uk
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Відкрити в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Показати більше
2 273
Підписники
+224 години
+177 днів
+2930 день
Архів дописів
ሰይጣን ከተሸኜ በኋላ እንዳይመለስ ማድረግ የሚገቡን 10 ወሳኝ ነገሮች! በአስም በሽታ የምትሰቃዬ ይኼንን አዳምጡ!! ሰከፋን ወደ ክርስቶስ ስደላን ጭፈራ ቤት! https://youtu.be/wDI9DaiX_Lg?si=UnDDszn4nxMF4ErX

👉 የበረከት ሥራ ጥሪ! በመምህር ተስፋዬ ለሐሙስ የሚመቻችሁ በአካል በመገኘት በዚህ የበረከት ሥራ ሁላችሁም እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል። የሚመቻችሁ ጠዋትም አባታችን ቀሲስ ሄኖክ እንዲሁ እዛው መቀዶኒ
+1
👉 የበረከት ሥራ ጥሪ! በመምህር ተስፋዬ ለሐሙስ የሚመቻችሁ በአካል በመገኘት በዚህ የበረከት ሥራ ሁላችሁም እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል። የሚመቻችሁ ጠዋትም አባታችን ቀሲስ ሄኖክ እንዲሁ እዛው መቀዶኒያ የበረከት ሥራ አዘጋጅተዋል መገኘት ትችላላችሁ። ያልተመቻችሁ ደግሞ ማታ መምህር ተስፋዬ ባዘጋጀው መርሀ ግበር መገኘትና የቻልን የታዘዝነው ይዘን ብንገኝ መልካም ነው። #ሸር አድርጉ!

👉 የበረከት ሥራ ጥሪ! በመምህር ተስፋዬ ለሐሙስ የሚመቻችሁ በአካል በመገኘት በዚህ የበረከት ሥራ ሁላችሁም እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል። የሚመቻችሁ ጠዋትም አባታችን ቀሲስ ሄኖክ እንዲሁ እዛው መቀዶኒ
👉 የበረከት ሥራ ጥሪ! በመምህር ተስፋዬ ለሐሙስ የሚመቻችሁ በአካል በመገኘት በዚህ የበረከት ሥራ ሁላችሁም እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል። የሚመቻችሁ ጠዋትም አባታችን ቀሲስ ሄኖክ እንዲሁ እዛው መቀዶኒያ የበረከት ሥራ አዘጋጅተዋል መገኘት ትችላላችሁ። ያልተመቻችሁ ደግሞ ማታ መምህር ተስፋዬ ባዘጋጀው መርሀ ግበር መገኘትና የቻልን የታዘዝነው ይዘን ብንገኝ መልካም ነው። #ሸር አድርጉ!

» አንድ ሰው መፍትሔ የሌለው የሚመስል መከራ ሊገጥመው ይችላል። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ መከራው የገጠመው ጥቂት ኃጢአቶችን ስለ ፈጸመ መሆኑን ከማስጠንቀቂያ ጋር ይነግረዋል። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ቃሉ ንስሓ ከገባህ መከራው ፍጻሜ ያገኛል እያለ ውስጡን ሲመክረው ይሰማል። ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ስለ ንስሓው ሲል ለሰውየው ይራራለታል። » የእግዚአብሔር ድምፅ አንድ ሰው ሲታመም ወይም እርሱ የሚወደው ሌላ ሰው ሲታመም ሊመጣ ይችላል። በዚህ ጊዜ እንዲጸልይ ወይም ስእለት እንዲሳል የሚመክረውን ድምፅ ከውስጡ ይሰማል ይህ ድምፅ የእግዚአብሔር ድምፅ ነው። » የዮሴፍ ወድሞች እህል ሊገዙ ወደ ግብጽ ከወረዱ በኋላ በዚያ ችግር ሲገጥማቸው እርስ በእርሳቸው እንዲህ በማለት ተነጋግረው ነበር፦ "በእውነት ወድማችንን በድለናል እኛን በማማጠን ነፍሱ ስትጨነቅ አይተን አልሰማነውና ስለዚህ ይህ መከራ መጣብን።"/ዘፍ 42፥21/ ከዚህ በኋላ ለዮሴፍ እንዲህ ብለውታል፦ "ለጌታዬ ምን እንመልሳለን? ምንስ እንናገራለን? ወይስ በምን እንነጻለን? እግዚአብሔር የባሪያዎችህን ኃጢአት ገለጠ"/ዘፍ 44፥16/ ኃጢአታቸውን እንዲያስታውሱ ኋላም እንዲገሰጹ ያደረጋቸው የእግዚአብሔር ድምፅ ነው። » ነቢዩ ዳዊት የጌራ ልጅ በሆነው በሳሚ ሲሰደብ የእግዚአብሔር ድምፅ ውስጡ ስላለፈ ኃጢአቱ እየወቀሰው መሆኑን አዳምጧል። ስለሆነም በዙሪያው ለነበሩ ሰዎች "እግዚአብሔር ዳዊትን ስደበው ብሎታልና ይርገመኝ።" /2ኛ ሳሙ.16፥10/ በማለት በግልጽ ተናግሯል። » ረሀብና የመሬት መንቀጥቀጥ በዓለም ሲደርስ የእግዚአብሔር ድምፅ በመላው ዓለም ውስጥ ይሰማል። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ የሚናገረን "ወደ እኔ ተመለሱ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ።" /ሚል 3፥7/ እያለ ነው። ይህ ድምፅ በረሀቡ ወይም በመሬት መንቀጥቀጡ ጉዳት ለደረሰባቸው ሀገሮች የሚሆን የእርዳታ ጥሪ ለማሰማት ወይም ሌሎቹ ከእነርሱ ትምህርት በመውሰድ ንስሓ እንዲገቡ ለማድረግ ወይም ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኝት ዝግጅት እንዲያደርጉ ነው። » ስለዚህ ማንኛውም ዓይነት መከራ ውስጥ ስትገቡ ከውስጣችሁ ያለውን የእግዚአብሔር ድምፅ አድምጡት እርሱ ለእናንተ ሊነግራችሁ የሚወደው ምን እንደ ሆነ ታውቃላችሁና። #አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@iam_haile

‛‛ጸሎትህ ወዲያውኑ መልስ ባያገኝ ተስፋ አትቁረጥ፤ አንተ ከምታውቀው በላይ እግዚአብሔር ላንተ የሚያስብበት የተሻለ ጊዜ አለው።’’ (አባ እንጦንስ)

የአይነጥላ ክፉ ባሕሪይና የሚያስከትለው መዘዝና መፍትሔው!! እርጉዞችና አራሶች ይኼንን በደንብ አዳምጡ!! የፈለግነውን ማግኘት ለምን አቃተን? #ጸሎት #ስግደት https://youtu.be/x9vsIjjvqDQ?si=0Yc4VFubi8Zi75CE

«መንፈሳዊ የሕልም ፍቺ» «ሰላም ወንድሜ እህቴ አርምሞ ይዛ ነበር እና ህልሟን ፍታልኝ አረብ አገር ልሂድ ብላ አስባ እመቤቴን ጠይቂ ብያት ነበር አርምሞ የገባችው 1ያየችው ህልም ፕሌን ውስጥ ብዙ ሰው አለ እለች እና ፕሌኑ ተገለበጠ አለች። 2ያየችው ህልም አንች አተር ክክ ሰጠሽኝ እና ይደርሳል አብስይው አልሽኝ አለች። 3ተኛ ደሞ አርምሞ ላይ እያለሁ ህልሜን በወረቀት እፅፍ ነበር አለች እና የሆንች መነኩሴ መጥታ ከምፅፍበት ወረቀት ላይ ደቃቃ ፅሁፍ ትፅፍ እና አትቸኩይ ትለኛለች አለች እና በብዛት እንጀራ ስትጋግር። የ9ዓመት ህፃን ልጅ ምግብ አምጥቶ ይሰጠኝ እና ብልቼ ጨርሸ ሰሀኑን ልመልሰው ስል እኔ ነኝ ምወስደው ብሎ በጠባብ መንገድ ይሄዳል አለኝ የሆነች መነኩሴ ደግሞ ከእጀ ላይ እንዳለች ሙታብኝ መልሳ ትነሳ እና ሽቶ እና ሳሙሳ ሰጣኝ ትሄዳለች አለች ሌላ ህልም ደግሞ ከእህቴ ጋ ምግብ እየበላን በጫማ እንጣላለን አለች ከዛ እኔ የራሴን ጫማ አደርግ እና የምበላውን ምግብ ለሌላ ሰው ሰጠሁት አለች።» የሕልሙ መንፈሳዊ ፍቺ ይኼው፡ 1ኛ. "ፕሌን ውስጥ ብዙ ሰው አለ እለች እና ፕሌኑ ተገለበጠ አለች።" - አውሮፕላን: የመረጠችው የሕይወት ጎዳና ወይም ለመሄድ ያሰበችው ጉዞ (ወደ አረብ አገር) ምሳሌ ነው። - ብዙ ሰው: ብዙዎች የሚከተሉትን የዓለማዊ ፍላጎት ጎዳና ያሳያል። - መገልበጥ/መውደቅ: ይህ ሕልም እጅግ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ነው። ፕላኑ መገልበጡ ያሰበችው ጉዞ ወይም የሕይወት ለውጥ (በተለይም ወደ አረብ አገር የመሄድ ዕቅድ) ከባድ መንፈሳዊ ወይም አካላዊ አደጋ፣ ውድቀትና ሥጋት ያለበት መሆኑን ያሳያል። እመቤታችንን በጠየቀችው ጥያቄ ላይ "አትሂጂ!" የሚል ቀጥተኛ መልስ እንደተሰጣት ሊቆጠር ይችላል። 2. ሁለተኛው ሕልም፡ አተር ክክ እና "አብስይው" "አንች አተር ክክ ሰጠሽኝ እና ይደርሳል አብስይው አልሽኝ አለች።" - አተር ክክ (ደረቅ ምግብ): ክክ የደረቀ በመሆኑ፣ ምኞቷ፣ ጸሎቷ ወይም ያሰበችው ነገር ወዲያውኑ የሚፈጸም ሳይሆን ጊዜ፣ ትዕግሥትና መንፈሳዊ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑን ያመለክታል። - "ይደርሳል አብስይው": ይህ መንፈሳዊ ትዕዛዝ ነው። የምትፈልገው ነገር በእርግጥም እንደሚመጣ ("ይደርሳል") ተስፋ እየሰጣት፣ ነገር ግን በጸሎት፣ በምጽዋት፣ እና በጽድቅ ሥራ እንድትዘጋጅና እንድትጠብቅ ("አብስይው" – አዘጋጂው) እየመከራት ነው። እግዚአብሔርን በመታመን እንድትታገሥ የሚሰጥ መልእክት ነው። 3. ሦስተኛው ሕልም፡ መነኩሴዋ እና "አትቸኩይ" "መነኩሴ መጥታ ከምፅፍበት ወረቀት ላይ ደቃቃ ፅሁፍ ትፅፍ እና አትቸኩይ ትለኛለች አለች።" - መነኩሴ: የቅድስና ሕይወት፣ ቤተ ክርስቲያን ወይም ቅድስት የሆነች የመንፈስ አገልጋይ ምሳሌ ናት። እመቤታችንን ጠይቂ ብላችኋት ስለነበር፣ መነኩሴዋ የእመቤታችን ወይም የቅዱስ መልአክ መልእክት አስተላላፊ ልትሆን ትችላለች። - ደቃቃ ጽሑፍ: መልእክቱ ትክክለኛ፣ ዝርዝር እና በመንፈሳዊ መዝገብ ላይ የሰፈረ መሆኑን ያመለክታል። - "አትቸኩይ": ይህ ቀጥተኛ የመንፈስ ትዕዛዝ ነው። ከሁለተኛው ሕልም ጋር ተደምሮ፣ ወደ አረብ አገር የመሄድ ዕቅዷን ወዲያውኑ እንዳትወስንና እንዳትፈጽም ይከለክላታል። መልሱ በሒደት ላይ እንዳለና መታገሥ እንዳለባት ያረጋግጣል። 4. አራተኛው ሕልም፡ እንጀራ፣ ሕፃን ልጅ እና ጠባብ መንገድ - "በብዛት እንጀራ ስትጋግር የ9ዓመት ህፃን ልጅ ምግብ አምጥቶ ይሰጠኝ እና ብልቼ ጨርሸ ሰሀኑን ልመልሰው ስል እኔ ነኝ ምወስደው ብሎ በጠባብ መንገድ ይሄዳል አለኝ።" - እንጀራ መጋገር: የዕለት ተዕለት ተግባሯን፣ የጉልበት ሥራዋን ወይም መንፈሳዊ ዝግጅቷን ያመለክታል። - የ9 ዓመት ሕፃን ምግብ ሲሰጣት: ቁጥር 9 የመላእክት ክፍል እና የመንፈሳዊ ፍጹምነት ምሳሌ ሊሆን ይችላል። ሕፃኑ ንጽሕናን፣ ወይም ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ራሱ (ምግብ ሲሰጥ) ሊያመለክት ይችላል። ይህ መለኮታዊ ምሕረትና አቅርቦት እንዳላት ያሳያል። - "እኔ ነኝ ምወስደው ብሎ በጠባብ መንገድ መሄድ": "ጠባብ መንገድ" የጽድቅ ጎዳና (ማቴዎስ 7:14) ነው። ሕፃኑ ሰሃኑን የሚወስደው በጠባቡ መንገድ ነው ማለቱ፣ መንፈሳዊ በረከቷና ምሕረቷ የሚጸናው ዓለማዊውን ምቾት ትታ ሃይማኖታዊውንና ጠባቡን የትሩፋት ጎዳና ስትከተል ብቻ መሆኑን የሚገልጽ ትምህርት ነው። 5. አምስተኛው ሕልም፡ የሞተች መነኩሴ መነሳት፣ ሽቶና ሳሙሳ "የሆነች መነኩሴ ደግሞ ከእጀ ላይ እንዳለች ሙታብኝ መልሳ ትነሳ እና ሽቶ እና ሳሙሳ ሰጣኝ ትሄዳለች አለች።" - መነኩሴ መሞትና መነሳት: በሕይወቷ ውስጥ ተስፋ የቆረጠችበት ወይም "ሞተ" ብላ ያሰበችው ጉዳይ (መንፈሳዊ ሕይወት፣ ጤና ወይም የፋይናንስ ሁኔታ) በእግዚአብሔር ኃይል እንደሚነሳና እንደሚታደስ የሚያሳይ ነው። - ሽቶ (ቅባት): የቅድስና፣ የመንፈስ ቅዱስ በረከት፣ ክብርና መልካም ሥራ ምሳሌ ነው። የመንፈሳዊ ዕድገት ምልክት ነው። - ሳሙሳ: ዘመናዊ ምግብ እንደመሆኑ መጠን፣ ምናልባት ከባድ ከሆነው መንፈሳዊ ትሩፋት ጎን ለጎን የሚገኝ ትንሽ ዓለማዊ ዕረፍት ወይም ያልጠበቀችው ጥቅም ምሳሌ ሊሆን ይችላል። ትልቁ በረከት ሽቶው (መንፈሳዊው) ነው፣ ሳሙሳው (ሥጋዊው) እንደ ተጨማሪ ይሰጣታል። 6. ስድስተኛው ሕልም፡ በጫማ መጣላት እና ምግብ መስጠት "ከእህቴ ጋ ምግብ እየበላን በጫማ እንጣላለን አለች ከዛ እኔ የራሴን ጫማ አደርግ እና የምበላውን ምግብ ለሌላ ሰው ሰጠሁት አለች።" - በጫማ መጣላት: ጫማ መንፈሳዊ ጉዞን፣ ቃል ኪዳንን ወይም የወንጌልን ሰላም ያመለክታል። ከእህቷ ጋር መጣላቷ የምትፈልገው የሕይወት ጎዳና ከቅርብ ዘመዶቿ/ጓደኞቿ አስተሳሰብ ጋር የተለያየ መሆኑን ያሳያል። - የራሷን ጫማ ማድረግ: የራሷን መንፈሳዊ መንገድ መምረጥና በራሷ ሃይማኖታዊ እምነትና ውሳኔ መጽናቷን ያመለክታል። በሌሎች ተጽዕኖ ሳትደረግ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መከተል እንዳለባት ትምህርት ነው። - የምበላውን ምግብ ለሌላ ሰው መስጠት: መሥዋዕትነት፣ ምጽዋትና ዓለምን መናቅ ነው። የሥጋን ፍላጎትና ጊዜያዊ ምቾት ለሌላ ሰው በመተው፣ መንፈሳዊውን ሕይወትና ሰማያዊውን በረከት መምረጧን ያመለክታል። የህልሙ ፍቺ ይኼንን ይመስላል እንግዲህ ተረድቶ መንቃትና የእግዚአብሔርን ጊዜ መጠበቅ ያስፈልጋል ለሁሉም። አሁንም ህልማችሁን በጹሁፍ በውስጥ መስመር ላኩልኝ! https://t.me/haile_gebriel_tube_bot #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@iam_haile

ከመተት መንፈስ ለመላቀቅና በተለይም በጨጓራ ህመም የምትሰቃዬ ይኼንን አድርጉ!! #መተት #መንፈስ #አጋንንት #ጸሎት #ስግደት #የጨጓራ_ህመም! https://youtu.be/X6x0qqEZsQA

ሁላችንም ማየት ያለብን ተዓምር! https://youtu.be/X3blLQ2Cv5Q?si=M-YDsStfZP-BoibP

+1
ስውሯ ማሪያም ችግሮቻችሁን ሁሉ ትፍታላችሁ። የእመቤታችን ረድኤት በረከት አይለየን በእውነት! የሚገርም እውነትም ስውሯ ማሪያም። 🙏 ለደጇ ያብቃችሁ።

ይኼንን ጸሎት በትክክል ከጸለያችሁ ምስጥር ይገለጽላችኋል!! ሴት ዓይነጥላ አጋንንት በወንዶች ላይ!! የሕሊና ጸሎት መንፈሳዊ በረከቶቹ! ጴንጠዎች ያቦካሉ ያሬዶ ያርማል!! https://youtu.be/xoXslmZ2XXE?si=D1QkRv9DHs5dMqwf

🔴ይኼንን ጸሎት በትክክል ከጸለያችሁ ምስጥር ይገለጽላችኋል!! ሴት ዓይነጥላ አጋንንት በወንዶች ላይ!! የሕሊና ጸሎት መንፈሳዊ በረከቶቹ! #ጸሎት #ስግደት https://youtu.be/xoXslmZ2XXE

🔴መተት ስታደስባችሁ እንዲህ አይነት ነገሮች ይላኩባችኋልና ንቁበት || ያለጸሎት መንፈሳዊ ዕድገት የለም || ሰው ከእግዚአብሔር ስርቅ እንዲህ ይሆናል #ጸሎት https://youtu.be/nLkZ-z-fD7c

መንፈሳዊ ጥያቄ 1፡ "ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን የወለደች የማርያምን ዕጮኛ ዮሴፍን ወለደ" ይላል (ማቴ.፩፥፲፰)። ያዕቆብ ለእመቤታችን ምኗ ነው? መልስ፦ ያዕቆብ ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ነው። አልዓዛር የዮሴፍም የድንግል ማርያምም ቅድመ አያታቸው ነው። የዮሴፍ ትውልድ በቅደም ተከተል እንዲህ ነው => አልዓዛር➡️ማትያን➡️ያዕቆብ➡️ዮሴፍ ነው። የድንግል ማርያም ትውልድ በቅደም ተከተል ደግሞ እንዲህ ነው => አልዓዛር➡️ቅስራ➡️ኢያቄም➡️ድንግል ማርያም ነው። መንፈሳዊ ጥያቄ 2፡ "እርሱ ግን ይህን ሲያስብ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ታየው። እንዲህም አለ ዮሴፍ ሆይ ከእርሷ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና ዕጮኛኽን ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ" ይላል (ማቴ.፩፥፳)። ዮሴፍ ሆይ ከእርሷ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና ሲል ምን ማለት ነው? መልስ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ጊዜ ከሕገ ተፈጥሮ በላይ የሆኑ አምላካዊ ሥራዎችን ለመንፈስ ቅዱስ አድሎ ይናገራል። በሕገ ተፈጥሮ ሰው የሚፀንሰው በወንድ ዘር፣ በሩካቤ ሥጋ ነው። የድንግል ማርያም ጌታን መጸነስ ግን ያለ ሩካቤ፣ ያለ ወንድ ዘር የሆነ ነው። ይህንን አምላካዊ ሥራ ግብረ መንፈስ ቅዱስ ይለዋል። ከእርሷ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነው ማለት በሕገ ተፈጥሮ በሩካቤ በወንድ ዘር ሳይሆን በአምላካዊ ጥበቡ ነው ማለት ነው። ጥያቄና መልሱ ይቀጥላል... #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@iam_haile

ጥቅምት ፳ /20/ ዳግመኛም በዚህች ቀን የስሙ ትርጓሜ ጠባቂና አዳኝ የሆነ የታላቅ ነቢይ የኤልሳዕ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። እርሱም አሜሁላ ከሚባል አገር ከይሳኮር ነገድ ነው ብዙ ትንቢትን ተናግሮአ
ጥቅምት ፳ /20/ ዳግመኛም በዚህች ቀን የስሙ ትርጓሜ ጠባቂና አዳኝ የሆነ የታላቅ ነቢይ የኤልሳዕ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። እርሱም አሜሁላ ከሚባል አገር ከይሳኮር ነገድ ነው ብዙ ትንቢትን ተናግሮአል ብዙ ተአምራትንም አድርጓል። የኢያሪኮም ሰዎች ኤልሳዕን ጌታችን እንደምታያት የዚች አገር ኑሮዋ ያማረ የተወደደ ነው የአገሩ ውኃ ግን ክፉ ነው ሴቶች ሲጠጡት ይመክናሉ አሉት ኤልሳዕም ጨው ጨምራችሁ አዲስ ሸክላ አምጡልኝ አላቸው እነርሱም አመጡለት ። ኤልሳዕም ወደ ውኃው ምንጭ ሒዶ ያንን ጨው በውስጡ ጨመረውና እግዚአብሔር እንዲህ አለ እርሱን ከመጠጣት የተነሣ የሚሞት እንዳይኖር የሚመክንም እንዳይኖር ይህን ውኃ ለውጥኩት አለ አላቸው ። ከዚያችም ቀን በኋላ ኤልሳዕ እንደተናገረ እስከ አሁን ድረስ ያ ውኃ ተለወጠ። የዚህ የነቢይ ኤልሳዕ ተአምራቱ ብዙ ነው የሶርያውን ሰው ንዕማንን ከለምጹ ያነጻው እርሱ ነው ሁለት ሙታንን አንዱን በሕይወት ሳለ ሌላውንም ከሞተ በኋላ አስነሥቷል። የትንቢቱንም ወራት ፈጽሞ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

+ ክርስትና ዝም ብሎ መቀመጥ አይደለም፤ ከኃጢአት፣ ከሰይጣንና ከሥጋዊ ፈቃድ ጋር የማያቋርጥ ትግል ነው። "ሕይወት የማያቋርጥ ትግል ነው" ("Life is a continuous struggle") ይላሉ
+ ክርስትና ዝም ብሎ መቀመጥ አይደለም፤ ከኃጢአት፣ ከሰይጣንና ከሥጋዊ ፈቃድ ጋር የማያቋርጥ ትግል ነው። "ሕይወት የማያቋርጥ ትግል ነው" ("Life is a continuous struggle") ይላሉ። ሁልጊዜ ንቁ መሆን እና ከፍቃደ ሥጋ ጋር መታገል ያስፈልጋል። በዓለማዊ ጫጫታ ውስጥ የምንኖር ሰዎች፣ ከዕለት ተዕለት ውጥረት ራሳችንን አግለን እግዚአብሔርን ብቻ የምናዳምጥበት የግል ጸሎትና ንባብ ጊዜ ሊኖረን ይገባል። ይህ የሰላም ምንጭ ነው። ብፁዕነታቸው ትሕትናንና ሌሎችን በፍጹም አለመውቀስን ያስተምራሉ። "ሌሎችን ከመፍረድ ይልቅ ራስህን ተች" ይላሉ። ሌሎች የሚሠሩት ኃጢአት ቢታይም እንኳ የእኛ ትኩረት የራሳችንን ነፍስ በማዳን ላይ መሆን አለበት ይላሉ። በረከታቸው ይደርብን! (ብጹዕ አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ)

🔴ይኼንን ልጅ አሁኑኑ አቁም ልንለው ይገባል!! በጽዋ ማህበራት የተከለከሉ 6 ነገሮች! የመናፍቃኑ ሴራ በገድለ ዮሐንስ ተጋለጠ!! ግሸን ኼዶ ሳይቆርብ መምጣት! https://www.youtube.com/watch?v=WcVqbTwoPrc&pp=ygUNaGFpbGUgZ2VicmllbA%3D%3D

ያሳዝናል! በመተት አራት መኖሪያ ቤቱንና ኑሮውን ተነጠቀ! በዲያብሎስ የባርነት ቀንበር ላለመያዝ ይኼንን አድርጉ!! እባካችሁ ምዕመናን የንስሐ አባቶቻችሁን መርምሩ! https://youtu.be/CeBlM0_QudY

«ይኼው አሁንም ሌላ ሐዘን!! ጌታ ሆይ ይቅር በለን!» በአርሲ ሀገረ ስብከት በኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ። ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ] በአርሲ ሀገረ ስብከት ጉና ወረዳ በሚገኘ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን መገዳላቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያሳያል። በደረሰን መረጃ መሠረት በቀበሌው የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን ከለሊቱ 6:00 ሰዓት አካባቢ በዕለተ ረቡዕ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ለ14 አጥቢያ ከተኙበት ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሲሆን ስድስቱ ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፈት ቀድመው ታፍነው ተወስደው ነበር ተብሏል። የተገደሉት ምእመናን የዕድሜ ክልላቸው ከ2 ዓመት ጀምሮ እስከ 76 ዓመት አዛውንት እንደሚገኙበት መረጃው ይገልጻል። በተጨማሪም ሁለት ሰዎች በጥቃቱ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ለተሻለ ሕክምና ወደ አቦምሳ ከተማ ሪፈር መሄዳቸውን በመረጃው ተያይዞ ተነግሯል፡፡ ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ በቀበሌው ውስጥ የሚኖሩ 8 ኦርቶዶክሳውያን ሌሊት ላይ ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸውን በደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል። ከተገደሉት ምእመናን ውስጥ 6ቱ በገገሌ በዓለወልድ ቤተ ክርስቲያን፣አንድ ደግሞ በሞዬ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን እና ቀሪ ሟቾች ባሉበት አካባቢያቸው ሥርዓተ ቀብራቸው መፈጸሙ ተገልጿል። በመረጃው እንደተመላከተው በቀበሌው ባለ ከፍተኛ ስጋት በቀጣይ የባሰ ችግር እንዳይፈጠር በሀገረ ስብከት ደረጃ ከመንግሥት ጋር በጋራ መሥራት ይገባል ተብሏል። በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ሁኔታዎችን ለማረረጋት የሀገር መከላከያ በስፍራው እንደሚገኝ በመረጃው ተጠቅሷል። 👉 ©ማኅበረ ቅዱሳን #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@iam_haile

«ውድ ቤተሰቦቼ ህልምን በተመለከተ ስትልኩልኝ እባካችሁ በተቻላችሁ መጠን "በጹሁፍ አድርጉልኝ" ብዙ ሰው በድምጽ ይልካል አይሰማም ወይም ድምጹ ይቆራረጣል ወይም ደግሞ ድምጹ ያነሰ ይሆናል ወይም ደግሞ መልዕክቱን በግልጽ አይናገርም። ስለዚህ በተቻላችሁ መጠን እንድንረዳዳ "በጽሁፍ" አጠር አድርጋችሁ ላኩልኝ። እኔም እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ በገባኝና ባወኩት መጠን ለመፍታት እሞክራለሁ ካልመለስኩ ደግሞ ታገሱ አደራ!» በዚህ በኩል ላኩ https://t.me/haile_gebriel_tube_bot