uk
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Відкрити в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Показати більше
2 280
Підписники
+124 години
+117 днів
+3230 день
Архів дописів
የንስሐ አባት የምንቀይርባቸው 10 መሠረታዊ ምክንያቶች!! በንስሐ አባትና ልጅ መካከል ያለው ግንኙነት!! የንስሐ አባት የሚያስቀይሩ ከባባድ ስህተቶች!! https://youtu.be/GEh1iwqwtoQ

በምትጸልይበት ጊዜ አትቸኩል፥ ምጽዋት መመጽወትንም አታቃልል። የሚያሳዝን፥ ደስ የሚያሰኝም አለና፥ ባዘነ ሰው አትሳቅ። . ብዙ ናቸው ብለህ ከኃጢአተኞች ጋር አንድ አትሁን። [ሲራክ 7: 10-11 & 16] ———______——— 1. ጥድፍ ጥድፍ ብለህ ብዙ ለመጸለይ ከመመኮር አጭርም ቢሆን ጸሎት ተረጋግተህ ከልብህ በማስተዋል ሆነህ መጸለይ 2. ስለ ምጽዋት ቅዱሳት መጽሐፍት የሚምሰክሩት ነገር በጣም ጠንካራ ነው.. “ለደሃ የሚሰጥ ለእግዚአብሔር ያበድራል” የሚልም ሳይቀር ነው ያለው[ምሳ 19:17].. ስለዚህም በፍቅር የሆነ ቸርነትን እናድርግ.. በማርያም ብሎ እየለመነን አልፈነው ቤት ስንገባ እኛም ጌታችንን “በማርያም” ብለን የምንለምን ነን.. 3. በኃጢአት ውስጥ ያሉ ብዙዎች ቢሆኑ ለመመሳሰል ብለህ ኃጢአተኛ አትሁን.. ለነ ኖኅ እና ሎጥ የተነገረውን አስብ 2ጴጥ 5-8.. ራስህን ለእግዚአብሔር ለይ.. አብረህ መሞትና እግዚአብሔርን ማጣት የለብህም.. መልካም ውሎ..ይሁን ለሁላችን!

«ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ» » በጥቅምቱ ጉባኤ መክፈቻ ከተናገሩት » ያለምንም ደመወዝ በራሳቸው አቅም በግብርና እየተዳደሩ ቤተ ክርስቲያንን በጥሩ ስብዕና በንፅህና በቅድስና ጠብቀው ያስረከቡ እል
«ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ» » በጥቅምቱ ጉባኤ መክፈቻ ከተናገሩት » ያለምንም ደመወዝ በራሳቸው አቅም በግብርና እየተዳደሩ ቤተ ክርስቲያንን በጥሩ ስብዕና በንፅህና በቅድስና ጠብቀው ያስረከቡ እልፍ አእላፍ አበው እንዳልነበሯት ዛሬ የተሻለ ኑሮና ደመወዝ እያገኘን #እግዚአብሔርን እንደ ቀኖናው ማገልገል አቅቶናል። እግዚአብሔር ይማረን። የብጹዕ አባታችን በረከት ይደርብን!

ጥቅምት ፭ /5/ ‎ ‎አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) ‎ ‎ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ:: ‎ ‎አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱ
ጥቅምት ፭ /5/ ‎ ‎አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) ‎ ‎ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ:: ‎ ‎አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ562 ዓመታት በዚህች ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ ልብስ ያልለበሱ ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ ነፍሳትን ያዳኑ አባት ናቸው። ‎ ‎የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ስለ ሀገራችን ፍቅር ሲሉ ለ100 ዓመታት በደብረ ዝቋላ መከራን ተቀብለዋል። ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው። ‎ ‎በ8ኛው ክ.ዘ አካባቢ የተወለዱት አባታችን ያረፉት በ14ኛው መቶ ክ.ዘ አካባቢ ነው። ፍጥረታትን ሁሉ አዘው መጋቢት 5 ቀን ሲያርፉ ግሩማን መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል። ‎ ‎ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍቱ መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሃ ነገስት አንቀጽ 15 ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ የመጋቢት 27 ስቅለት ጥቅምት 27 ቀን እንደሚከበረው ሁሉ ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር ተደረገ፡፡ ‎ ‎የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን!አሜን ‎ወስብሐት ለእግዚአብሔር ‎ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር እና ፍትሃ ነገስት

ጸሎትን ጸሎት የሚያሰኙ 4ቱ መሠረታዊ ቅኝቶና ማወቅ ያሉብን ነገሮች!! የጸሎት ቅደም ተከተል ይኼንን እወቁ!! ከሦስት ዓይነት ሴቶች ተጠንቀቁ!! https://youtu.be/WG1d_z9duck?si=YvjKYdZtVMgOJiAW

SPIRITUALISM ከአጋንንት ጋር የሚያቆራኝ ድብቁ የአዲሱ ዓለም ሃይማኖት!! መስገድ መጸለይ መንበርከክ ስትጀምሩ መንፈሳችሁ ይለያል! #spiritualism https://youtu.be/GQXhMmRG1DI

እግዚአብሔር ረስቶኛል ጸሎተን አይሰማኝም ለምትሉ ይኼንን አዳምጡና ወስኑ!! አስቀዳሹና መዝሙር ደጋሚው አጋንንት ጠቋርና ሴራዎቹ!! ጸጸት በንስሐ ወቅት! https://youtu.be/a-EdnBequS4

ውድ ቤተሰቦቼ፣ መወያየት የምትፈልጉት መንፈሳዊ ጥያቄ፣ ማጋራት የምትፈልጉት አስተማሪ ታሪክ፣ ወይም የሚያነቃ መልዕክት ካላችሁ፣ አብረን እንድንማማር በዚህ የቴሌግራም ቦት በኩል ያግኙን። 👉 http
ውድ ቤተሰቦቼ፣ መወያየት የምትፈልጉት መንፈሳዊ ጥያቄ፣ ማጋራት የምትፈልጉት አስተማሪ ታሪክ፣ ወይም የሚያነቃ መልዕክት ካላችሁ፣ አብረን እንድንማማር በዚህ የቴሌግራም ቦት በኩል ያግኙን። 👉 https://t.me/Haile_Gebriel_Tube_bot 👉 ሰላም፣ ፍቅርና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን። በርቱ!

«ስለ ሌሎች መዳን ከማይጨነቅ ክርስቲያን በላይ ሰነፍ ሰው የለም፡፡ ወዳጄ “እኔ ድኻ ነኝና ይህን ማድረግ አልችልም” የምትል አትኹን፤ ባለ ኹለት ዲናሯ ሴት ትወቅስሃለችና፡፡ ዳግመኛም “ወርቅም ብርም
«ስለ ሌሎች መዳን ከማይጨነቅ ክርስቲያን በላይ ሰነፍ ሰው የለም፡፡ ወዳጄ “እኔ ድኻ ነኝና ይህን ማድረግ አልችልም” የምትል አትኹን፤ ባለ ኹለት ዲናሯ ሴት ትወቅስሃለችና፡፡ ዳግመኛም “ወርቅም ብርም የለኝም” ብሎ የተናገረ ጴጥሮስ ይወቅሰሃልና፡፡ ምናምንቴ ነኝ አትበል፤ እንዲህ ስትል ምናምንቴዎቹ ሐዋርያት እንዳይሰሙህ! "እኔ በሽተኛ ነኝ" አትበል፤ በሽተኛው ጢሞቴዎስ ይታዘብሃልና፡፡ ፈጽመህ “እኔ ሌሎች ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ማምጣት አይሆንልኝም” አትበል፡፡ በእውነት ክርስቲያን ከኾንክ ይህን ከማድረግ ይልቅ አለማድረጉ ይከብዳልና፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ እንድትኾን አድርጎ ፈጥሮሃልና ተፈጥሮህን መካድ አይቻልህም፡፡ ክርስቲያን በጨለማ ውስጥ ለሚኖሩ ወንድሞቹ ብርሃኑን ከሚከለክል ይልቅ ፀሐይ ብርሃኗን ብትከለክል ይቀላልና ስለዚህ አልጠቅምም አትበል፡፡» ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@iam_haile

ጥቅምት ፫ /3/ በዚሕችም ቀን ሊቀ ጳጳሳት አባ ስምዖን አረፈ። የዚሕ አባት ወላጆቹ ሃይማኖታቸው የቀና እርሱም ከታናሽነቱ የሃይማኖት ወተትን ጠጥቶ ያደገ የቤተክርስቲያንንም ትምሕርት ተምሮ ያደገ ነ
ጥቅምት ፫ /3/
በዚሕችም ቀን ሊቀ ጳጳሳት አባ ስምዖን አረፈ። የዚሕ አባት ወላጆቹ ሃይማኖታቸው የቀና እርሱም ከታናሽነቱ የሃይማኖት ወተትን ጠጥቶ ያደገ የቤተክርስቲያንንም ትምሕርት ተምሮ ያደገ ነው። ወደ አስቄጥስ ገዳም በሊቀ ጳጳሳት በአባ ያዕቆብ ገዳም የምንኩስናን ልብስ ለብሶ መነኮሰ ተጋድሎውንም በየጊዜው ጨመረ ሥጋውንም አያደከመ በእርሱ ዘንድ ኖረ። ስለ በጎ ተጋድሎውና ስለ አገልግሎቱ ዳግማዊ ሊቀ ጳጳስ አባ ማርቆስ ወደ አባ ያዕቆብ ወስዶት እያገለገለው ከእርሱ ጋር ኖረ። አባ ያዕቆብ በአረፈ ጊዜም ካሕናትና ኤጲስቆጶሳት ትሩፋቱንና ያማረ ሥራውን ስለተመለከቱ አምላካዊ ፍቅር አነሳስቷቸዋልና በወንጌላዊ ማርቆስ መንበር ላይ ይዘው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት። በሹመቱ ጸንቶ መልካምን ጉዞ ተጓዘ እግዚአብሔርንም እያገለገለ የሃይማኖትንም ሕግ በማስጠበቅ የክርስቶስን መንጋዎች ጠበቀ። በሹመቱ ወራትም ቤተ ክርስቲያን በጸጥታና በሰላም ኖረች። ከዚሕም በኋላ እግሮቹን በጽኑዕ ደዌ ታመመ እግዚአብሔርንም ከዚሕ ደዌ ያሳርፈው ዘንድ ለመነው ክብር ይግባውና ጌታችንም ልመናውን ተቀብሎ በሰላም በፍቅር በአንድነት አሳረፈው የሹመቱም ወራት አምስት ወር ከዐሥራምስት ቀን ነው። የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን! አሜን ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@iam_haile

#ድንግል_ሆይ ፣ ቅድስት ሆይ፣ ንጽሕት ሆይ፣ 🌹 የተመሰገንሽ ቡርክት ሆይ የድግልናሽ ምስጋና በኹሉ መላ ውዳሴሽም በዓለም ዙሪያ ሰፈፈ፤ የውቅያኖስ ባሕር በምልአቱ ውሱን ነው የሐኖስም ባሕር በመጠኑ
#ድንግል_ሆይ ፣ ቅድስት ሆይ፣ ንጽሕት ሆይ፣ 🌹 የተመሰገንሽ ቡርክት ሆይ የድግልናሽ ምስጋና በኹሉ መላ ውዳሴሽም በዓለም ዙሪያ ሰፈፈ፤ የውቅያኖስ ባሕር በምልአቱ ውሱን ነው የሐኖስም ባሕር በመጠኑ ልክ አለው፤ #ለአንቺ ምስጋና ግን ልክና መጠን ወሰንና መስፈርት፣ ማለቂያም የለውም አእምሮም አይወስነውም አንደበትም ተናግሮ ሊፈጽመው አይችልም“ #ኦ_ድንግል፣ ኦ ቅድስት፣ ኦ ንጽሕት ፣ኦ ቡሩክት፣ ኦ ኅሪት፣ ስብሐተ ድንግልናኪ መልአ በኵለሄ ወውዳሴ ዚአኪ ሰፈፈ ውስተ ኵሉ አጽናፈ ዓለም፤ ባሕረ ውቅያኖስ ውሱን በድንጋጊሁ ወባሕረ ሐኖስኒ ዐቅም ቦ በአምጣኒሁ ወለስብሐተ ዘኣኪሰ አልቦቱ ማኅለቅት ወኅሊናኒ ኢይክል አግምሮቶ ወልሳንኒ ኢይክል ፈጽሞቶ“ (አርጋኖን ዘሰኑይ ፰ ÷ ፲ - ፳፰) እንኳን ለጥቅምት 3 በዓታ ማሪያም ወርሃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ።

መምህር ግርማና ሊቁ ስምዓኮነ መልዓክ የነገሩን የማንቂያ መልዕክት!! መላዕክት ሲጸልዩ ካሳየኼኝ ኦርቶዶክስ እሆናለው!! https://youtu.be/L8D17Ker6Bk?si=hnNNO7nR98ogGldG

ጥቅምት ፩ /1/ በዚህችም ቀን በጥቅምት አንድ ቅድስት አንስጣሲያ በሰማዕትነት አረፈች። ይህችም ቅድስት መስተጋድልት ከሮሜ አገር ናት ወላጆቿም ክርስቲያኖች ናቸው ጠቃሚ የሆነ ትምህርትን በማስተማር
ጥቅምት ፩ /1/ በዚህችም ቀን በጥቅምት አንድ ቅድስት አንስጣሲያ በሰማዕትነት አረፈች። ይህችም ቅድስት መስተጋድልት ከሮሜ አገር ናት ወላጆቿም ክርስቲያኖች ናቸው ጠቃሚ የሆነ ትምህርትን በማስተማር ክብር ባለው በመልካም ሥርአት አሳደጓት። በአደገችም ጊዜ ወላጆቿ ሊያጋቡአት ፈለጉ እርሷ ግን በሥውር  በሮሜ ከሚገኙ  ወደ አንዱ ገዳማት ሂዳ የምንኩስና ልብስን በመልበስ በጾም በጸሎት በረኃብ በጽምዕ በመጠመድ ሥጋዋን አደከመች በቀኑ ርዝመት ትጾማለች በየሁለት ቀኖችም ታከፍላለች በጌታችን ጾም ግን ያለ ሰንበታት ቀን አትመገብም። ከዚሕም በኋላ የንጉስ ዳኬዎስ ወታደሮች ክርስቲያኖችን አሥረው በቁጣ ሲጎትቷቸው አይታ ልቧ በሃይማኖቷ ፍቅር ነደደና እንዲህ ብላ ዘለፈቻቸው የእውነት ፈጣሪን የካዳቹ ልባቹ የደነዘዘ እግዚአብሔር በመልኩና በአምሳሉ በፈጠራቸውና ስለ እነርሱም ነፍሱን አሳልፎ በሰጣቸው ላይ ለምን እንዲህ ትሠራላቹ። ወታደሮቹም ይሕን ሲሰሙ ተቆጡ ይዘውም ወደ መኮንኑ አቀረቧት እርሱም እንዲህ ብሎ ጠየቃት በእውነት አንቺ የተሰቀለውን የምታመልኪው ክርስቲያን ነሽን እርሷም ስለእኛ የተሰቀለውን ክብር ይግባውና እርሱን አመልከዋለው ብላ መለሰችለት። በዚያን ጊዜ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያት በሥጋዋም እሳትን ጨመረ  ከዛም ዘቅዝቆ ሰቀላት ከበታቿም አጤሱባት ከሃይማኖቷም ባልተናወጸች ጊዜ ራሷን በሰይፍ ቆረጧት። በመንግስተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለች። የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን! አሜን ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦መጽሐፈ ስንክሳር

ባሎችና ምስቶች ይኼንን ቀድሞ ብታውቁ ኖሮ ብዙ አትጎዱም ነበር!! 4ቱ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በኑሯችን!! በአምልኮት የተገነባ ቤትና ትዳር እንዲህ ነው!! #ንቁ https://youtu.be/WE_FA4qo5LQ?si=kSo2FiQjYds3JHUn

ሦስት ዓይነት ጠላቶች አሉብን ይኼንን አይታችሁ እራሳችሁን ፈትሹ!! ከሰውነቷ ዘይት የሚፈሳት ሴትና በተክሊል መጋባት ትዳር ላለመፍረስ ዋስትና ልሆን ይችላል?? https://youtu.be/4GuB0lTG-8k

«ኃጢአትን ባትሠራት መልካም ነው። ኃጢአትን ከሠራህ ሳትቆይ ንስሐ ብትገባ መልካም ነው። ንስሐ ከገባህ ዳግመኛ ወደ ኃጢአት ባትመለስ መልካም ነው። ወደ ኃጢአት ካልተመለስክ ይህ በእግዚአብሔር እርዳታና ቸርነት መሆኑን ብታውቅ መልካም ነው። ይህንን ካወቅህ ስለአለህበት ሁኔታ እግዚአብሔርን ብታመሰግን መልካም ነው።» ቅዱስ ባስልዮስ

photo content
+1

ሰማዕት ቅድስት አርሴማ
መስከረም ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን ከቅድስት አርሴማ ከእመምኔቷ ከአጋታ ጋር ደናግል በሰማዕትነት አረፉ። ይህም እንዲህ ነው በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ። ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ። እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ። ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው። ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት። የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው። ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ። አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ። ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕት ቅድስት አርሴማ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (ስንክሳር ዘወርኅ መስከረም) #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 https://www.youtube.com/@estifo2239

አይነጥላና ዛር መንፈሳችን ሲሆኑ ይኼንን በኑሯችን እናስተናግዳለን!! ውስጣችን ባዶ ሆኖ ውጭው ብቻ ቢያምር ምን ያደርጋል? ለወላጆች የተላለፈ ጥብቅ መልዕክት! https://youtu.be/ILMxW17lIp4?si=JC8bekI82FYgWThT

የፈስ ድግምትና መተት የትውልዱን ዕድል ያመሰቃቀለው የመናፍስቱ ሴራ!! ተበልቶና ሳይበላ የሚጸለይ ጸሎት የትኛው ይሆን? አጋብቶ የሚያፋቱ ክፉ መናፍስቶች!! https://youtu.be/-Vow7CYuHf4?si=KZFodQLUtK6umReA