es
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Ir al canal en Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Mostrar más
2 273
Suscriptores
+224 horas
+177 días
+2930 días
Archivo de publicaciones
ጥቅምት ፩ /1/ በዚህችም ቀን በጥቅምት አንድ ቅድስት አንስጣሲያ በሰማዕትነት አረፈች። ይህችም ቅድስት መስተጋድልት ከሮሜ አገር ናት ወላጆቿም ክርስቲያኖች ናቸው ጠቃሚ የሆነ ትምህርትን በማስተማር
ጥቅምት ፩ /1/ በዚህችም ቀን በጥቅምት አንድ ቅድስት አንስጣሲያ በሰማዕትነት አረፈች። ይህችም ቅድስት መስተጋድልት ከሮሜ አገር ናት ወላጆቿም ክርስቲያኖች ናቸው ጠቃሚ የሆነ ትምህርትን በማስተማር ክብር ባለው በመልካም ሥርአት አሳደጓት። በአደገችም ጊዜ ወላጆቿ ሊያጋቡአት ፈለጉ እርሷ ግን በሥውር  በሮሜ ከሚገኙ  ወደ አንዱ ገዳማት ሂዳ የምንኩስና ልብስን በመልበስ በጾም በጸሎት በረኃብ በጽምዕ በመጠመድ ሥጋዋን አደከመች በቀኑ ርዝመት ትጾማለች በየሁለት ቀኖችም ታከፍላለች በጌታችን ጾም ግን ያለ ሰንበታት ቀን አትመገብም። ከዚሕም በኋላ የንጉስ ዳኬዎስ ወታደሮች ክርስቲያኖችን አሥረው በቁጣ ሲጎትቷቸው አይታ ልቧ በሃይማኖቷ ፍቅር ነደደና እንዲህ ብላ ዘለፈቻቸው የእውነት ፈጣሪን የካዳቹ ልባቹ የደነዘዘ እግዚአብሔር በመልኩና በአምሳሉ በፈጠራቸውና ስለ እነርሱም ነፍሱን አሳልፎ በሰጣቸው ላይ ለምን እንዲህ ትሠራላቹ። ወታደሮቹም ይሕን ሲሰሙ ተቆጡ ይዘውም ወደ መኮንኑ አቀረቧት እርሱም እንዲህ ብሎ ጠየቃት በእውነት አንቺ የተሰቀለውን የምታመልኪው ክርስቲያን ነሽን እርሷም ስለእኛ የተሰቀለውን ክብር ይግባውና እርሱን አመልከዋለው ብላ መለሰችለት። በዚያን ጊዜ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያት በሥጋዋም እሳትን ጨመረ  ከዛም ዘቅዝቆ ሰቀላት ከበታቿም አጤሱባት ከሃይማኖቷም ባልተናወጸች ጊዜ ራሷን በሰይፍ ቆረጧት። በመንግስተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለች። የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን! አሜን ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦መጽሐፈ ስንክሳር

ባሎችና ምስቶች ይኼንን ቀድሞ ብታውቁ ኖሮ ብዙ አትጎዱም ነበር!! 4ቱ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ በኑሯችን!! በአምልኮት የተገነባ ቤትና ትዳር እንዲህ ነው!! #ንቁ https://youtu.be/WE_FA4qo5LQ?si=kSo2FiQjYds3JHUn

ሦስት ዓይነት ጠላቶች አሉብን ይኼንን አይታችሁ እራሳችሁን ፈትሹ!! ከሰውነቷ ዘይት የሚፈሳት ሴትና በተክሊል መጋባት ትዳር ላለመፍረስ ዋስትና ልሆን ይችላል?? https://youtu.be/4GuB0lTG-8k

«ኃጢአትን ባትሠራት መልካም ነው። ኃጢአትን ከሠራህ ሳትቆይ ንስሐ ብትገባ መልካም ነው። ንስሐ ከገባህ ዳግመኛ ወደ ኃጢአት ባትመለስ መልካም ነው። ወደ ኃጢአት ካልተመለስክ ይህ በእግዚአብሔር እርዳታና ቸርነት መሆኑን ብታውቅ መልካም ነው። ይህንን ካወቅህ ስለአለህበት ሁኔታ እግዚአብሔርን ብታመሰግን መልካም ነው።» ቅዱስ ባስልዮስ

ሰማዕት ቅድስት አርሴማ
መስከረም ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን ከቅድስት አርሴማ ከእመምኔቷ ከአጋታ ጋር ደናግል በሰማዕትነት አረፉ። ይህም እንዲህ ነው በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ። ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ። እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ። ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው። ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት። የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው። ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ። አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ። ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕት ቅድስት አርሴማ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (ስንክሳር ዘወርኅ መስከረም) #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 https://www.youtube.com/@estifo2239

አይነጥላና ዛር መንፈሳችን ሲሆኑ ይኼንን በኑሯችን እናስተናግዳለን!! ውስጣችን ባዶ ሆኖ ውጭው ብቻ ቢያምር ምን ያደርጋል? ለወላጆች የተላለፈ ጥብቅ መልዕክት! https://youtu.be/ILMxW17lIp4?si=JC8bekI82FYgWThT

የፈስ ድግምትና መተት የትውልዱን ዕድል ያመሰቃቀለው የመናፍስቱ ሴራ!! ተበልቶና ሳይበላ የሚጸለይ ጸሎት የትኛው ይሆን? አጋብቶ የሚያፋቱ ክፉ መናፍስቶች!! https://youtu.be/-Vow7CYuHf4?si=KZFodQLUtK6umReA

የፈስ ድግምትና መተት የትውልዱን ዕድል ያመሰቃቀለው የመናፍስቱ ሴራ!! ተበልቶና ሳይበላ የሚጸለይ ጸሎት የትኛው ይሆን? አጋብቶ የሚያፋቱ ክፉ መናፍስቶች!! https://youtu.be/-Vow7CYuHf4

#መድኃኔዓለም (27) - ምስጋና የሁል ጊዜ ተግባራቸው የሆነ ሰማያውያን መላእክት ምድራውያን ጻድቃን ሰማአታት ተመራምረው ለማይደርሱበት ለስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ። 🤲/መልክአ መድኃኔዓለም/ -
#መድኃኔዓለም (27) - ምስጋና የሁል ጊዜ ተግባራቸው የሆነ ሰማያውያን መላእክት ምድራውያን ጻድቃን ሰማአታት ተመራምረው ለማይደርሱበት ለስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ። 🤲/መልክአ መድኃኔዓለም/ - እኛ ደግሞ አስቀድመን የማናስተውል ነበርንና፤ የማንታዘዝ፥ የምንስት፥ ለምኞትና ለልዩ ልዩ ተድላ እንደ ባሪያዎች የምንገዛ፥ በክፋትና በምቀኝነት የምንኖር፥ የምንጣላ፥ እርስ በርሳችን የምንጠላላ ነበርን። ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥ - እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤ ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው። /ቲቶ 3 ፥ 3 - 7/

ለጸሎት ስንዘጋጅና ስንቆም ይኼንን ማድረጋችሁን ሁላችሁም አስተውሉ!! የዋቄፋታ መሪ ሆኜ እራሰን እስከማጥፋት ደርሼ ነበር!! የአቡነ ኤርሚያስ ጥብቅ መልዕክት! https://youtu.be/PqvyLdsO3UE?si=0hM-a8i54Kr-Yfx1

» ሕይወታችን ቢያበራ ኖሮ ቃላት አያስፈልጉንም ነበር። ሥራ ብናሳይ ኖሮ መምህራን አያስፈልጉም ነበር። እኛ እውነተኛ ክርስቲያኖች ብንሆን ኖሮ አንድም አህዛብ ባልቀረ ነበር። » ብዙ ሰባኪያን ስለ ግላዊ ገጽታና ስለ ክብር አጠባበቅ ይናገራሉ፤ አስፈላጊው ነገር ግን የልብ ንጽሕና ነው። የእግዚአብሔር ፍቅር ወደ ልብ ከገባ፣ የስብከት ፍላጎት ሳያስፈልግ የነውር ሁሉ ዱካ በራሱ ጊዜ ይጠፋል። የውስጥን ማረም መሠረት ነው። » ስህተቴ፣ እኔ መስታወት መሆኔ ነው፤ ይህ መስታወት በፊቱ ለሚቆም ማንኛውም ሰው እውነተኛ ገጹን ያሳያል። ሰዎች ደግሞ በሚያሳዝን ሁኔታ እውነተኛ መልካቸውን ማየት አይወዱም። እነርሱ እኔ መስታወት እንድሆን ሳይሆን፣ የተሻለ መልክ እንዲኖራቸው የማደርግ ‘ሜካፕ’ እንድሆንላቸው ፈለጉ። ይህ ምሳሌያዊ አነጋገር፣ እውነተኛ ክርስትና ራሳችንንና ሌሎችን እንዳሉበት በማሳየት ለለውጥ የሚያነሳሳ እንጂ፣ ድክመትን የሚሸፋፍን እንዳልሆነ ያስረዳል።

«ውድ ወንድሜ ሰውን በስብከት ማገልገል የግድ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ መድረክ ላይ መቆም ብቻ አይደለም፣ ትልቁና ዋነኛው ሰውን በራስ ሕይወት መለወጥ ነው፡፡ ስለዚህ በሕይወትህ ለብዙዎች አብነት እንድትሆን እንጂ የግድ ስብከት አዘጋጅተህ መድረክ ላይ መቆም ብቻ አይጠበቅብህም፡፡ እንዲህ አይነት ሰው ከሆንክ ሰዎች ፊትህን ባዩት ጊዜ የዋህነትን፣ ሩህሩህነትን ይማራሉ፣ ንግግርህንም በሰሙ ጊዜ መንፈሰ ጠንካራነት፣ ታማኝነት፣ ፍፁምነትና ፍቅርን ያገኛሉ፡፡» (ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ - ከመንፈስ ነፃነት የተወሰደ)

#የመምህር_ግርማ_አገልግሎት_ታግዷል_ያልከው_ሰውዬ ደህና ነህ ግን!! ይሄው ከቦታው #ተመስገን ነው! የእግዚአብሔር ሥራ እንደሆነ መሰራቱ የግድ ነው፡፡ በቃ የግድ ነው! ሒዱ እንጅ ቁሙ አልተባልንማ!
+8
#የመምህር_ግርማ_አገልግሎት_ታግዷል_ያልከው_ሰውዬ ደህና ነህ ግን!! ይሄው ከቦታው #ተመስገን ነው! የእግዚአብሔር ሥራ እንደሆነ መሰራቱ የግድ ነው፡፡ በቃ የግድ ነው! ሒዱ እንጅ ቁሙ አልተባልንማ! በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ ሜሪላንድ በዛሬው እለት ማለትም እሑድ መሰከረም 25, 2018 ዓ.ም Sunday - October 5, 2025 በአሜሪካ ሜሪላንድ 16000 Croom Airport Road Upper Marlboro MD 20772 የተከናወነው የመልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ እና የመልአከ ኃይል መምህር ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ መንፈሳዊ አገልግሎት በልዑል እግዚአብሔር ፍቃድ በሰላም ተከናውኗል። አገልግሎታችን ብዙ ህዝበ ክርስቲያን በእግዚአብሔር ኃይል ለዘመናት ከተተበተቡበት ከመተተኛው፤ ከደብተራው ከጠንቋዩ ክፉ የዲያቢሎስ እስራት ብዙ ምዕመናን የተፈቱበት ዲያቢሎስ በዘመናችን ምን ያህል የጥፋት መረብ ዘርግቶ እንደሚራመድ ከቤተእግዚአብሔር ቤት ጀምሮ የራሱን የጥፋት መረብ በሰዎች እየዘረጋ እንዴት የክፋት የዘረኝነት፤ የአድመኝነት፤ የግፍ፤ የጥላቻ፤ የፍቅረነዋይ ስራውን እንደሚሰራ በጥልቀት የተረዳንበት ቅዱሱን ወንጌል በሰፊው የተማርንበት ልዩ መንፈሳዊ ጉባዔ ነው! በህዝቡም ጥያቄ መሰረት የማታ’ ጉባዔ እና ነገ ሰኞ መሰከረም 26, 2018 ዓ.ም Monday - October 6, 2025 ይቀጥላል። እናመሰግናለን በነጻ ማስታወቂያ የምትሰሩልን ሰዎች!

መዝሙረ ዳዊትን በርዕስ ጸሎት ወቅት እንዴት በአግባቡ እንጠቀም? መዝሙረ ዳዊት በአጋንንት ላይ ያለው የበላይነት! መዝሙረ ዳዊት + የርዕስ ጸሎት + ስግደት  https://youtu.be/u2HsItb-HeY?si=fiG0-GGFeQmiB_5J

በመናፍስት ውጊያ ወቅት ማወቅ የሚገቡን 3 መሰረታዊ ነጥቦች! አጋንንት ለክፋት ይተባበራሉ እኛ ግን ለመልካሙም አንመችም!! https://youtu.be/Rp24hiCQy5k

ይኼንን ጉድ ነው እሬቻ የሰላም የማንሰራራት እየተባለ የሚከበረው እባካችሁ ንቁ!! #እሬቻ #irreecha #irreechafestival https://youtu.be/pEEz1r5BX84?si=nJfXKD8_rOaj9KBo

ምቾትን ብቻ ዘወትር ስንፈልግ ይኼ ሁሉ ሆነብን እግዚአብሔር ይማረን!! ለማይረባ አዕምሮ ለምን ተላልፈን ተሰጠን? እውነተኛዋ ሃይማኖትና እምነት የትኛዋ ናት? https://youtu.be/5kciDXjYmKA?si=OBedO9H2FgiiKaPL

+ ተክለሃይማኖት ሆይ (24) + ከፀሐይ እና ከጨረቃ ሥነ ፀዳል ይልቅ + በክርስቶስ ሥነ ጸዳል ለተዋበው ፊትህ ሠላም እላለሁ + ቅዱስ አባት ሆይ + ትምህርትህ የተስፋፋ + ትሩፋትህ የተትረፈረፈ +
+  ተክለሃይማኖት ሆይ (24) +  ከፀሐይ እና ከጨረቃ ሥነ ፀዳል ይልቅ + በክርስቶስ ሥነ ጸዳል ለተዋበው ፊትህ   ሠላም እላለሁ +    ቅዱስ አባት ሆይ +   ትምህርትህ የተስፋፋ +   ትሩፋትህ የተትረፈረፈ +   ዮሐንስ የተባልክ አንተ ተክለሃይማኖት ነህ +   ስለዚህ የዓለም ሥራው ብዙ ስለሆነ +   ንጹሑ የትዕዛዛዝ ቃል ከድካም ያሳርፈኝ +   ከማዕሠረ ኃጢአት ይፍታኝ ።     / መልክአ ተክለሐይማኖት /  የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት ረድኤት በረከታቸው አይለየን 🙏🏾

ያላወቅንበት ነገር ግን ዘወትር ደግሞ የምንሰቃይበት የመናፍስቱ ጥቃት!! በሕይወታችን አሁኑኑ ማስተካከል ያሉብን ነገሮች!! ጴንጠው ደብተራና ጠንቋይ! #ጸሎት https://youtu.be/iyrOjBy3EjY