uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 389 підписників, посідаючи 5 582 місце в категорії Релігія і духовність та 2 199 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 389 підписників.

За останніми даними від 02 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 23, а за останні 24 години на -3, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 21.38%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 10.20% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 290 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 569 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 17.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 03 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 389
Підписники
-324 години
+207 днів
+2330 день
Архів дописів
#ምስካየ_ኅዙናን ( #ዴ_ሡልጣን_) (#ቤተ_ሳይዳ) መድኀኔ ዓለም ገዳም፡፡ ታቦቱ የሚነግሠውም በዓመት አንዴ ሚያዝያ 27ት ብቻ ነው፡፡ #ምስካየ_ኅዙናን ፠ ከ1895-ሚያዚያ 27 ቀን 1929 ዓ.ም. ዴር ሡልጣን (የንጉሥ ገዳም) ገዳም በሚል ስያሜ፡፡ ፠ ከሚያዚያ 27 ቀን 1929 ዓ.ም. - ነሐሴ 23 ቀን 1933 ዓ.ም. ‹‹በስደት ያለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን›› እየተባለ ይጠራ ነበር፡፡ ፠ ከሚያዚያ 27 ቀን 1940 ዓ.ም. እስካሁን፤ ምስካዬ ኅዙናን ገዳም እየተባለ ይጠራል፡፡ ፠ ምስካየ ኅዙናን፤ የስሙም ትርጓሜ ለተበደሉትና ላዘኑት ማረጋጊያ ማጽናኛ ማለት ነው፡፡ ምስካየ አመስከይ ተጠጋ አስጠጋ ከሚለው የተገኝ ሲሆን ያዘኑ የተከዙ የተጨነቁ መጠጊያ ለማለት ነው፡፡ ፠ ከግራኝ መሐመድ ወረራ በኋላ እስከ አፄ ዮሐንስና ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ድረስ በኢየሩሳሌም ያሉ ገዳሞቻችንን በቋሚነት የሚረዳቸው ባለመኖሩ አብዛኞቹን የግሪክ የአርመንና የግብጽ አብያተ ክርስቲያን ወሰዷቸው፤ አፄ ምኒልክ በ1895 ዓ.ም. ለኢየሩሳሌም ገዳማት የሚተዳደሩበት ቦታ ገዝተው ሕንፃ ሠርተው ሲሰጡ፤ መምህር ፈቃደ እግዚእ የተባሉ መነኵሴን በኢየሩሳሌም አለቅነት ሹመውና ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው እንዲሄዱ አድርገዋል፤ በወቅቱ የትራንስፖርት አቅርቦት ባለመኖሩ እስከ ጂቡቲ ድረስ በእግር ከዛ በኋላ በመርከብ ተጕዘው ኢየሩሳሌም ደርሰዋል፡፡ ታቦተ ሕጉም በዴር ሡልጣን መድኀኔ ዓለም ገዳም (የንጉሥ ገዳም) ለ34 ዓመታት ሲቀደስበት፥ ሲወደስበት ኖሯል፡፡ ፠ በ1928 ዓ.ም. ጣሊያን ኃይሏን አጠናክራ ሽንፈቷን ለመበቀል ኢትዮጵያን ስትወርር፤ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ቅዳሜ ሚያዚያ 24 ቀን 1928 ዓ.ም. ወደ ጅቡቲ በባቡር፤ ከዚያም በእንግሊዝ የጦር መርከብ ሚያዚያ 26 ቀን ከጅቡቲ ተነስተው ሚያዚያ 30 ቀን ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ደረሱ፡፡ በሰኔ ወር 1928 ዓ.ም. ደግሞ በእንግሊዝ የጦር መርከብ ተሳፍረው ከኢየሩሳሌም ወደ እንግሊዝ ሀገር በSouthhampton ወደብ አድርገው ወደ ለንደን ከተማ በባቡር ተጉዘው Waterloo station ደረሱ፡፡ ለጥቂት ቀናት ከሰነበቱ በኋላ፤ ስዊዘርላድ ውስጥ ጄኔቫ በሚገኘው፣ የመንግሥታቱ ማኅበር ስብሰባ ላይ ሰኔ 23 ቀን 1928 ዓ.ም. የኢጣሊያ መንግሥት በሀገራችንና ሕዝባችን ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍ በመዘርዘር አስረዱ፤ ነገር ግን ለአቤቱታቸው የመንግሥታቱ ማኅበር ምንም ዓይነት አቋምና እርምጃ አለመውሰዱ እንዳሳዘናቸው ‹‹እግዚአብሔርና ታሪክ ፍርዳችሁን ሲያስታውሱት ይኖራሉ›› በማለት ልብን የሚነካ ታሪካዊና ትንቢታዊ ንግግር አድርገው ወደ ኢንግላንድ ተመልሰው በ‹‹ባዝ›› ከተማ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የስደት ኑሯቸውን ቀጠሉ፡፡ ፠ ንጉሡም በማኅበሩ ላይ ተስፋ በመቁረጥ፤ ፊታቸውን ወደ አባቶቻቸው አምላክ በማዞር በጾምና በጸሎት ለመማፀን በማሰብ፤ እንዲሁም የሃይማኖት ችግር እንዳያገኘን የሚያድጉ ልጆቻችን የሃይማኖታቸውን መሠረት እንዳይለቁ በማለት በብፁዕ ዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ ፈቃድ ቀደም ሲል በአፄ ምኒሊክ ወደ ኢየሩሳሌም ዴር ሱልጣን ገዳም ተልኮ አገልግሎት እየሰጠ የነበረውን ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ከኢየሩሳለም ወደ እንግሊዝ እንዲላክላቸው፤ በጥር ወር 1929 ዓ.ም. አባ ሃና ጂማን ከእንግሊዝ ሀገር ወደ ኢየሩሳሌም ላኳቸው፤ አባ ሃና ጂማማ ታቦቱን ከሌሎች 4 መነኮሳት (መምህር ገ/ኢየሱስ፣ አባ ማርቆስ፣ አባ ኃይሌ ቡሩክ እና አባ ገ/ማርያም) ጋር በመሆን ወደ እንግሊዝ ይዘው ተመለሱ፡፡ ጽላቱም ንጉሡ በሚኖሩበት ቤት ሚያዚያ 27 ቀን 1929 ዓ.ም. ባዝ ከተማ ደርሶ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ፡፡ በዚህ ቤትም ስደተኞቹ የጸሎትና የቊርባን ሥርዓትን እየፈጸሙ፤ የሚማሩበትና የሚጽናኑበት ሆኖ ቆየ፤ ስሙም ‹‹በስደት ያለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን›› እየተባለ ይጠራ ነበር፡፡ ፠ በዓለም ጦርነት ኢጣልያ ከጀርመን ጎን ስትሰለፍ፤ እንግሊዝ አፄ ኀይለ ሥላሴን ለመርዳት ወሰነች፡፡ በሰኔ 17 ቀን 1932 ዓ.ም. ንጉሡን ወደ ግብጽ ከዚያም ወደ ሱዳን በመውሰድ፤ ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ለሚደረገው የጦር ዘመቻ ዝግጅት እንዲጀመር አደረገች፡፡ በሱዳን የነበሩ ብዙ ስደተኛ ኢትዮጵያን እንዲሁም ሌሎች ከኢትዮጵያ በመምጣት በካርቱም አስፈላጊውን የጦር፣ ልምምድና ዝግጅት ከተደረገ በኋላ፤ ከእንግሊዞች ጋር በመሆን ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ጦርነቱ ተጀመረ፡ ፡ አፄ ኀይለ ሥላሴም ሱዳን ከደረሱ ከ7 ወራት በኋላ ጥር 12 ቀን 1933 ዓ.ም. ከሱዳን ወደ ሃገራቸው ኢትዮጵያ ግዛት በመግባት ኦሜድላ ላይ የኢትዮጵያን ባንዲራ ሰቀሉ፡፡ ከዚያም በጎጃም ደብረ ማርቆስ አድርገው ወደ መሐል ሀገር (በወጡ በ5 ዓመታቸው ሚያዚያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም.) ወደ መናገሻ ከተማቸው አዲስ አበባ በመግባት በቤተ መንግሥታቸው ባንዲራችንን ሰቀሉ፡፡ ፠ በነሐሴ 23 ቀን 1933 ዓ.ም. እቴጌ መነን ወደ አዲስ አበባ በተመለሱ ቀንም አባ ኃይሌ ቡሩክ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ተመልሰው በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት (የአሁኑ የስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ) የጸሎት ቤት ተከፍቶለት እያጠኑና እየጠበቁ ከቆዩ በኋላ፤ ለተበደሉትና ላዘኑት ማረጋጊያ ፥ ለሕሙማን መጽናኛ እንዲሆን የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ተብሎ ተሰይሞ በቀድሞ ቤተ ሳይዳ ቀዳማዊ ኃይለ ሥለሴ ሆስፒታል /አሁን የካቲት 12 ሆስፒታል/ ተብሎ በሚጠራው ግቢ በሚያዚያ 27 ቀን 1935 ዓ.ም. ውስጥ ተተከለ፡፡ ፠ ሕመምተኛው በጸሎት በመፈወስ፤ ከሩቅም ሆነ ከቅርብ የሚሳለመው ሕዝብ ቊጥር እየተበራከተ በመምጣቱ ሕዝቡ ይበልጥ እንዲሳብና የቅዳሴ ፍቅር እንዲያድርበት በማለት በአባ ሐና መሪነት፥ በአባ ኃይሌ ቡሩክ ኃላፊነት ሌሎች አገልጋዮች ተቀጥረው ጸሎትና ቅዳሴው ጠቅላላው ሥነ ሥርዐቱ ሁሉ በስደት ሀገር አገልግሎት ይሰጥበት በነበረው በአማርኛ ተደረገ፤ ይህ ነገርም በመደበኛነት የቤተክርስቲያን ልሳኗ ግእዝ ከመሆኑ አንጻር በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥም ሆነ ውጭ ባሉት አባቶች ቅሬታ አስነሣ፡፡ ፠ ከአምስት ዓመት በኋላ ቀ/ኃ/ሥላሴ ቤተ ክርስቲያኑ አሁን በሚገኝበት ቦታ ላይ እንዲሠራ ሚያዚያ 27 ቀን 1940 ዓ.ም. የመሠረተ ድንጋይ አኖሩ፡፡ ቦታው ሲመረጥ በአካባቢው ያሉ ት/ቤቶችን (የተፈሪ መነኰንን፣ የእቴጌ መነን፣ የቀ/ኀ/ሥ ዩኒቨርሲቲ /አሁን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን/)ከግምት ውስጥ በማስገባት ተማሪዎች ከቀለም ትምህርታቸው ጎን ለጎን በጸሎትና ትምህርተ ሃይማኖታቸውን እንዲጠብቁ ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡ ፠ ሕንፃውም ለ2 ዓመት በፍጥነት ከተሠራ በኋላ ሚያዚያ 27 ቀን 1942 ዓ.ም. ተሠርቶ ተጠናቅቆ ቅዳሴ በቤቱ ተከበረ፤ በዋይዜማው ሚያዚያ 26 ቀን ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ የቤተ ክርስቲያኑ ቡራኬ ሥነ ሥርዓትና የሰዓታት ጸሎት እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት ሲካሄድ አደረ፡፡ ታቦቱም ከቤተ ሳይዳ (የካቲት 12) ሆስፒታል ግቢ ወጥቶ አዲስ ወደተሠራው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ገባ፡፡ ንጋት ላይ ልክ 12 ሰዓት ተኩል ላይ አፄ ኃ/ሥላሴ እቴጌ መነንና ንጉሣውያን ቤተሰቦች እንደደረሱ እና ብዙ ምዕመናን በተሰበሰቡበት የቅዳሴው ሥነ ሥርዓት ተጀመረ፡፡ በዕለቱም የቅዳሴው ሥነ ሥርዓት የተመራው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ፣ አቡነ ቴዎፍሎስና፣ አቡነ ጢሞቴዎስ ነበር፡፡ ከቅዳሴውም በኋላ የገዳሙ አስተዳዳሪ የነበሩት አባ ሃና የታቦቱን

እንኳን ለበዓለ ትንሣኤ እና #ሚያዝያ_23_በዓለ_ክላሌሁ_ለሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ በሰላም አደረሳቹህ 👉👉#ሥርዓተ_ማኀሌቱን ሰሙነ ፋሲካ ስለሆን እንደ #የደብሩ_ይትባህል እያጣቀሳቹህ እንድጠጠቀሙ የበዓለ #ትንሣኤን እና #የቅዱስ_ጊዮርጊስን ሥርዓተ ማኀሌት እነሆ ብለናን፡፡ #እስከ_ዳግም_ትንሣዔ_ድረስ_መልክ_አይደረስም! #ሚያዝያ 23 --- ቀዳም ሥዑር ላይ ስላዋለ በዓሉ እንደ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያሉ አድባራት ሐሙስ(በ28) የሚያከበሩት ሲሆን እንዲሁ ደግሞ እሮብም(በ27) የሚያከብሩት አድባራት አሉ፡፡ #በዱባይ_ራስ_አልኬማም ዐርብ ይከበራል (29) ※※※※ #ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡፡ ※እናቱ ቴዎብስታ ስትባል አባቱ እንጣስዮስ ይባላል፡፡ አባቱ ባረፈ ጊዜ መስፋን ነበርና የእርሱን ሹመትን ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ሄደ፤ ሰዎችን ጣዖት አቁም በግድ እንደሚየስመልክ ባየ ጊዜ ፤ ባሮቹን ነጻ አውጥቶ ገንዘቡንም ለምስኪኖችና ለድኀች ሰጠ ንጉሡም ከእርሱ ጋር እንዲተባብር ቢያባብለው እና ቃል ኪዳን ቢገባለት ቅዱስ ጊየርጊስ አልተቀበለውም ፡፡ ※ለመስማት የሚያስጨንቅ መከራን እና ስቃይን አደረሰበት ጌታችን ግን መልሶ ያጸናዋል ቊስሉንም ያድንለት ነበር ፡፡ ※ጌታችን ለቅዱስ ጊየርጊስ 3 ጊዜ እንደሚሞት እርሱም እንደሚያስነሳው በአራተኛውም የምስክርነት አክሊልን እንደሚቀበል ነገረው ፤ ስሙ በዓለም ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ በተጋድሎና መከራ በመቀበልም ጽኑዕ በሆነ ሥቃይም ሰባት ዓመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚያገለግሉት ነገርው ፤ ቃል ኪዳንንም ሰጠው ፡፡ ※ ንጉሡ አትናስዮስ በሚባል ታላቅ ሥረየኛ መርዘ አስበጥብጦ እና ክፉ አስማትን አስርቶ ቢሰጠው ቅዱስ ጊያርጊስን ምንም ሳያገኝው ቀረ ፤ ሥርየኛውም ይህን አይቶ በኢየሱስ ክርስቶስ አሞኖ ሰማዕትነትን ተቀብሎ ሞቷል፡፡ከእርሱም ጋር #ሠላሳ ሺህ የሚሆኑ ሰዎች አብረው የሕይወት አክሊልን ተቀብለው በሰማዕትነትን ዐረፈዋል፡፡ ※ በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ የተቀመጡባቸውን የእንጨት ወንበሮች እንዲአብቡና እንዲበቅሉ አድርግ ቢሉት በጾሎቱ አድርጎ አሳያችው ይህንንም አይተው እጅግ ብዙ አህዛብ በአምላካችን አምነዋል፡፡ ※ ብዙ መከራንም አደረሱበት በጐድጓዳ በረት ምጣድ ውስጥ አኑርው አበሰሉት ፤ እቃ ጥለው አሳርረው ሥጋውንና ዐጥንቱን ፈጭተው አመድ አድረገው በተኑት ፡፡ ጌታችንም ነፍሱን ከሥጋው መልሶ ዳግም አስነሳው ወደ እነርሱም ተመልሶ በጌታችን ስም ሰበካቸው ይህንንም አይተው ቁጥር የሌላቸው አሕዛብ በጌታችን አምነው ሰማዕታት ሆኑ፡፡ ※ ነገሥታቱም ሙታኖችን ብታስነሳ በአምላክህ እናምናለን አሉ ፤በጸሎቱ ሙታኖችም አስነሳላቸው በጌታቸንም ስም አምነው በእርሱ ስም አስተማሩ ጥምቀትንም ተቀበሉ ፡፡የቀሩት ነገሥታት ግን ሰይጣናትን ነው ያሳየኸን ብለው ተከራከሩ ፡፡ ※ ከአንዲት እምበለት ቤት ተቀምጦ ምግብ ልትፈልግለት ሄዳ በተመለሰች ጊዜ ቤቷ ላይ ተአምር አየች ፤ የክርስቲያኖች አምላክ በሰው ተመስሎ እኔ ጋር መጣ ብትል ቅዱስ ጊየርጊስም #_እኔ_አምላክ_አይደለሁም_የአምላክ_ባርያ_ነኝ እነጂ አላት፡፡ የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምናለሁ አለችው ልጇንም በመስቀል ምልክት አማትቦበት ከዕውርነት አድኖታል ፡ ※ ንጉሡም ተአምር ማድረጉን በሰማ ጊዜ በመንኰራኵርም ፈጨው ከከተማ ውጪ ወስደው ጣሉት ከሞትም ተነሣ ተመለሶም ወደ ነገሥታቱ ሄደ ፡፡ንጉሡም አድንቆ ይለምንው ጀመር በመንግሥቱ ላይ ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስ እየዘበት ነገ ጠዋት ለአማልክቶች እሰዋለሁ ብሎት አደረ ፡፡ በሚጸልይበትም ጊዜ የንጉሡ ሚስት ሰምታ ጠየቀችው እርሱም ስለ ጌታችን አስተምራት አመነች ፡፡ በማግሥቱም ንጉሡ ሰውን ሰብስቦ እንደሚጠብቀውና እውነት መስሎ በታያት ጊዜ አዘነች ፡፡እርሱም ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት ከዚያም ወደ አጵሎን (ጣዖቱ) ሂድ ወደ እኔም እንዲመጣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እዘዘው አለው ፡፡ ልጁም ድኖ ቅዱሱ እንዳለው ሄዶ አዘዘው ፡፡ በጣዖቱም የነበረው እርኩስ መንፈስ ወጥቶ እኔ ሰውን የማስት እንጅ አምላክ አይደለሁም አለው ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ምድር ትውጠው ዘንድ አዘዛት ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋር አጠፋቸውን ንጉሡም ከወገኖቹ ጋር አፈረ፡፡ ※ ንጉሡም ሚስቱ በጌታችን እንዳመነች ባወቀ ጊዜ በመጋዝ አሰነጠቃት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች፡፡ ※ ነገሥታቱ ኀፍረት እንዳይጨመርባቸው ለንጉሡ በሰይፋ እንቁረጠው ብለው ጻፉለት እርሱም አዘዘ ፡፡ ድል አድራጊው ጊዮርጊስም ከሰማይ እሳት ወርዶ ሰባውን ነገሥታት ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያን ወገኖች ጸጥ ይል ዘንድ ለመነ ፤ አሣቱም መጥቶ ወዲያውኑ አጠፋቸው፡፡ ※ጌታችን ተገልጾለት እጅግ ብዙ ቃል ኪዳንን ሰጠው ፤ መታሰቢያህን የሚያደርግ ኃጢያቱን እደመስሳለሁ በመከራ ውስጥም ያለ በባሕርም ሆነ በየብስ በደዌም ሆነ በሕማም ያለ በስምህ የሚለምነኘን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለው ይህንንም ጌታችን ተናግሮ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ፡፡ ※ በስተ መጨረሻም ራሱን ዘንበል አድርጎ በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም አክሊላትን ተቀበለ ፡፡ አገልጋዮቹም የቀረውን ሥጋውን ወስደው በልብስ ጠቀልልው ወደ ሀገሩ ልዳ ወሰዱት ፡፡ ቤተ ክርስቲያንንም ሰርተው በውስጥዋ አኖሩት ከእርሱም ቊጥር የሌላቸው ብዙዎዋች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ ወስብሐት ለእግዚአብሔር የቅዱስ ጊዮርጊስ ምልጃ አይለየን ከመ ሀሊብ ዘዕጐልት ፤ ወከመ ወይን ዘገነት፤ ይትዕም ስምከ ጊዮርጊስ ሰማዕት፡፡ #ኮከበ ክብር፥ *ሊቀ ሰማዕታት፥ *መክብበ ሰማዕታት፥ *የፋርስና የቤሩት ኮከብ፥ *የልዳ ፀሐይ፥ *የኢትዮጵያ ገበዝ፥ *ባለ ፀዓዳ ፈረስ፥ *፸ ነገሥታትን ድል ያደረገ፥ *በሕይወቱ ክርስትናን ያስፋፋ፥ በዕረፍቱ ክርስቶስን የሰበከ፥ ከዕረፍቱ በኋላ ዛሬን ጨምሮ ፈጥኖ የሚራዳ፥ *፫ት ጊዜ ሞቶ ፫ት ጊዜ የተነሣ፥ *፯ት አክሊላትን የተቀናጀ፤ *እመቤታችንን በጣም ስለሚወድ ስሙ ከስሟ፥ ዝክሩ ከዝክሯ፥ ፍልሰቱ ከፍልሰቷ ጋር የተባበረ እንዲኾን ያደረገችለት፤ #ኀያል መስተጋድል ኀያል ኮከበ ክብር፤ ኀያል ገባሬ ተአምር፤ ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር፡፡ #በእንተ ጊዮርጊስ ፍቁርከ (ሰማዕትከ፥ ምዕመንከ)፤ ምህላነ ስማዕ በዕዝንከ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

#ሰሙነ_ፋሲካ (#ከትንሣኤ_እስከ_ዳግም_ትንሣኤ) (ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ) ከትንሣኤ እሑድ ቀጥለው ያሉት ዕለታት ሰሙነ ፋሲካ ወይም ትንሣኤ እየተባሉ የየራሳቸው ምሥጢራዊ ስያሜ አላቸው፡፡ ይኸውም፡- ✞ #ሰኞ፤ #ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡ ጌታችን በሞትና ትንሣኤው ነፍሳትን ከሲኦል አውጥቶ ወደ ገነት አሻግሮ ለማስገባቱ መታሰቢያ ሆና «ፀአተ ሲኦል ማዕዶት» ትባላለች፡፡ ዮሐ. 19-18 ሮሜ. 5-10-17 የዳግም ትንሣኤው ማግሥት ያለችው ግን ገበሬው፤ ወንዶቹ እርሻ ቁፋሮውን፣ ንግዱን፣ ተግባረ እዱን ሁሉ ሴቶቹ ወፍጮውን፣ ፈትሉን፣ ስፌቱን የሚጀምሩባት ዕለት ስለሆነች «እጅ ማሟሻ» ሰኞ ትባላለች፡፡ ✞ #ማክሰኞ፤ #ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29 የትንሣኤው ዕለት እሑድ ማታ ጌታችን በዝግ ቤት ገብቶ ለሐዋርያት ሲገለጽ ቶማስ ሐዋርያ አልነበረም ኋላ ከሔደበት ሲመጣ ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሣኤውን ቢነግሩት እኔ ሳላይ አላምንም በማለቱ በዚህ ጥያቄው መሠረት በሳምንቱ ጌታችን በድጋሚ ስለተገለጸ ለዚህ መገለጹ መታሰቢያ ሆና ዕለቲቱ «በቶማስ» ተሰየመች፡፡ ዮሐ. 20-24-30 ✞ #ረቡዕ፤ #አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ ከሞተና ከተቀበረ አራት ቀን በኋላ ከመቃብር ጠርቶ ላሥነሣው፣ አላዓዛር መታሰቢያ የእርሱንም ተነሥቶ በማየት በጌታችን ብዙ ሕዝብ ስለአመነበት ቀኒቱ «አላዓዛር» ተብላ ትታሰባለች፡፡ ዮሐ. 11-38-46 ✞ #ኀሙስ፤ #አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ የአዳም ተስፋው ተፈጽሞለት ከነልጅ ልጆቹ ወደቀደመ የገነት ክብሩ ለመግባቱ መታሰቢያ ሆና «የአዳም ኀሙስ» ተብላ ይኸው ትከበራለች፡፡ ሉቃ. 24-25-49 ✞ #ዐርብ፤ #ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በክርስቶስ ደም ተዋጅታ በተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዐርብ «ቤተ ክርስቲያን» ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ. 26-26-29 የሐ. ሥራ. 20-28 በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡ ✞ #ቅዳሜ፤ #ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ቀዳሚት ሕዝቡ ከአንዳንዱ በስተቀር ገበያ እንኳን ስለማይገበይባት «የቁራ ገበያ» የገበያ ጥፊያ ስትባል በቤተ ክርስቲያን ግን በዘመነ ሥጋዌው በገንዘባቸውና ጉልበታቸው ለአገለገሉት በስቅለቱ ዋይ ዋይ እያሉ እስከ ቀራንዮ ለተከተሉት፣ የትንሣኤው ዕለት ገና ከሌሊቱ ወደ መቃብሩ ሽቱና አበባ ይዘው በመገሥገሣቸው ትንሣኤው ከሁሉ ቀድሞ ለተገለጸላቸው ቅዱሳት አእንስት መልካም መታሰቢያ ሆና «አእንስት» ተብላ ትጠራለች፡፡ ሉቃ. 23-27-33፣ 24-1-01፣ ማቴ. 25-1-11 ✞ #እሑድ፤ #ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት) + + + መልካም በዓል!!! + + + /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

#ሰሙነ_ፋሲካ (#ከትንሣኤ_እስከ_ዳግም_ትንሣኤ) (ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ) ከትንሣኤ እሑድ ቀጥለው ያሉት ዕለታት ሰሙነ ፋሲካ ወይም ትንሣኤ እየተባሉ የየራሳቸው ምሥጢራዊ ስያሜ አላቸው፡፡ ይኸውም፡- ✞ #ሰኞ፤ #ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡ ጌታችን በሞትና ትንሣኤው ነፍሳትን ከሲኦል አውጥቶ ወደ ገነት አሻግሮ ለማስገባቱ መታሰቢያ ሆና «ፀአተ ሲኦል ማዕዶት» ትባላለች፡፡ ዮሐ. 19-18 ሮሜ. 5-10-17 የዳግም ትንሣኤው ማግሥት ያለችው ግን ገበሬው፤ ወንዶቹ እርሻ ቁፋሮውን፣ ንግዱን፣ ተግባረ እዱን ሁሉ ሴቶቹ ወፍጮውን፣ ፈትሉን፣ ስፌቱን የሚጀምሩባት ዕለት ስለሆነች «እጅ ማሟሻ» ሰኞ ትባላለች፡፡ ✞ #ማክሰኞ፤ #ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29 የትንሣኤው ዕለት እሑድ ማታ ጌታችን በዝግ ቤት ገብቶ ለሐዋርያት ሲገለጽ ቶማስ ሐዋርያ አልነበረም ኋላ ከሔደበት ሲመጣ ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሣኤውን ቢነግሩት እኔ ሳላይ አላምንም በማለቱ በዚህ ጥያቄው መሠረት በሳምንቱ ጌታችን በድጋሚ ስለተገለጸ ለዚህ መገለጹ መታሰቢያ ሆና ዕለቲቱ «በቶማስ» ተሰየመች፡፡ ዮሐ. 20-24-30 ✞ #ረቡዕ፤ #አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ ከሞተና ከተቀበረ አራት ቀን በኋላ ከመቃብር ጠርቶ ላሥነሣው፣ አላዓዛር መታሰቢያ የእርሱንም ተነሥቶ በማየት በጌታችን ብዙ ሕዝብ ስለአመነበት ቀኒቱ «አላዓዛር» ተብላ ትታሰባለች፡፡ ዮሐ. 11-38-46 ✞ #ኀሙስ፤ #አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ የአዳም ተስፋው ተፈጽሞለት ከነልጅ ልጆቹ ወደቀደመ የገነት ክብሩ ለመግባቱ መታሰቢያ ሆና «የአዳም ኀሙስ» ተብላ ይኸው ትከበራለች፡፡ ሉቃ. 24-25-49 ✞ #ዐርብ፤ #ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በክርስቶስ ደም ተዋጅታ በተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዐርብ «ቤተ ክርስቲያን» ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ. 26-26-29 የሐ. ሥራ. 20-28 በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡ ✞ #ቅዳሜ፤ #ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ቀዳሚት ሕዝቡ ከአንዳንዱ በስተቀር ገበያ እንኳን ስለማይገበይባት «የቁራ ገበያ» የገበያ ጥፊያ ስትባል በቤተ ክርስቲያን ግን በዘመነ ሥጋዌው በገንዘባቸውና ጉልበታቸው ለአገለገሉት በስቅለቱ ዋይ ዋይ እያሉ እስከ ቀራንዮ ለተከተሉት፣ የትንሣኤው ዕለት ገና ከሌሊቱ ወደ መቃብሩ ሽቱና አበባ ይዘው በመገሥገሣቸው ትንሣኤው ከሁሉ ቀድሞ ለተገለጸላቸው ቅዱሳት አእንስት መልካም መታሰቢያ ሆና «አእንስት» ተብላ ትጠራለች፡፡ ሉቃ. 23-27-33፣ 24-1-01፣ ማቴ. 25-1-11 ✞ #እሑድ፤ #ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት) /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

#ሚያዝያ_23_በዓለ_ክላሌሁ_ለሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡፡ ኦ ፍጡነ ረድኤት … ብለን እኛ ኢትዮጵያውያን በእምነት ኾነው ስንጠራው፤ ከዐይን ጥቅሻና ከዐውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥኖ የሚደርስልን የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ የበዓለ ዕረፍቱ ክብረ በዓል ነው፡፡ #ሚያዝያ 23 --- ቀዳም ሥዑር ላይ ስላዋለ በዓሉ እንደ ገነተ ጽጌ ቀዱስ ጊዮርጊስ ያሉ አድባራት ሐሙስ(በ28) የሚያከበሩት ሲሆን እነዲሁ ደግሞ እሮብም(በ27) የሚያከብሩት አድባራት አሉ፡፡ #ሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡፡ ※እናቱ ቴዎብስታ ስትባል አባቱ እንጣስዮስ ይባላል፡፡ አባቱ ባረፈ ጊዜ መስፋን ነበርና የእርሱን ሹመትን ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ሄደ፤ ሰዎችን ጣዖት አቁም በግድ እንደሚየስመልክ ባየ ጊዜ ፤ ባሮቹን ነጻ አውጥቶ ገንዘቡንም ለምስኪኖችና ለድኀች ሰጠ ንጉሡም ከእርሱ ጋር እንዲተባብር ቢያባብለው እና ቃል ኪዳን ቢገባለት ቅዱስ ጊየርጊስ አልተቀበለውም ፡፡ ※ለመስማት የሚያስጨንቅ መከራን እና ስቃይን አደረሰበት ጌታችን ግን መልሶ ያጸናዋል ቊስሉንም ያድንለት ነበር ፡፡ ※ጌታችን ለቅዱስ ጊየርጊስ 3 ጊዜ እንደሚሞት እርሱም እንደሚያስነሳው በአራተኛውም የምስክርነት አክሊልን እንደሚቀበል ነገረው ፤ ስሙ በዓለም ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ በተጋድሎና መከራ በመቀበልም ጽኑዕ በሆነ ሥቃይም ሰባት ዓመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚያገለግሉት ነገርው ፤ ቃል ኪዳንንም ሰጠው ፡፡ ※ ንጉሡ አትናስዮስ በሚባል ታላቅ ሥረየኛ መርዘ አስበጥብጦ እና ክፉ አስማትን አስርቶ ቢሰጠው ቅዱስ ጊያርጊስን ምንም ሳያገኝው ቀረ ፤ ሥርየኛውም ይህን አይቶ በኢየሱስ ክርስቶስ አሞኖ ሰማዕትነትን ተቀብሎ ሞቷል፡፡ከእርሱም ጋር #ሠላሳ ሺህ የሚሆኑ ሰዎች አብረው የሕይወት አክሊልን ተቀብለው በሰማዕትነትን ዐረፈዋል፡፡ ※ በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ የተቀመጡባቸውን የእንጨት ወንበሮች እንዲአብቡና እንዲበቅሉ አድርግ ቢሉት በጾሎቱ አድርጎ አሳያችው ይህንንም አይተው እጅግ ብዙ አህዛብ በአምላካችን አምነዋል፡፡ ※ ብዙ መከራንም አደረሱበት በጐድጓዳ በረት ምጣድ ውስጥ አኑርው አበሰሉት ፤ እቃ ጥለው አሳርረው ሥጋውንና ዐጥንቱን ፈጭተው አመድ አድረገው በተኑት ፡፡ ጌታችንም ነፍሱን ከሥጋው መልሶ ዳግም አስነሳው ወደ እነርሱም ተመልሶ በጌታችን ስም ሰበካቸው ይህንንም አይተው ቁጥር የሌላቸው አሕዛብ በጌታችን አምነው ሰማዕታት ሆኑ፡፡ ※ ነገሥታቱም ሙታኖችን ብታስነሳ በአምላክህ እናምናለን አሉ ፤በጸሎቱ ሙታኖችም አስነሳላቸው በጌታቸንም ስም አምነው በእርሱ ስም አስተማሩ ጥምቀትንም ተቀበሉ ፡፡የቀሩት ነገሥታት ግን ሰይጣናትን ነው ያሳየኸን ብለው ተከራከሩ ፡፡ ※ ከአንዲት እምበለት ቤት ተቀምጦ ምግብ ልትፈልግለት ሄዳ በተመለሰች ጊዜ ቤቷ ላይ ተአምር አየች ፤ የክርስቲያኖች አምላክ በሰው ተመስሎ እኔ ጋር መጣ ብትል ቅዱስ ጊየርጊስም #_እኔ_አምላክ_አይደለሁም_የአምላክ_ባርያ_ነኝ እነጂ አላት፡፡ የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምናለሁ አለችው ልጇንም በመስቀል ምልክት አማትቦበት ከዕውርነት አድኖታል ፡ ※ ንጉሡም ተአምር ማድረጉን በሰማ ጊዜ በመንኰራኵርም ፈጨው ከከተማ ውጪ ወስደው ጣሉት ከሞትም ተነሣ ተመለሶም ወደ ነገሥታቱ ሄደ ፡፡ንጉሡም አድንቆ ይለምንው ጀመር በመንግሥቱ ላይ ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስ እየዘበት ነገ ጠዋት ለአማልክቶች እሰዋለሁ ብሎት አደረ ፡፡ በሚጸልይበትም ጊዜ የንጉሡ ሚስት ሰምታ ጠየቀችው እርሱም ስለ ጌታችን አስተምራት አመነች ፡፡ በማግሥቱም ንጉሡ ሰውን ሰብስቦ እንደሚጠብቀውና እውነት መስሎ በታያት ጊዜ አዘነች ፡፡እርሱም ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት ከዚያም ወደ አጵሎን (ጣዖቱ) ሂድ ወደ እኔም እንዲመጣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እዘዘው አለው ፡፡ ልጁም ድኖ ቅዱሱ እንዳለው ሄዶ አዘዘው ፡፡ በጣዖቱም የነበረው እርኩስ መንፈስ ወጥቶ እኔ ሰውን የማስት እንጅ አምላክ አይደለሁም አለው ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ምድር ትውጠው ዘንድ አዘዛት ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋር አጠፋቸውን ንጉሡም ከወገኖቹ ጋር አፈረ፡፡ ※ ንጉሡም ሚስቱ በጌታችን እንዳመነች ባወቀ ጊዜ በመጋዝ አሰነጠቃት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች፡፡ ※ ነገሥታቱ ኀፍረት እንዳይጨመርባቸው ለንጉሡ በሰይፋ እንቁረጠው ብለው ጻፉለት እርሱም አዘዘ ፡፡ ድል አድራጊው ጊዮርጊስም ከሰማይ እሳት ወርዶ ሰባውን ነገሥታት ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያን ወገኖች ጸጥ ይል ዘንድ ለመነ ፤ አሣቱም መጥቶ ወዲያውኑ አጠፋቸው፡፡ ※ጌታችን ተገልጾለት እጅግ ብዙ ቃል ኪዳንን ሰጠው ፤ መታሰቢያህን የሚያደርግ ኃጢያቱን እደመስሳለሁ በመከራ ውስጥም ያለ በባሕርም ሆነ በየብስ በደዌም ሆነ በሕማም ያለ በስምህ የሚለምነኘን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለው ይህንንም ጌታችን ተናግሮ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ፡፡ ※ በስተ መጨረሻም ራሱን ዘንበል አድርጎ በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም አክሊላትን ተቀበለ ፡፡ አገልጋዮቹም የቀረውን ሥጋውን ወስደው በልብስ ጠቀልልው ወደ ሀገሩ ልዳ ወሰዱት ፡፡ ቤተ ክርስቲያንንም ሰርተው በውስጥዋ አኖሩት ከእርሱም ቊጥር የሌላቸው ብዙዎዋች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ ወስብሐት ለእግዚአብሔር የቅዱስ ጊዮርጊስ ምልጃ አይለየን ከመ ሀሊብ ዘዕጐልት ፤ ወከመ ወይን ዘገነት፤ ይትዕም ስምከ ጊዮርጊስ ሰማዕት፡፡ #ኮከበ ክብር፥ *ሊቀ ሰማዕታት፥ *መክብበ ሰማዕታት፥ *የፋርስና የቤሩት ኮከብ፥ *የልዳ ፀሐይ፥ *የኢትዮጵያ ገበዝ፥ *ባለ ፀዓዳ ፈረስ፥ *፸ ነገሥታትን ድል ያደረገ፥ *በሕይወቱ ክርስትናን ያስፋፋ፥ በዕረፍቱ ክርስቶስን የሰበከ፥ ከዕረፍቱ በኋላ ዛሬን ጨምሮ ፈጥኖ የሚራዳ፥ *፫ት ጊዜ ሞቶ ፫ት ጊዜ የተነሣ፥ *፯ት አክሊላትን የተቀናጀ፤ *እመቤታችንን በጣም ስለሚወድ ስሙ ከስሟ፥ ዝክሩ ከዝክሯ፥ ፍልሰቱ ከፍልሰቷ ጋር የተባበረ እንዲኾን ያደረገችለት፤ #ኀያል መስተጋድል ኀያል ኮከበ ክብር፤ ኀያል ገባሬ ተአምር፤ ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር፡፡ #በእንተ ጊዮርጊስ ፍቁርከ (ሰማዕትከ፥ ምዕመንከ)፤ ምህላነ ስማዕ በዕዝንከ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #share

ት ትምህርት ቤት, [17.04.20 22:08] #ክርስቶስ_ተንሥአ_እሙታን (ክርስቶስ ከሙታን መካከል ተነሣ) #በዐቢይ_ኀይል_ወሥልጣን (በታላቅ ኀይልና ሥልጣን)፤ #አሰሮ_ለሰይጣን_ (ሰይጣንን አሰረው) #አግዐዞ_ለአዳም(አዳምን ነጻ አወጣው)፤ #ሰላም (ሰላም ፍቅርና አንድነት) እምይእዜሰ (ከዛሬ ጀምሮ) #ኮነ (ኾነ) #ፍሥሐ_ወሰላም (ሰላምና ደስታ ኾነ)፡፡ ፠ በማዕረግ ከፍ ያለው ካህንም፤ ከላይ ያለውን ዐውጆ ሲያበቃ «#ነዋ_መስቀለ_ሰላም» እያለ መስቀል ሲያሳልም ካህናትና ሕዝቡም «#ዘተሰቅለ_ቦቱ_መድኀኔ_ዓለም» እያሉ ይሳለማሉ፡፡ በማዕረግ ከፍ ያለው ካህንም፤ «#እግዚአብሔር_ይፍታ» ይላል፡፡ ግብረ ሕማማት ሲነበብበት ከሰነበተው ጠበልም ይረጫል፡፡ የተረፈውንም ጠበል ሕዝቡ ለበረከት ወደየቤቱ ይወስደዋል፡፡ ፠ ከዚያም ልኡካኑ ለቅዳሴ ይዘጋጃሉ፤ ሊቃውንት ደባትር መዘምራንም ምስማክ፥ መወድሱን ካዜሙ በኋላ በመቋሚያ ይዘምሙታል፡፡ አያይዞም በዓመት ፫ት ጊዜ የሚዘመረውን «ይትፌሣሕ ሰማይ …» የተባለውን መዝሙር ቃኝተው ከዘመሙ በኋላ «ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ፤ ተኀፂባ በደመ ክርስቶስ = ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካውን ታደርጋለች፡፡» እያሉ ይጸነጽላሉ፡፡ አያይዘውም የመዝሙሩን ሰላም (ፍጹመ ንጉሠ ኰነንዎ …)ን ይጸፋሉ፡፡ ፠ ወዲያው መንፈቀ ሌሊት ሲሆን ቅዳሴ ተቀድሶ ይቈረባል፡፡ ከዚያም ዕጣነ ሞገር = በዕጣን ፈንታ ቅኔው ተቁሞ ሠርሖተ ሕዝብ = የሕዝብ ስንብት ከሆነ በኋላ ለመፈሰክ ሕዝቡ ወደየ ቤቱ ይሔዳል፡፡ #የትንሣኤ_አከባበር_በዕለቱ ፠ ሕዝቡ በየቤቱ፣ ካህናቱም ከቤተ ክርስቲያን በየአካባቢው ባህል በተለይ አክፋዮች መጀመሪያ ቅባት አጥቶ የሰነበተ ሆድ እንዲለሰልስ የተሞቀ የተልባ ጭልቃ ይጠጣና የሹሮ ወጥ በቅቤ፣ በአይብ፣ የበረታም በዶሮ ወጥ፣ ወይም በበግና በከብት ሥጋ ወጥ ይገድፋል፡፡ ፠ በእርጎ፣ በአይብ የተደራረበ እንጀራ በግፍልፍል የሚገድፉም አሉ፡፡ በአንዳንድ የሰሜኑ ሀገራችን ደግሞ የተልባ፣ የኑግና የሱፍ ጭልቃ ከማር ጋር ታሽቶ ከተጠጣ በኋላ በእርጎ፣ በአይብ፣ በወተት፣ በቅቤና ድልህ በተቀባ እንጀራ ይገድፋሉ፡፡ ፠ በዋልድባ ገዳም ከዓመት ዓመት ምግቡ ቋርፍ ብቻ መሆኑ ይታወቃል፤ ነገር ግን ለትንሳኤ በዓል ከሃገራችን ካሉ ቦታዎች በተለየ ሁኔታ በዓሳ ይገድፋሉ፤ ዓሳው ሲዘጋጅም ሙሉ ለሙሉ ሆድ ዕቃው ሳይወጣ ተወቅጦ ነው፡፡ ፠ ሊነጋጋ ሲልም ከጾሙ አጋማሽ ጀምሮ ወንዱ ለእርድ የሚሆነውን ሰንጋውን፣ ሲቀልብ፣ በጉን ፍየሉን ሲሞክት ዶሮውን ሲመርጥ፣ ሲገዛ ሲለውጥ ሰንብቶ ነበርና በግልም በኅብረትም ያ ይታረዳል፡፡ ፠ ሴቶችም ቅቤውን ሲያነጥሩ፣ በርበሬውን ሲደልሁ፣ ለእንጀራና ዳቦ የሚሆነውን ዱቄት ሲያዘጋጁ ለጠላ የሚሆነውንም እኸል ሲያሰናዱ አይቡን በልዩ ልዩ ቅመም መጣጣ ሲያደርጉና ባዶ ማለትም ወገሚት የተባለውን በሽንኩርት፣ በጤና አዳም፣ ጣዕሙ እንዳይለወጥ ሲቀምሙ፤ እንደ መከለሻ፣ ጥቁር አዝሙድ የመሳሰሉትንም ሰንብተው ዝግጅቱ ተከናውኖ ነበር፡፡ ፠ ጧትም ይህ የመግደፊያ ዝግጅት በየቤታቸው ለሌላቸው ድኾች በየመንደሩ እየተዞረ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታላችሁ» እየተባለ ከሥጋውም፣ ከአይቡም፣ ከቅቤውም ከመጣጣሙም፣ ከእርጐውም ይታደላል፡፡ ፠ ከትንሣኤ እሑድ ጀምሮ እስከ ዳግም ትንሣኤ ድረስ ሕዝበ ክርስቲያኑ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታላችሁ» እየተባባለ በመጠራራት ዐብሮ ሲበላ ሲጠጣ ልዩ ልዩ ጨዋታ ሲጨዋወት ለንስሐ አባትና ለሽማግሌዎች፤ ለወላጅ አባትና እናት፤ ለወንድምና ለእኅት ለወዳጅ ዘመድም የአክፋይ ዳቦ፣ ወይም የሥጋ ወጥና የድሮ ወጥ፣ ግፍልፍል ሲወስድ ይሰነብታል፡፡ ፠ የቻለም ከትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሣኤ እየተገባባዘ በዓሉን በፍስሐና በሐሴት ሲያከብር ይከርማል፡፡ ‹‹ሕያው ተንሥአ እሙታን (ሕያው ከሙታን ተነሣ፡፡)›› /ጾመ ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ/ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡ \ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

እንኳን በሰላምና በጤና አደረሰን፥ አደረሳችሁ፡፡ #ፋሲካ_ፋሲካ_ፋሲካ፤ #ተዝካረ_ትንሣኤሁ_ለክርስቶስ፡፡ /ቅዱስ ያሬድ/ #ትንሣኤ_ትርጕም_በዓሉና_አከባበሩ_ (ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ) «ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡ መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግስ ሲሆን፡፡ «ትንሣኤ» ማለት = መነሣት፥ አነሣሥ፥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡ «ትንሣኤ» በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዓይነቱ ሲተረጐም ፭ት ክፍል አለው፡፡ ፩ኛ) «ትንሣኤ» ማለት ኅሊና ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት ተዘክሮተ እግዚአብሔር ነው፡፡ ፪ኛ) «ትንሣኤ» ማለት ልቡና ማለት ነው፡፡ የዚህም ምሥጢሩ ቃለ እግዘብሔርን መስማትና በንስሐ እየታደሱ በሕይወት መኖር ነው፡፡ ፫ኛ) «ትንሣኤ» ለጊዜው የሙታን በሥጋ መነሣት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ድጋሚ ሞት ይከተለዋል፡፡ ፬ኛ) «ትንሣኤ» የክርስቶስ በገዛ የባሕርይ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣት ነው፡፡ የዛሬው ትምህርታችንም ይህንን መሠረት ያደረገ ነው፡፡ ፭ኛው)ና የመጨረሻው «የትንሣኤ» ደረጃም የባሕርይ አምላክ የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን «ትንሣኤ» መሠረት ያደረገ «ትንሣኤ ዘጕባኤ» ነው፡፡ ይህም ከዓለም ኅልፈት በኋላ ሰው ሁሉ እንደየሥራው ለክብርና ለውርደት፥ ለጽድቅና ለኩነኔ በአንድነት የሚነሣው የዘለዓለም ትንሣኤ ይሆናል፡፡ ፠ ወደተነሣንበት ርዕስ ስንመለስ የትንሣኤ በዓል በቃሉም ምሥጢር በይዘቱም ስለሚመሳሰሉ ጥላው ምሳሌውም፣ ስለሆነ «ፋሲካ» ተብሎ ይጠራል፡፡ «#ፋሲካ_» ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ «ፌሳሕ» በጽርዕ (በግሪክኛ) «ስኻ» ይባላል፡፡ በግእዝና በዐማርኛ ፍሥሕ ዕድወት = ማዕዶት፣ በዓለ ናእት = የቂጣ በዓል፣ እየተቸኮለ የሚበላ መሥዋዕት፣ መሻገር፣ መሸጋገር ማለት ነው፡፡ በእንግሊዝኛ «ስኦቨር» ይሉታል፡፡ የዚህም ታሪካዊ መልእክቱ በዘመነ ኦሪት ይከበር የነበረው በዓለ ፋሲካ እስራኤል ዘሥጋ ከግብጽ የባርነት ቀንበር ወደነፃነት የተላለፉበት፣ ከከባድ ሐዘን ወደ ፍጹም ደሰታ የተሸጋገሩበት በዓል ነበር፡፡ በዚህ ኦሪታዊ ምሳሌ በዓል አሁን አማናዊው በዓል «ትንሣኤ» ተተክቶበታል፡፡  በዓለ ትንሣኤ በዘመነ ሐዲስ የምንገኝ እስራኤል ዘነፍስ የሆንን ምዕመናነ ክርስቶስ ትንሣኤውን የምናከብረው፤  በእርሱ ትንሣኤ ከኀጢአት፤ ወደ ጽድቅ፣  ከኀሳር ፥ ከውርደት፤ ወደክብር፣  ከጠላት ሰይጣን አገዛዝ፤ ወደ ዘለዓለማዊ ነፃነት፣  ከአደፈ፥ ከጐሰቆለ አሮጌ ሕይወት፤ ወደ ሐዲስ ሕይወት የተሻገርንበት ታላቅ መንፈሳዊ የነፃነት በዓል ነው፡፡ ስለዚህም እኛ ክርስቲያኖች የትንሣኤን በዓል በታላቅ ደስታና መንፈሳዊ ስሜት እናከብረዋለን፡፡ ስለዚህም ከበዓላት ሁሉ የበለጠ ሆኖ ይታያል፡፡ #የበዓሉ_አከባበር_«እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን»  መድኀኒታችን ሞትን በሞቱ ድል መትቶ፣ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ በሥልጣኑ የተነሣው በእለተ እሑድ፥መጋቢት 29፥ በ34 ዓ.ም እንደሆነ ታሪከ ቤተ ከርስቲያን ያስረዳል፡፡  የትንሣኤ በዓል መከበር የጀመረው በቅዱሳን ሐዋርያትና በሰብዐ አርድእት፣ ኋላም በየጊዜው በተነሡት ሊቃውንትና ምእመናን ነው፡፡ ድምቀቱና የአከባበር ሥርዐቱ ይበዛ ይቀነስ እንደሆን እንጂ መከበሩ ተቋርጦ አያውቅም፡፡ እንደ ዋልድባ፣ ማኅበረ ሥላሴ፣ ኢየሩሳሌም ባሉ ታላላቅ ገዳማት ደግሞ በዓሉ እጅግ በጣም በታላቅና በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ #የበዓሉ_አከባበር_ከዋይዜማው_ጀምሮ_እስከ_ሌሊት_የሚከተለውን_ይመስላል፤  በዋይዜማው ማታ በ2 ሰዓት «ለጸሎት ተሰብሰቡ» የሚል ደወል ድምፅ ይደወላል፡፡ እንደ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ባሉ ታላላቅ አድባራት የተጋብኦ ከበሮ ይመታል፡፡  ካህናቱ ዲያቆናቱና ምዕመናኑ ነጭ ልብስ ይልበሱ፤ ጧፍ ያብሩ፤ ዲያቆናት ጥላ ያጥሉ፡፡  በላይ ቤት አቋቋም በሚቆሙ፤ የነቢያት ጸሎት የለም  /በታች ቤት/፤ የነቢያት ጸሎት (ጸሎተ ሐና፣ ጸሎተ ሕዝቅያስ፣ ጸሎተ ምናሴ፣ ጸሎተ ዮናስ፣ ጸሎተ ዳንኤል፣ ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ፣ ጸሎተ ዕንባቆም፣ ጸሎተ ኢሳይያስ፣ ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም፣ ጸሎተ ዘካርያስ፣ ጸሎተ ስምዖን) ይድገሙ፡፡  ውዳሴ ማርያምንና ክስተተ አርያምን በዜማ ያድርሱ፡፡  ‹‹ተፈሥሒ ማርያም ለአዳም ፋሲካሁ›› የሚለውን ግጥማዊ የደስታ መዝሙር ይዘምራሉ፡፡  መልክአ ሥዕል ከትንሣኤ እስከ በዓለ ፶ ድረስ አይደረስም  እሰግድ ለኪ ብለህ ተዓምረ ማርያምና ተዓምረ ኢየሱስን አንብብ እንዳበቃ ጸሎተ አኰቴት ይደርሳል፡፡  ዲያቆኑ ነጭ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ፥ አክሊል ደፍቶ፥ የመጾር መስቀል ይዞ፥ እንደ እርሱ ነጭ ልብሰ ተክህኖ በለበሱ ደማቅ የጧፍ መብራት በሚያበሩና ድባብ ፥ ጃንጥላ በያዙ ሁለት ዲያቆናት በግራ በቀኝ ታጅቦ ከመቅደስ ብቅ ብሎ በቅድስት ይቆማል፡፡ (ይህም በጌታችን መቃብር በራስጌና በግርጌ በታዩት መላእክት ምሳሌ ነው፡፡ ዮሐ.20-12) ቀጥሎም በመዝሙረ ዳዊት /መዝ.፸፯፥፳፭/ ያለውን፤ ‹‹ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃሕ እምንዋም፤ ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን፤ ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ፡፡ (ትርጕም፤ እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ፤ የወይን ስካር እንደተወው ኀያል ሰውም፣ ጠላቱን በኋላው ገደለ፡፡» የሚለውን ምስባክ ይላል፤  ካህናቱና ሕዝቡ ከበሮ እየመቱና እያጨበጨቡ በእርጋታ እያጨበጨቡ የምስባኩን ተሰጥኦ ይመልሱ፡፡ ምስባኩንም በዲያቆኑ 2 ጊዜ በመላው ካህናትም 2 ጊዜ ለመጨረሻ ጊዜ ዲያቆኑም መላው ካህናትም አንድ ጊዜ ብለው 5 ጊዜ ይሆናል፡፡ 5,500 ዘመን ሲፈጸም በጌታችን ሞትና ትንሣኤ ዓለም ለመዳኑ ምሳሌያዊ ማስረጃ ነው፡፡  ቀጥሎም ካህኑ ትንሣኤውን የሚያበሥር ወንጌል ከማቴዎስ፣ ከማርቆስና ከሉቃስ አውጥቶ ያነባል፡፡ ከዮሐንስ ወንጌል ያለው የትንሣኤው ወንጌል ኋላ ለቅዳሴው ጊዜ ይቆያል፡፡ ዮሐ. 20፥1-9  በማስከተል ከሊቃውንት ደባትር መዘምራን የተመደበው መዘምር የዲያቆኑን መፆር መስቀል ይዞ «ትንሣኤከ ለእለ አመነ» የሚለውን እስመ ለዓለም ከቃኘ በኋላ ለበዓሉ ተስማሚ የሆነው 2 አርያም (ሃሌ ሉያ ለአብ፥… የሚለው) ተመርቶ በመቋሚያ ይዘመማል፤  በማስከተልም «ዮም ፍሥሐ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን፣ እስመ ተንሥአ ክርስቶስ እሙታን = ክርስቶስ ከሙታን ቀድሞ ተለይቶ ተነሥቷልና በሰንበተ ክርስቲያን ዛሬ ደስታ ሆነ፡፡...» የሚለውን አንገርጋሪ ያመለጥናል (ይመራል)፡፡ በግራ በቀኝ እየተነሣ መዘምራኑም ይዘምሙታል ይጸፉታል፤ ያለዝቡታል፤ ወዲያውም «ብርሃነከ ፈኑ፤ ለእለአመነ = ለአመነው ብርሃንህን ላክልን፡፡» የሚለውን እስመ ለዓለም እየወረቡ መብራት እያበሩ ዑደት ያደርጋሉ = ቤተ ክርስቲያኑን በውስጥ ይዞራሉ፡፡  በዚህ ጊዜ «በጨለማ የነበራችሁ ሕዝቦች ኑ የትንሣኤውን ብርሃን እዩ፣ ብርሃኑንም ወስዳችሁ የብርሃኑ ተካፋይ ሁኑ፡፡» እያለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስታዘጋጅ የሰነበተችውን ጧፍ ለምዕመናን እንዲያበሩ ታድላቸዋለች፡፡ ሕዝቦቹም ካህናቱን ተከትለው በታላቅ ደስታና ድምቀት ዑደት ያደርጋሉ፡፡ ፠ መዘምራኑና ካህናቱ ከዑደት ሲመለሱ «ይእቲ ማርያም» የተባለው የኪዳን ሰላም ይጸፋና ኪዳን ተደርሶ ሲያበቃ እንደ በማዕርግ ከፍ ያለው ካህን ዘለግ ባለ ድምፅ በንባብ የሚከተውን ፫ት ጊዜ ሲያውጅ ካህናቱና መዘምራኑም ይቀበሉታል፤ FINOTE HIWOT የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበ