፔን እና የፖርቱጋል ክፍል፣ አልፎም እስከ ደቡብ ፈረንሳይ ድረስ በ7 ዓመታት ውስጥ በኢስላም ጥላ ስር አስገባ። ይህች ምድርም አንደሉስ ተብላ ተሰየመች። 2⃣  ቆርዶባ (Córdoba)፡ የዓለም የዕውቀት ማዕከል! 😀 🎀 አንደሉስ በተለይም በዐብዱ-ር'ረሕማን አድ-ዳኺል (Abd al-Rahman I) እና በኡመውያ ኸሊፋዎች ዘመን፣ የዓለም የዕውቀት፣ የሥልጣኔ እና የንግድ ማዕከል ሆነች። ዋና ከተማዋ ቆርዶባ (قرطبة) በዚያ የጨለማ ዘመን የአውሮፓ ትልቋ ከተማ ነበረች።   ✅  ከ100,000 በላይ ነዋሪዎች ነበሯት። ✅ መንገዶቿ በሌሊት በመብራት (Oil lanterns) ያበሩ ነበር (በዚያን ጊዜ ለንደን እና ፓሪስ በጭቃ እና በጨለማ የተዋጡ ነበሩ)።   ✅ በከተማዋ 70 ግዙፍ ቤተ-መጻሕፍት፣ 700 መስጂዶች፣ እና 3,000 የሕዝብ መታጠቢያዎች ነበሩ።   ✅ ዛሬም ድረስ በአርክቴክቸር ድንቅነቱ የሚነገርለት የቆርዶባ ታላቁ መስጂድ (Mosque-Cathedral of Córdoba) የዚህ ዘመን ትሩፋት ነው። 3⃣ የሳይንስ እና የሕክምና ወርቃማ ዘመን 🔬 🎀 ዛሬ አውሮፓውያን ለደረሱበት የሳይንስ እና የሕዳሴ (Renaissance) ከፍታ፣ መሠረቱን የጣሉት የአንደሉስ ሙስሊም ምሁራን ናቸው። ✅ ሕክምና፡ ➡️ አቡ አል-ቃሲም አል-ዘህራዊ የተባለው ሙስሊም ሊቅ፣ ዘመናዊ የቀዶ ጥገና (Surgery) አባት ይባላል። ዛሬ የምንጠቀምባቸውን 200 የሰርጀሪ እቃዎች የፈጠረው እርሱ ነው።   ✅ አስትሮኖሚና ሒሳብ፡ ➡️ አል-ዘርቃሊ (Al-Zarqali)፣ የኮፐርኒከስን ሥራዎች ያስቀደመ ታላቅ የአስትሮኖሚ ሊቅ ነበር። ከ0-9 ያሉት ቁጥሮች (Arabic numerals) ወደ አውሮፓ የገቡት በዚችው በአንደሉስ በኩል ነው።   ✅ ግብርና (Agronomy)፡ ➡️ ሙስሊሞች ዘመናዊ የመስኖ ስርአት (Irrigation)፣ ሸንኮራ አገዳ፣ ሎሚ፣ ሩዝ፣ እና ሮማን (Pomegranate) የመሳሰሉትን ፍራፍሬዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አውሮፓ ያስተዋወቁት በአንደሉስ ነበር። 4⃣ ፍትህ፣ አብሮነት እና መቻቻል (La Convivencia) 🕊️ 🎀 በአንደሉስ ዘመን ሙስሊሞች፣ አይሁዶች እና ክርስቲያኖች በአንድነት በሰላም የኖሩበት "ወርቃማው የአብሮነት ዘመን" ነበር። ክርስቲያኖችና አይሁዶች የራሳቸውን ኃይማኖት በነፃነት መተግበር ብቻ ሳይሆን፣ በመንግስት ውስጥ ትልልቅ የሥልጣን ቦታዎች (አምባሳደር፣ ሐኪም፣ ሚኒስትር) ነበሯቸው። በተለይም አይሁዶች በአውሮፓ ይደርስባቸው ከነበረው ጭፍጨፋ ሸሽተው ሰላም ያገኙት በኢስላማዊቷ ስፔን (አንደሉስ) ውስጥ ነበር። ይህ ዘመን በታሪክ "Golden age of Jewish culture" ተብሎ ይጠራል። ዛሬ ግን እነርሱ ታሪካቸውን ረስተው ፍልስጤምን ወረዋል። 5⃣ የአንደሉስ ብርሃን መጥፋት፡ የውድቀት መጀመሪያ (Reconquista) 💔፦ 🎀 ከጥንካሬዋ በኋላ አንደሉስ መዳከም ጀመረች። ምክንያቱ ደግሞ የውጭ ጠላት ሳይሆን፣ የሙስሊሙ የውስጥ ሽኩቻ እና መከፋፈል (Taifas/የአናሳ መንግስታት ዘመን) መምጣቱ ነበር። በ1031 እ.ኤ.አ የቆርዶባ ኸሊፋነት ሲፈርስ፣ አንደሉስ ወደ ትናንሽ እና እርስበርስ ወደሚዋጉ የሙስሊም ግዛቶች ተከፋፈለች። ✒️ ይህንን የሙስሊሙን መከፋፈል የተጠቀሙት የሰሜን ክርስቲያን መንግስታት (ካስቲል፣ አራጎን፣ ሊዮን) በጋራ በመሆን የሪኮንኪስታ (Reconquista - ዳግም የማስመለስ) ጦርነት ጀመሩ። መጀመሪያ ቶሌዶን (1085)፣ ከዚያም ቆርዶባን (1236) እና ሲቪልን (1248) ተቆጣጠሩ። ✒️ የመጨረሻዋ ምሽግ መውደቅ፡ ግራናዳ (1492) 💾  የመጨረሻዋ የሙስሊሞች ምሽግ የነበረችው ግራናዳ (Granada)፣ ለ250 ዓመታት ታግላ፣ በመጨረሻ ጃንዋሪ 1 ቀን 1492 እ.ኤ.አ በንጉስ ፈርዲናንድ እና ንግስት ኢዛቤላ ጦር ተከበበች። የአንደሉስ የመጨረሻው ሙስሊም መሪ (አቡ ዐብደልሏህ)፣ ያንን ድንቅ የሆነውን የአልሐምብራ ቤተመንግስት (Alhambra Palace) ቁልፍ አስረክቦ፣ ከከተማዋ ሲወጣ፣ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ያኔ እናቱ «እንደ ወንድ ተዋግተህ ማቆየት ያቃተህን ሀገር፣ እንደ ሴት አታልቅስላት» ብላዋለች ይባላል። ✒️ ከዚያ በኋላ ስፔንን የተቆጣጠሩት ካቶሊኮች፣ በሙስሊሞች እና አይሁዶች ላይ ታይቶ የማይታወቅ የዘር ማጥፋት (Inquisition) አወጁ። «ወይ ወደ ክርስትና ግቡ፣ ወይ ሀገር ለቃችሁ ውጡ፣ አለበለዚያ ትገደላላችሁ» የሚል አዋጅ ወጣ። በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሙስሊም መጽሐፍት በአደባባይ ተቃጠሉ፤ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች (ሞሪስኮስ በመባል የሚታወቁት) ተገድለዋል፤ ከፊሎችም ወደ ሞሮኮ እና አልጄሪያ ተሰደዋል። ⏰ አንደሉስ ዛሬ በካርታ ላይ የለችም። ነገር ግን የተዋበው አርክቴክቸሯ፣ ያስተማረችው የሳይንስ ብርሃን እና የፍትህ ታሪኳ መቼም አይረሳም። የሙስሊሙን ኡማ ትልቅነትም ሆነ መከፋፈል፣ ምን አይነት ውርደትና ውድቀት እንደሚያመጣ የምታስተምር ሕያው የታሪክ መጽሐፍ ናት! ታሪክን እንማር፤ ከስህተታችንም እንንቃ! #HistoryOfIslam #AlAndalus #IslamicSpain #GoldenAge #Cordoba #MuslimHistory #EthiopianMuslims (ይህን ማራኪ ታሪካዊ ጽሑፍ ሼር በማድረግ፣ እኛ ሙስሊሞች ምን አይነት የከፍታ ታሪክ እንደነበረን ለትውልዱ እናስታውስ!) || t.me/MuradTadesse