HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Ir al canal en Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Mostrar más2 273
Suscriptores
+224 horas
+177 días
+2930 días
Archivo de publicaciones
መንፈሳዊ ተስፋ እንዳይኖረን ዲያብሎስ አጥብቆ የሚዋጋን በዚህ መንገድ ነው!! ተገፊቼ ሃይማኖተን ቀየርኩ የምትሉ ይኼንን አዳምጡ! እግዚአብሔርን ማጣት እንዴት? https://youtu.be/LVXy5zTtCZM
"በአንደበትህ ላይ መዝጊያን ያላደረግህ እንደሆነ፣ የነፍስህን መዝገብ ሁሉ ትበትነዋለህ። አንደበት ከትንሽ የእሳት ብልጭታ እንደሚነሳ ትልቅ ቃጠሎ ነው። ከመጠን ያለፈ ንግግር፣ ከንቱ ውይይት፣ ወይም የሌላውን ሰው ስህተት መዘርዘር የውስጥ ሰላምን ያጠፋል፤ ጸጋን ያርቃል፤ ለሰይጣንም መግቢያ በር ይከፍታል። ዝምታን ከሁሉ በላይ ውደድ። በዝምታህ ውስጥ የአንተንና የእግዚአብሔርን ድምፅ ብቻ ትሰማለህ። በመናገር ፈንታ ጸልይ።"
- አባ ጳውሎስ (Abba Paul) እና የበርሃው አባቶች አስተምህሮ መሠረት።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
"የትዕግስትን ካባ የለበሰ፣ የሰይጣንን ፍላፃ ሁሉ መክቷል ማለት ነው። ቅዱስ ባስልዮስ እንዳሉት ቁጣ የክርስቶስን መገኘት ከልብ ያርቃል። ትዕግስት ደግሞ ቁጣን የምንዋጋበት ዋናው መሳሪያ ነው። ሰው ሲሳደብህ ወይም ሲበድልህ ወዲያውኑ ምላሽ ለመስጠት አትቸኩል። ዝምታን ይዘህ ታገስ። ለክርስቶስ ስትል ስትታገስ፣ የጸጋ በረከትና መንፈሳዊ ዕድገት ታገኛለህ። ትዕግስት የፍቅር እና የሰላም መገለጫ ነው።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (St. John Chrysostom) በትዕግስት ላይ የሰጠው ትምህርት።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
*** የነፍስህን ደጅ ካልጠበቅህ፣ ምንም እንኳ በውጭ ብትጸልይም በውስጥህ ዘራፊ (ሰይጣን) ይበረብርሃል። በየሰዓቱ የምታስበውን፣ የምትናገረውንና የምትሠራውን ነገር ፈትሽ። ንቃት (watchfulness) ማለት መንፈሳዊ እንቅልፍን አስወግዶ ሁልጊዜ ለክርስቶስ መምጣት ተዘጋጅቶ መኖር ማለት ነው። ንቃት በዋነኝነት የሚገኘው ያለማቋረጥ "ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፣ ማረኝ" እያሉ መጸለይን በመለማመድ ነው። ይህ ጸሎት ልብህን እንደ ቅጥር ይጠብቀዋል።
ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ (St. Isaac the Syrian) እና የሄሲካዝም (Hesychasm) ትምህርት
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
ሕዳር ፫ /3/ በዚችም ቀን አባ አትናቴዎስና እኅቱ ኢራኢ አረፉ ። እሊህንም ቅዱሳን ከሀዲ ንጉሥ መክስምያኖስ ጽኑዕ የሆነ ሥቃይን አሠቃያቸው ። በማሠቃየትም በደከመ ጊዜ ዕራቁታቸውን ከጉድጓድ ጨመራቸው በላያቸውም የጒድጓዱን አፍ ዘጋ በውስጧም ነፍሳቸውን አሳለፉ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@iam_haile
ቅዱስ ሚካኤል ይባርከን! ለዓመታዊ ክብረ በዓል የዝክር ተሳትፎ ጥሪ
የዓለማት ሁሉ ጌታ ስሙ የተመሰገነ ይሁን! ውድ ቤተሰቦቼና ወዳጆቼ፣ እንደምን ሰነበታችሁ?
ልዑለ ቃል፣ ሐያልና ዓቃቤያችን የኾነው የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል ደርሷል። በየዓመቱ እንደምናደርገው፣ በዚህ ታላቅ የበዓል ዝግጅት እና ዝክር ሥራ ተሳትፈን የበረከቱን ተካፋይ እንድንሆን በፍቅር እንጠይቃችኋለን።
ይህን መንፈሳዊ አገልግሎት ለመደገፍና የበረከት ሩጫውን ለመሮጥ፦
- በገንዘብ (ለቁሳቁስና ለዝግጅት ግዥ)
- በጉልበት (ሥራውን በማገዝ)
- በቁሳቁስ (ለዝክር በሚውሉ ነገሮች)
አቅማችሁ በፈቀደው መንገድ ሁሉ ልትሳተፉ ትችላላችሁ። ለመሳተፍና ለዝርዝር መረጃ፣ እባክዎ በውስጥ መስመር ያነጋግሩን።
- በስልክ ቁጥር፦ 0945957646
- በቴሌግራም (ውስጥ መስመር): https://t.me/haile_gebriel_tube_bot
ልዑል እግዚአብሔር የቅዱስ ሚካኤልን በረከት ያድለን!
እግራችሁን የሚያሳክክና ደም እንድወጣችሁ የሚያደርገው የቡዳ አጋንንት ክፋትና ተንኮል!! ሰው እንዴት ዳን ተፈወስ እየተባለ ይለመናል!! #አጋንንት #መናፍስት https://youtu.be/Pn2_au62CoA
ልዩ ፍርድ ቤት (በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
- የብዙዎቻችን ከንፈሮች ለሐሜት የተከፈቱ ናቸው፡፡ የራሳችንን ግንድ ትተንም ከሰዎች ጉድፍን ለማውጣት እንዳዳለን። በወንድሞቻችንም ላይ እንፈርዳለን፡፡ ተወዳጆች ሆይ! እንጠንቀቅ! የፍርድ ዙፋን ያለው ከእርሱ ጋር ብቻ ነውና የወልድን ሥልጣን እኛው አንያዘው፡፡ መፍረድ ትፈልጋላችሁን? እንግዲያስ ምንም የማያስወቅስና በጣም ብዙ ጥቅም ያለው የፍርድ ችሎት አለላችሁ፡፡ አጥብቃችሁ በራሳችሁ ላይ ለመፍረድ ተቀመጡ፡፡ አስቀድማችሁ በደላችሁን ከፊታችሁ በመዝገብ አስቀምጡት፤ የነፍሳችሁም ወንጀል በሙሉ መርምሩ፤ ተገቢውንም ፍርድ አስቀምጡና ነፍሳችሁን “ይህንና ያንን በደል ያደረግሺው ስለምንድነው?” በሏት፡፡ ከዚህ ፈቀቅ ብላ የሌሎችን ሰዎች ኃጢአት መፈለግ ከጀመረች “የተከሰስሽበት ጉዳይ የእነዚያ አይደለም፣ አንቺም የመጣሽው ስለነዚያ ሰዎች ለመሟገት አይደለም፡፡ ስለምንድነው ክፋትን የሠራሽው? ስለምንስ ነው ያንንና ይህን ጥፋት ያጠፋሽው? የራስሽን ተናገሪ እንጂ ሌሎችን አትውቀሺ” በሏት፡፡ ሁል ጊዜም ይህን አስጨናቂ ፈተናን እንድትመልስ አቻኩሏት፡፡ ተሸማቅቃ ምንም የምትመልሰው ነገር ከሌላትም አስፈላጊውን ቅጣት (ቀኖና) ወሱንባት፡፡ ይህን ልዩ ፍርድቤት ሁል ጊዜ የምትቀመጡ ከሆነ የእሳት ሸሎቆው፣ መርዘኛው ትልና ሊመጣ ያለውን ስቃይ በአእምሮዋችሁ እንዲቀረፅ ይረዳችኋል፡፡
- ሁልጊዜም “እሱ ወደ እኔ መጥቶብኝ ነው፤ እሱ ሸውዶኝ ነው፤ እሱ ፈትኖኝ ነው” እያለች ከዲያብሎስ ጐን እንድትሰለፍና ሐፍረት የለሽ ንግግሮችን እንድትናገር አትፍቀዱላት፡፡ ይልቁንም “አንቺ ፍቃደኛ ባትሆኚ ነው እንጂ እነዚህ ሁሉ ካንቺ ጋራ ምንም ጉዳይ የላቸውም” ብላችሁ ንገሯት፡፡ “እኔ እኮ ሥጋ ለባሽ ነኝ፣ የምኖረውም በምድር ነው” ካለቻችሁም “ይህ ሁሉ ሰበብና ምክንያት ነው፡፡ ብዙዎች አንቺ የለበስሽውን ሥጋ ለብሰው በዚህች ምድር ኑረው ጻድቃንና ሰማዕታት ሆነዋል። አንቺ ራስሽ አንዳንድ ጊዜ መልካም ስታደርጊ ይኸን የምታስቢበት ሥጋ ይዘሽ ነው” በሏት፡፡ ይህን ሁሉ ስትሏት በጣም ካመማት እጃችሁን አታንሱባት፡፡ ምክንያቱም (በቀኖና) ስትቀጧት ከሞት ታድኗታላችሁ እንጂ አትገድሏትም፡፡ ምክንያት የምታበዛባችሁ ከሆነም “እባብ አሳተኝ” ብላ ከተጠያቂነትና ከፍርድ ያላመለጠችውን የመጀመርያዋን ሴት እንድታስተውስ ንገሯት፡፡
- ይህን ሁሉ ስታደርጉ ከአጠገባችሁ ማንም አይኑር፤ ማንምም የሚረብሻችሁ አይሁን፡፡ ይልቁንም ዳኛ በፍርድ ወንበር ላይ እንደሚቀመጥ እናንተም በፍርድ ወንበር ፈንታ በምቹ ጊዜና ቦታ በጽሞና ተቀመጡ፡፡ እራት ከበላችሁ በኋላና ወደ መኝታ ክፍላችሁ ስትሄዱ ይህን የፍርድ ወንበር ይዛችሁት ሂዱ፡፡ ነቢዩም፡- “በመኝታችሁ ሳላችሁ በልባችሁ የምታስቡት ይታወቃችሁ” /መዝ.4፥4/ እንዳለው ይህ ቦታና ጊዜ ከሁሉም በላይ ተስማሚ ነውና፡፡ ይህን ዕለት ዕለት የምታደርጉ ከሆነ በዚያ በአስፈሪው የፍርድ ወንበር ያለፍርሐት ትቆማላችሁ፡፡
- ሐዋርያው “እኛ በራሳችን ብንፈርድ ኖሮ ባልተፈረደብም ነበር” እንዲል /1ቆሮ.11፥31/። ይህን ሁሉ እንድናደርግ ሰውን በመውደድ ሰው የሆነው ክርስቶስ ይርዳን አሜን!!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.facebook.com/hailegebrieltube2021
https://www.tiktok.com/@iam_haile
"ሰዎች የፈጸሙብንን ክፉ ነገር የምናስብ ከሆነ፣ እግዚአብሔርን ለማሰብ የምንችልበትን ኃይል እናጣለን። ነገር ግን የአጋንንትን ክፉ ሥራ ዘወትር የምናስብ ከሆነ ጽኑዐን እንሆናለን።”
(አባ መቃርስ)
ክፋትን ከአንተ አርቃት
«ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ ውስጥ ያለ መሆን አለመሆኑን ያውቃል፡፡ ይኸውም ስትቆጣ ወይም ስትጮህ ወይም የማይረቡ ከንቱ ነገሮችን ስትናገር ሲያይህ ጠላት በአንተ ዘንድ እግዚአብሔር እንደሌለ ያውቃል ያን ጊዜ በውስጥህም በውጭህም ያለውን ሳይቀር ይገዛል፤ መዝጊያ እንደሌለው ቤት እንደ ክፉ ሌባ ይገባና ውስጥህን ይበረብረዋል፡፡"»
ቅዱስ ባስልዮስ
ያሳዝናል!! በቅኔ መምህሩ ተደግሞ የገባ የአፍልሆ ድግምት ያስከተለው መዘዝ! የከበሮ መተት እንዳለ ስንቶች ታውቃላችሁ! የአብር አንክርት መንፈስና መዘዙ!! https://youtu.be/OqHcvpY7yoU
ክፉ መናፍስት ሲዳከሙ የምታዩ ምልክቶች! https://youtu.be/57DswcXvb3A?si=7ToB2XYEHsYwfO8r
የአምልኮትና የክብር ስግደትን በመልካ መልኮች እንዴት እንስገድ? #ስግደት #መልክአ_ማሪያም #መልክአ_ኢየሱስ
https://youtu.be/MU-DySX9nhk?si=iIIe66B8o30k7lat
መናፍስት እንዳያዩንና የተባረከ ልጅ ለመውለድ ይኼንን መንገድ ተጠቀሙ!! አራዳነት ክርስቶስን መያዝ ነው ስኬትም እሱ ነው!! ዘፍኜ የምኖር ነበር የመሰለኝ!! #Amleset #Muchie
https://youtu.be/NS5_EPTXWGQ?si=qTn1c-j528WlVsHI
ከአጋንንት ፈተናና ከችግሮቻችን ከተላቀቅን በኋላ ለምን እግዚአብሔርን እናሳዝናለን? ዲያቆን ሄኖክ ለበጋሻውና መሰሎቹ የሰጠው መልስ! መነኩሰው የገጠማቸው ፈተና https://youtu.be/0uYhcXuu9oM
ይኼንን የመቁጠሪያ አጠቃቀም ምስጥር ሁላችሁም ማወቅ ይገባችኋል!! ለዚህ ያበቁኝ መምህር ግርማ ናቸው!! እንዲህ ብላችሁ ሁላችሁም ጸልዩ!! https://youtu.be/FIVojHJLRsQ
** እግዚአብሔርን የሚፈሩት ሁሉ፥ በመንገዶቹም የሚሄዱ ምስጉኖች ናቸው። የድካምህንም ፍሬ ትመገባለህ፤ ምስጉን ነህ መልካምም ይሆንልሃል። ሚስትህ በቤትህ እልፍኝ ውስጥ እንደሚያፈራ ወይን ናት፤ ልጆችህ በማዕድህ ዙሪያ እንደ ወይራ ቡቃያ ናቸው። እነሆ፥ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው እንዲህ ይባረካል። እግዚአብሔር ከጽዮን ይባርክህ፤ በሕይወትህ ዘመን ሁሉ፥ የኢየሩሳሌምን መልካምነትዋን ታያለህ። የልጆችህንም ልጆች ታያለህ። በእስራኤል ላይ ሰላም ይሁን። (መዝሙር 128)
** እርሱ ደሙን አፍስሶልናል ስለዚህ ሌላ ደም መፍሰስ የለበትም!
** በክርስትናችን በሃይማኖታችን መገደላችን የሚቆመው መቼ ነው? ነፃነት እንፈልጋለን። የሰው ልጆች ደም በከንቱ መፍሰስ መቆም አለበት። ይኼ ፖለቲካ አይደለም። ሰላም መሻት፣ ዕረፍት መፈለግ፣ አንሙት ማለት ፖለቲካ ሳይሆን ሰብአዊ መብት ነው። ሰው መሆን ነው፤ ደከመን፤ ብዙ ጊዜ ሰማን። እናንተም በእኛ ፈረዳችሁብን፤ እናንተም ወቀሳችሁን፤ እውነት አላችሁ ግን ለማን ነው የምንነግረው ይኼንን? ማን ነው የሚሰማን ይኼንን? ማን ነው የሚያቆመው ይኼንን? ተለማመድነው እኮ። ስንቶቻችን ስናልቅ ነው የሚቆመው? ይብቃ። ሕዝባችን ዕረፍት ይፈልጋል። ሞት ሰለቸን በቃን፤ ደም መፍሰስ ሰለቸን፤ ይበቃናል፤ ምድሪቷ ዕረፍት ያስፈልጋታል፤ ሕዝቡ ዕረፍት ያስፈልገዋል፤ ስለ እኛ ደም ፈሰሰ እኮ፤ በእርሱ ቁስል ተፈወስን እኮ፤ ሌላ ደም አያስፈልግም። መከራችን እንዲያበቃ ጸልዩ"
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል
ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም የተናገሩት
የብፁዕነትዎ በረከት ይደርብን።
ጬሌን ከማቃጠላችሁና ከመጣላችሁ በፍት ይኼንን ማድረጋችሁን አትርሱ!! ሳትጸልይ የወለድከው ልጅ ባይታዘዝ አይገርምም!! ዕድላቸው በመተት የተያዘባቸው ቤተሰቦች! https://youtu.be/i8zTHpwNYvM
27 #መድኃኔዓለም
ምስጋና የሁል ጊዜ ተግባራቸው የሆነ ሰማያውያን መላእክት ምድራውያን ጻድቃን ሰማአታት ተመራምረው ለማይደርሱበት ለስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ ። /መልክአ መድኃኔዓለም/
እኛ ደግሞ አስቀድመን የማናስተውል ነበርንና፤ የማንታዘዝ፥ የምንስት፥ ለምኞትና ለልዩ ልዩ ተድላ እንደ ባሪያዎች የምንገዛ፥ በክፋትና በምቀኝነት የምንኖር፥ የምንጣላ፥
እርስ በርሳችን የምንጠላላ ነበርን።
ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥
እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤
ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን
በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው። ቲቶ 3 ፥ 3 - 7
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
