HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Відкрити в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Показати більше2 282
Підписники
+224 години
+37 днів
+2530 день
Архів дописів
በመምህር ተስፋዬና በመጋቢ ሐዲስ እሼቱ መካከል የተፈጠረው ምንድነው?? ብዙ ባልና ምስቶች በጸበል ተፋቷል የመጋቢ ሐዲስ ንግግር! #አጋንንት #መናፍስት #ጸሎት https://youtu.be/h792LhWyHN8
#ህዳር_12 በዓለ ሢመቱ #ለሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሚካኤል
"#ሚካኤል ሥዩም በዲበ ኃይላት፤ በኃይላት ላይ የተሾምክ ሚካኤል› ሲል ቅዱስ ኤጲፋንዮስ እንዳመሰገነው፤
- #ቅዱስ_ሚካኤል በኃይላት መላእክት ላይ የተሾመ ሊቀ መላእክት እንደመሆኑ በዓለ ሢመቱ ኅዳር ፲፪ ቀን በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ይከበራል፡፡ (መጽሐፈ አክሲማሮስ) ኃይላት የተባሉት መላእክትም ሰዎች በዓለም ፈተና ውስጥ ሆነው ሰይጣን ሊያደክማቸው ሲፈልግ ኃይልን ብርታትን የሚሰጡ፣ ይህን ዓለም ንቀው በበርሃ ወድቀው ከሥጋ ምኞት ጋር የሚጋደሉትን፣ በከተማም እየኖሩ መንፈሳዊ ትሩፋት የሚያደርጉትን ደግሞ የሚያበረቱ ናቸው፡፡
- ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ ‹እርሱም ወደ ሰማይ ያረገ እግዚአብሔርም ተቀምጦ ያለ መላእክትና ሥልጣናት ኃይላትም የተገዙለት ነው…› ሲል ‹ኃይላት› በማለት ያነሣቸው በኢዮር አራተኛይቷ ከተማ የሚኖሩትን ነው፡፡ በእነዚህ ላይ እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤልን አለቃቸው አድርጎ ሾሞታል፡፡ (፩ኛጴጥ.፫፥፳፪)
- #የቅዱስ_ሚካኤል ሢመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻም ግን አይደለም፤ የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይም ጭምር ነው፡፡ ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ትርጓሜ በዕብራይስጥ ‹‹እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው!›› ማለት እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠቅሳሉ፤ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ላይ እንዳሰፈሩት ደግሞ የስሙን ፊደላት በመተንተን እንዲህ ተርጉመውታል፤ ሚ-መኑ፣ ካ-ከመ፣ ኤል-አምላክ፤ ‹‹መኑ ከመ አምላክ፤ እንደ አምላክ ማን ነው!›› (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ)
- የሰማይ ሠራዊት ሁሉ አለቃቸው ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ ይህ ኃያል መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባሉትን እስራኤል ዘሥጋን ሲረዳና ሲጠብቅ እንደነበረ ተጽፎልን እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ በኢያሪኮ ምድረ በዳ እንደተገለጠለት ‹‹… ዐይኑን አንሥቶ ተመለከተ፤ እነሆም፥ የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ ሰው በፊቱ ቆሞ አየ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ፥ “ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ?” አለው፡፡ እርሱም “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ፤ አሁንም ወደ አንተ መጥቼአለሁ፡፡” ሲል ተናግሯል፡፡ (ኢያ.፭፥፲፫)
- እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ነፃ ሲያወጣቸው ይመራቸው የነበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ‹‹ በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ፥ ወዳዘጋጀሁልህም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ ፥እኔ መልአኬን በፊትህ እልካለሁ›› እንዲል፤ ሹመቱ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይም በመሆኑ ስለ እነርሱ ከእግዚአብሔር ምሕረትን ይለምንላቸው ነበር፡፡ (ዘፀአት.፳፫፥፳)
- ነገር ግን ኃጢአት ሲሠሩ እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን ይቀጣልና ሕዝቡን ‹‹ራስህን ጠብቅ፤ ስማው፤ እንቢም አትበለው፤ ስሜ በእርሱ ስለሆነ ይቅር አይልምና›› ብሎ አስጠንቅቋቸው ነበር፤ ይህም ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ መሾሙን ያስረዳናል፡፡ (ዘፀ.፳፫፥፳፩) ቅዱስ ገብርኤል በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ቅዱስ ሚካኤል ስለመሾሙ ሲመሰክር ‹‹በእውነት በመጽሐፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር የሚረዳኝ ማንም የለም›› ብሎአል፡፡ ስለዚህም ለኢያሱ የተገለጠውና እስራኤላውያንንም የመራው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን እንረዳለን፡፡ (ዳን.፲፥፳፩)
- የቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት በሐዲስ ኪዳንም እንደነበር ይህ ነቢይ በትንቢቱ ‹‹በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ ሚካኤል ይነሣል›› በማለት ተናግሮለታል፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ሚካኤል እኛን ከሰይጣን አሽክላና ወጥመድ ይጠብቀንና በጸሎቱ በእግዚአብሔር ፊት ይቆምልን ዘንድ በእኛም ላይ ሹም ነው፡፡ ምክንያቱም እኛ የእግዚአብሔር ሕዝቦችና የርስቱ ወራሾች ነንና፡፡ (ዳን.፲፪፥፩) በመጽሐፈ ስንክሳርም ተመዝግቦ እንደምናኘው ቅዱስ ሚካኤል በየወሩ በዐሥራ ሁለት ቀን ለመታሰቢያው በዓል ተሠርቶለታል፤ እርሱ ስለ እኛ የምድሩን ፍሬ ይባርክልን ዘንድ ዝናሙም በጊዜው እንዲወርድልን የወንዙንም ውኃ እንዲመላልን ነፋሱንም የምሕረት ነፋስ እንዲያደርግልን ሁሉንም የተስተካከለ እንዲያደርግልን ወደ እግዚአብሔር በጸሎት ይማልዳልና፡፡ (ስንክሳር ኅዳር ፲፪)
- ስለሆነም በኃጢአት ባርነት ተይዘን በችግር እና በመከራ ውስጥ ተዘፍቀን ለምንኖር ሰዎች ስለ ሕዝበ እስራኤል በእግዚአብሔር ፊት የቆመው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ለእኛም ያማልደንና ተራዳኢ ይሆነን ዘንድ በጸሎት እንማጸነው። አምላካችን እግዚአብሔርም የምሕረት ፊቱን ወደ እኛ በመመለስ በጸብና በጦርነት ምትክ ፍቅርን፣ ሰላምንና መግባባትን፤ በመለያየት ምትክ አንድነትን እንዲሰጠን በቅዱስ ሚካኤል ስም እንለምን።
#የሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሚካኤል
አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን፡፡
/ መጽሐፈ ዘኅዳር 12 : መጽሐፈ አክሲማሮስ /
#ኅዳር_11
#ቅድስት_ሐና
ኅዳር ዐሥራ አንድ በዚች ዕለት አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እናቷ የሆነች የተመሰገነች የቅድስት ሐና የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው።
ይችም ቅድስት ከኢየሩሳሌም አገር ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሜልኪ ልጅ ለሆነ ለማጣት ልጁ ናት። ለማጣትም ሦስት ሴቶች ልጆች አሉት የታላቂቱም ስሟ ማርያም ናት ሁለተኛዋም ስሟ ሶፍያ ሦስተኛዪቱም ስሟ ሐና ናት ታላቂቱ ማርያምም ለባል ተድራ አዋላጅ የሆነች ሰሎሜን ወለደቻት እርሷም መድኃኒታችንን ከወለደችበት ጊዜ ጀምሮ በስደቷም ወራት ከአረጋዊ ዮሴፍ ጋር እመቤታችንን ድንግል ማርያምን ያገለገለቻት ናት።
ሶፍያም ለባል ተድራ ለመጥመቁ ዮሐንስ እናቱ የሆነች ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደቻት። ይችንም ቅድስት ሐናን ከይሁዳ ነገድ ለሆነ ጻድቅ ስሙ ኢያቄም ለሚባል አጋቧትና እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደቻት እሊህም ሰሎሜና ኤልሳቤጥ ለቅድስት ሐና የእኅትማማች ልጆች ናቸው።
የዚችንም የቅድስት ሐናን በሥውር የምትሠራውን ገድሏንና ትሩፋቷን እንዳናስታውሰው አናውቀውም ግን ከሴቶች ሁሉ እንደምትበልጥና እንደምትከብር እናውቃለን እንረዳለን እርሷ አምላክን በሥጋ ለወለደችው ወላጅዋ ትሆን ዘንድ የተገባት ሁናለችና ከሴቶች ሁሉ የሚበልጥና የሚበዛ ትሩፋትና ተጋድሎ ባይኖራት ይህ ታላቅ ጸጋ ባልተገባት ነበር።
ይህችም ጻድቅት ሐና መካን በመሆንዋ ልጅን ይሰጣት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር በጸሎት ትማልድ ነበር እግዚአብሔርም በእርሷ ለዓለም ሁሉ ድኅነት የተደረገባትን ይቺን የተባረከችና የከበረች ልጅን ሰጣት እርሷም አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት።
ስለዚህም ይህን ታላቅ ጸጋ ስለሰጣት የበዓሏን መታሰቢያ በደስታ ልናከብር ይገባናል።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በጸሎቷ የሚገኝ በረከቷም ከእኛ ጋር ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ኅዳር)
ለንስሐ አባቴ ሳልናዘዝ ቅዱስ ቁርባን ተቀበልኩ የተፈጠረውን ተመልከቱ!! የሰላቢ መንፈስና የሆቴሎቻችን ጉድ! 3 ሚሊዮን ብር በመተት የተቀማው ወጣትና መከራው! https://youtu.be/r_wogRLw57A
😡 ዝም ብትልም ያፈናቅሉሀል ንብረትህን ያወድሙብሀል በመጨረሻም እንደ አርሲ ምዕመናን ጨፍጭፈው ይገድሉሀል። ዲያቆን ዮሴፍ ፍሥሓን ማሰርም ለኦርቶዶክሳዊያን ከተደገሰው የመከራ ትሩፋት አንዱ ነው። እንደ ዲያቆን ዮሴፍ ነቅተህ ፍትህ ስትጠይቅም ያፍኑሀል ያስሩሀል ድራሽህን ያጠፉሀል። ምክንያቱም ኦርቶዶክስን ማዳከም ማመንመን ማፅዳት ማጥፋት ቋሚ ተረክ ያለው ፕሮጀክት ስለሆነ ነው። ከሆነውና እየሆነ ካለው ይልቅ ሊሆን ያለው በብዙ እጥፍ አደ,ገኛ አስፈ,ሪ እና ጅምላ ጨራ,ሽ ነው። ዛሬ የተሻለ ካልሰራን ዛሬን የሚያስናፍቅ መከ,ራ ከፊታችን ላይ አለ። መፍትሄው አንድ ልብ ሆኖ ለእውነት መቆም አስተማማኝ ፍትህን መፈለግ ብቻ ነው። (የኔታ ገብረ መድህን እንየው) ዲያቆን ዮሴፍ ከስራ ቦታ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተወስዷል። ያለበት ቦታም አልታወቀም። በምስራቅ አርሲ በኦርቶዶክሳዊያን ላይ በተደረገው ግፍ ጠንከር ያለ ትችት ሲያቀርብ ቆይቶ ነበር።
ወላጆች ሴት ልጆቻችሁን ጠብቁ ዘመኑ እጅግ ከፍቷል ይኼንን ተመልከቱ!! መላቀቅ ያልቻልነው የዝሙት መንፈስ ፈተናዎች! መንፈሳዊነት ከማንነት ጋር ሲጣመር! #ንቁ https://youtu.be/S9jbIrUo9fY
ኅዳር ፲ /10/
በዚች ቀን ቅዱሳት ንጹሐት መነኰሳይያት ደናግል እናታቸው ሶፍያም በሰማዕትነት አረፉ።
እኚህም ቅዱሳት ከተለያዩ አገሮችና ቦታዎች ሲሆኑ መለኮታዊ ፍቅር በአንድነት ሰበሰባቸው የምንኲስናንም ልብስ ለበሱ ይኸውም የመላእክት ልብስ ነው። በሮሜ አገር ከአሉ ገዳማትም በአንዱ የሚኖሩ ሆኑ ቅድስት ሶፍያም በእነርሱ ላይ እመ ምኔት ሆነች። እርሷም ጸጋንና ዕውቀትን የተመላች ናት የቅዱሳን መነኰሳትን ገድል በማንበብ እየጾሙ እየጸለዩ በምድር ላይ እንደ መላእክት እስከ ሆኑ ድረስ መንፈሳዊ ዕድገትን አሳደገቻቸው ከእነርሱም በአንድ ገዳም ውስጥ ሰባ ዓመት ያህል የኖሩ አሉ ከውስጣቸውም ልጅ እግሮች የሆኑ አሉ።
ከሀዲ ንጉሥ ዑልያኖስም ከፋርስ ንጉሥ ከሳቦር ጋር ሊዋጋ በሮሀ ሀገር በኩል በሚያልፍ ጊዜ እርሱ ሳቦር ሊወጋው ወደርሱ እንደሚመጣ ሰምቷልና አልፎ ሲሔድም በውስጡ እሊህ ደናግል ያሉበትን ገዳም አይቶ ይህ ምንድን ነው ብሎ ጠየቀ ሰዎችም ይህ የደናግሎች ገዳም ነው አሉት። በዚያንም ጊዜ ወደዚያ ገዳም ገብተው ደናግሎችን እንዲገድሏቸው በገዳሙ ውስጥም ያለ ገንዘባቸውን ሁሉ እንዲዘርፉ ወታደሮቹን አዘዘ ወታደሮችም ገብተው እሊያን ደናግል በሰይፍ ገደሏቸው ገዳሙንም አጠፉ የገዳሙን ገንዘብ ሁሉንም ዘረፉ።
ከሀዲውን ንጉሥ ግን ስለ መንጋዎቹ በቀል እግዚአብሔር ተበቀለው ይህም እንዲህ ነው ያጠፋው ዘንድ ሰማዕት መርቆሬዎስን አዘዘው መርቆሬዎስም በአካለ ነፍስ ሒዶ በጦር ወጋውና በክፉ አሟሟት ሙቶ ወደ ዘላለም ሥቃይ ሔደ። እሊህ ቅዱሳት ደናግል ግን ወደ ዘላለም ተድላ ደስታ ገቡ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
"We believe that our Lord, God and Saviour Jesus Christ, the Incarnate - Logos is perfect in His Divinity and perfect in His Humanity. He made His humanity One with His Divinity without Mixture, nor Mingling, nor Confusion. His Divinity was not separated from His Humanity even for a moment or twinkling of an eye. At the same time, we anathematize the Doctrines of both Nestorius and Eutyches".
ስንታረድ ስንገደል እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል?? ገዳማት በማዞር ዕድሜያችንን የሚጨርሱ ክፉ መናፍስትና ሴራቸው! በድመት ሥጋ የተደገመ መተት ያስከተለውጣጣ!
https://youtu.be/Cr1fsh1E8Nw
ስንታረድ ስንገደል እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል?? ገዳማት በማዞር ዕድሜያችንን የሚጨርሱ ክፉ መናፍስትና ሴራቸው! በድመት ሥጋ የተደገመ መተት ያስከተለውጣጣ! https://youtu.be/Cr1fsh1E8Nw
ኅዳር ፱ /9/
በዚች ዕለት ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ አንደኛ የእስክንድርያ አገር ሊቃ ጳጳሳት ቅዱስ አባት ይስሐቅ አረፈ።
ወላጆቹ ይህን ቅዱስ በወለዱት ጊዜ በታላቅ ደስታ ደስ ተሰኙበት። ያጠምቀው ዘንድ ወደ ኤጲስቆጶስ በአቀረቡት ጊዜ ሲያጠምቀው በሕፃኑ ራስ ላይ የብርሃን መስቀልን አየ። እንዲህም ብሎ ትንቢት ተናገረለት ይህ ሕፃን በእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሾማል እርሱ ለእግዚአብሔር የተመረጠ መሣሪያ ይሆናልና። የቤተ ክርስቲያንን ትምህርትና ጽሕፈትን አስተማሩት ወላጆቹንም ትቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ በአበምኔቱ በአባ ዘካርያስም ዘንድ መንኩሶ በገድል ተጠመደ።
በአንዲትም ዕለት አንድ ጻድቅ ሰው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አየው በእርሱም ላይ ይስሐቅ በክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሾም ዘንድ አለው ብሎ ትንቢት ተናገረ። ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሐንስ ጸሐፊ የሚሆነውና የሚረዳው ብልህ ሰው ፈለገ ስለ አባ ይስሐቅም ነገሩት እሱንም አስመጣው ይጽፍለትም ዘንድ ደብዳቤ ሰጠው እርሱ ግን አባ ይስሐቅ እያወቀ ጽሕፈቱን አበላሽ ሊቀ ጳጳሳቱ እንዲተወውና ወደ አስቄጥስ ገዳም እንዲመለስ ነበር የዚህን ዓለም ክብር ይጠላልና።
ሊቀ ጳጳሳቱም እንዲተወውና እንዲአሰናብተው አውቆ ማበላሸቱን በአወቀ ጊዜ በጥሩ ጽፈሃል እንድትሔድም እኔ አልተውህም አለው ከወራትም በኋላ አባ ይስሐቅ ወደ አስቄጥስ ገዳም ተመለሰ አባ ዮሐንስም የሚያርፍበት ቀን በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔርን በራእይ ከአንተ በኋላ ለዚች ሹመት የሚጠቅም ረዳትህ ይስሐቅ ነው አለው። አባ ዮሐንስ በአረፈ ጊዜ ይህን ቅዱስ አባት ይስሐቅን ይዘው በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ :- መጽሐፈ ስንክሳር
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@walkinaddistv
#_ታላቅ_የንግስ_በዓል_እና_የዝክር_በረከት_ጥሪ!
#_በንቡ_ቅዱስ_ሚካኤል_ቤተ_ክርስቲያን!
ሼር በማድረግ ለቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች አዳርሱ!
የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች የፊታችን አርብ ህዳር 12 ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ታላቅ ክብረ በዓሉ ነው። ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል አርብ ህዳር 12 በተአምረኛው በንቡ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ይከብራል።
በእለቱም ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ሕዝቡን ይባርካል። ታቦተ ሕጉ ወደ መንበረ ክብሩ ከተመለሰ በኋላ፣ ከቅዳሴ መልስ ተአምረኛውና ብዙ ሰው የተፈወሰበት የቅዱስ ሚካኤል ማር ይታደላል፣ የቅዱስ ሚካኤል የዝክር በረከትም በሰፊው ይዘከራል።
ስለዚህ ህዳር 12 አርብ ተአምረኛው ንቡ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን መጥታችሁ ቅዱስ ሚካኤል እንድታከብሩ እንዲሁም የቅዱስ ሚካኤልን የዝክር በረከት እንድትቀምሱ፣ ተአምረኛውን ማር እንድትቋደሱ ቤተ ክርስቲያኗ ጥሪዋን ታስተላልፋለች!
#_አድራሻ :-
መገናኛ ከመጣችሁ በኋላ በቦሌ አራብሳ ታክሲ ተሳፍራችሁ ንቡ ሚካኤል አደባባይ ጋር ወርዳችሁ አጠገቡ ቤተ ክርስቲያኑ ይገኛል። ወይም አያት ሰንሻይን አፓርታማ ዝቅ ብሎ ይገኛል!
ከየትኛውም አቅጣጫ በመኪና እና በራይድ የምትመጡ አያት ሰንሻይን አፖርታማ ዝቅ ስትሉ ንቡ ሚካኤል አደባባይ አለ አጠገቡ ቤተ ክርስቲያኑ ይገኛል!
ቅዱስ ሚካኤል በእለተ ቀኑ በደጁ ለበረከት ያገናኘን!
ህዳር 8-3-2018 ዓ.ም
አዲስ ዝማሬ ''የፈቀድከው ይሁን'' #Hersolan#HeranandMenfesawi https://youtu.be/04gO-b0gyLI?list=RD04gO-b0gyLI
3ቱ ሁላችንም ማወቅ የሚገባን የአይነጥላ ክፉ መንፈስ ልዩ ልዩ ባሕሪና መገለጫዎች!! የአይነጥላ መንፈስን ለማሸነፍ እንዴት እንጸልይ? #አጋንንት #መናፍስት https://youtu.be/r2nGdmIWxo0
