uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 389 підписників, посідаючи 5 582 місце в категорії Релігія і духовність та 2 199 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 389 підписників.

За останніми даними від 02 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 23, а за останні 24 години на -3, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 21.38%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 10.20% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 290 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 569 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 17.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 03 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 389
Підписники
-324 години
+207 днів
+2330 день
Архів дописів
ለምን #ቀዳሚት_ሥዑር_ (#ሥዑር_ቅዳሜ) (የስቅለት ማግስት ) ላይ ቄጤማ ይታደላል ወይንም ይደረጋል ??? ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ይህቺ ቅዳሜ በእነዚህ ስሞች ትታወቃለች #ቀዳሚት_ሥዑር_ (#ሥዑር_ቅዳሜ)፤ #ገብረ_ሰላመ_፤ (#ለምለም_ቅዳሜ) #ሰንበት_ዐባይ #ቅዱስ_ቅዳሜ፤ #ቀዳሚት_ሰንበት ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #ቀዳሚት_ሰንበት፤ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ ከፈጸመ በኋላ ያረፈባት ስለሆነች፤ የእግዚአብሔር የዕረፍት ዕለት፤ ቀዳሚት ሰንበት (የዕረፍት ቀን) ትባላለች፡፡ #ሰንበት_ዐባይ (ታላቋ ሰንበት)፤ የመጀመሪያዋ ሰንበት በመሆኗ ታላቋ ሰንበት ትባላላች፡፡ #ቀዳሚት_ሥዑር_ (#ሥዑር_ቅዳሜ)፤ እግዚአብሔር ሥነ ፈጥረትን ከመፍጠር ዕረፍት እንዳደረገባት ዅሉ፣ የፍጥረት ርእስ የኾነውን አዳምን ለማዳን ሕማምና ሞት የተቀበለው አምላካችን ክርስቶስ በከርሰ መቃብር አርፎባታል፡፡ (ማቴ. ፳፯፥፷፩)፡፡ ፠ ‹ሥዑር› የተባለችበት ምክንያትም በዓመት አንድ ቀን ስለምትጾም (የጾም ቀን በመኾኗ) ነው፡፡ የጌታችን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያትና ሌሌችም የጌታ ወዳጆች ጌታችን ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት ጀምሮ ብርሃነ ትንሣኤውን እስኪያዩ ድረስ እህል ውኃ በአፋቸው አልዞረም፡፡ ይመኩበትና ተስፋ ያደረጉት የነበረ አምላካቸው በመቃብር ስላረፈ ዕለቷን ሞቱን በማሰብና ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡ ፠ የቻልን ሕዝበ ክርስቲያንም ይህን መነሻ በማድርግ ከዐርብ ጀምረን በማክፈል (በመጾም) እህል ውኃ ሳንቀምሱ ለሁለት ቀናት እናድራለን (እንካፍላለን)፡፡ እንደ ዋልድባና ማኅበረ ሥላሴ ባሉ ገዳማት ያሉ ታላላቅ አባቶችና ወንድሞች ደግሞ ከሆሳዕና አንዳንዶችም ከዕለተ ረቡዕ ጀምረው ለ7ት ቀናት ወይም ለ3ት ቀናት ያከፍላሉ፡፡ #ገብረ_ሰላመ_፤ (#ለምለም_ቅዳሜ) ቅዳሜ የጠዋቱ ጸሎት ሲፈጸም ካህናቱ ‹‹ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፤ (በመስቀሉ ሰላምን አደረገ፥ መሠረተ)›› እያሉ በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰቡ ምእመናን የምሥራች ቄጠማ ያድላሉ፡፡ ፠ ቄጠማው በኖኅ ዘመን በንፍር ውኃ ምደር በተጠለቀለቀች ጊዜ፤ ኖኅ ወደ መርከብ ይዟቸው ከገባው እንስሳት መካከል የውኃውን መጉደል ለመረዳት ርግብን በመርከብ መስኮት አሾልኮ ልኮ እርሷም ቄጠማ በአፏ ይዛ በመመለስ የምሥራች ምልክት፥ የውኃውን መድረቅ እንደተነገረችውና እንደተደሰተ ሁሉ (ዘፍ. ፱፥፩-፳፱)፡፡ ‹‹በክርስቶስ ሞት፤ ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ፤›› ስንል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ጠዋት ደባትር መዘምራን ዝማሬን ካቀረቡ በኋላ ለልጆቿ ቄጠማ ታድለናለች፡፡ የምሥራች ተምሳሌት የኾነውን ቄጠማም፤ ከሲኦል ቃጠሎ ወደ ጥንተ ማኅደራችን ገነት መመለሳችንን ለመመስከር በግንባራችን እናስረዋለን፡፡ (ፍኖተ ሕይወት) #ቅዱስ_ቅዳሜ፤ ለ5500 በሲኦል ሲማቅቁ የነበሩ ነፍሳትን ሰላም ለሁላችሁን ይሁን ብሎ ወደ ገነት አስገብቷቸዋልና፤ ይህች ቅዳሜ ቅዱስ (የተለየች) ቅዳሜ ትባላለች፡፡ አውረድዎ፥ አውረድዎ፥ አውረድዎ እምዕፅ፤ ወአምጽኡ አፈዋተ ከርቤ ሕዉስ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

፠ የተጻፈውን መግለጫ የሚያነቡትም ‹አይሁድ ነጻ የሚያወጣቸውን የገዛ ንጉሣቸውን ሰቀሉ› ብለው እንዲሳለቁባቸው፤ ክርስቶስን እንደ ክፉ ወንጀለኛ እንዲታይና እንዲዋረድ ፈልገው ላሰቀሉት አይሁድ ለወደፊቱም ቢሆን ለወሬ እንዳይመቻቸው፥ ክርስቶስን እንደማይጠቅምና እንደ ክፉ ሰው አድርጎ የሚወቅሰው ሰው ኃይል እንዲያጣ የሚያደርግ ነበር፡፡ በዚህም ቅዱስ ዳዊት የተነበየው ትንቢት ‹‹አንሰ ተሰየምኩ ንጉሠ በላዕሌሆሙ ፤ በጽዮን በደብረ መቅደሱ›› (እኔ ግን በላያቸው ላይ ንጉሥ ሆኜ ተሾምሁ ፤ በቅድስናው ተራራ በጽዮን) /መዝ. ፪፥፮/ ያለው ተፈጸመ፡፡ ፠ ‹የአይሁድ ንጉሥ ነኝ በማለቱ የተሰቀለው ኢየሱስ› ብሎ ሊጽፍ ሲገባው (መንፈስ ቅዱስ አፉን ከፍቶ ፊቱን ጸፍቶ) ‹ኢየሱስ ናዝራዊው የአይሁድ ንጉሥ› ብሎ ጻፈ፤ ይህም የክስ ጽሕፈት ሳይሆን የአንድን ድል አድራጊ ንጉሥ ማንነት የሚያስረዳ መግለጫ፥ ለጌታችን የተሰጠ የክብር ስም አደረገው፡፡ በገዛ ንጉሣቸው ላይ እንደተነሡ አድርጎ በማሳየት የሁሉንም አፍ ዘጋው፡፡ በዚያን ወቅት በስፋት በሚነገሩት በሦስት ቋንቋዎችም #በዕብራይስጥ፣ #በግሪክና #በሮማይስጥ ‹ኢየሱስ ናዝራዊ የአይሁድ ንጉሥ› ብሎ ጻፈ፡፡ በወታደሮቹ አማካይነትም ሰሌዳው ወደ ቀራንዮ ተወስዶ ሁሉም ሰው እንዲያየው ከጌታችን ከራሱ በላይ ተሰቀለ፡፡ ይህንንም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ወጸሐፈ ጲላጦስ መጽሐፈ ወይብል መጽሐፉ ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ፡፡ (ጲላጦስ መጽሐፍን ጻፈ ፤ መጽሐፉም ኢየሱስ ናዝራዊ የአይሁድ ንጉሥ ይላል፡፡››) ብሎ በድርሰቱ ገልጾታል፡፡ ፠ ‹‹ኢየሱስ የተሰቀለበት ሥፍራ ለከተማ ቅርብ ነበርና ከአይሁድ ብዙዎች ይህንን ጽሕፈት አነበቡት›› /ዮሐ. ፲፱፥፳/ ፠ ከመስቀሉ ሥር አንጋጥጠው ያነበቡት የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን በንዴት እየተብከነከኑ ከቀራንዮ ወደ ጲላጦስ ግቢ በብስጭት እየሮጡ መጡ፡፡ የሠራውን ሥራ የሚያውቀው ጲላጦስም የሚጠብቀው ነገር ነበርና ሊቃነ ካህናቱን አነጋገራቸው፡፡ እነርሱም ‹‹እርሱ የአይሁድ ንጉሥ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ›› አሉት፡፡ ጲላጦስ ግን ያቃጠሉትን ሊቃነ ካህናት አንጀት የሚያሳርርና የተዘጋጀበት የሚመስል አጭር መልስ መለሰላቸው ‹‹#የጻፍሁትን_ጽፌያለሁ::›› ፠ አይሁድ ይህንን ጽሕፈት ሲያዩ በንዴት ተንገበገቡ ፤ ተሰቅሎም እንኳን የካህናት አለቆች ይቀኑበት ነበርና፡፡ ‹‹እናንተ እንደምትሉት ክርስቶስ ሙትና ደካማ ከሆነ ይህ ጽሕፈት ሊጎዳችሁ አይችልም፤ የክርስቶስ ስሙም ሊረሳ ይችላል፡፡ ‹ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ› ተብሎ መጻፉ ለምን ያስፈራችኋል?›› /ይላቸዋል ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/ *፠* በቤተ ልሔም ሲወለድ ‹‹የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ›› እያሉ የምሥራቅ ነገሥታት መሰከሩለት፤ *፠* በቀራንዮ ሲሰቀል ‹‹የተሰቀለው የአይሁድ ንጉሥ›› ብሎ የምዕራብ ንጉሥ እንደራሴ ጲላጦስ ደግሞ መሰከረለት፡፡ *፠* ነቢዩ ዳዊት ‹‹እምሥራቀ ፀሐይ እስከነ ዐረብ፥ ይትአኰት ስሙ ለእግዚአብሔር›› (የእግዚአብሔር ስሙ ከፀሐይ መውጫ (ምሥራቅ) እስከ መግቢያው (ምዕራብ) ድረስ ይመስገን፤) ብሎ የዘመረለት አምላካችን ከምሥራቅ ብቻ ሳይሆን ከምዕራብም ‹የአይሁድ ንጉሥ› ተብሎ ተመሰከረለት፡፡ ፠ ጌታችን በምድር ላይ ባስተማረበት ወቅት ያስተማረው በአንድ ቋንቋ ብቻ ተወስኖ ነበር፤ ‹‹በሰናዖር ሜዳ ቋንቋዎችን የደባለቀውና ብዙ ቋንቋዎች እንዲናገሩ ያደረገው እርሱ ሆኖ ሳለ ስለ ትሕትናው በአንዲት ቋንቋ ብቻ አስተማረ›› /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/፡፡ ጲላጦስ ደግሞ ወንጌላውያን ወንጌላቸውን ከመጻፋቸው ቀድሞ በሦስት ቋንቋዎች ጽሕፈቱን መጻፉ (ወንጌልን መስበኩ) የክርስቶስ መንግሥት የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በቋንቋ የማትገደብ በሕዝብና በአሕዛብ ላይ የምትጸና መሆኗን ያሳያል፡፡ ፠፠ በጥቅሉ ‹ኢ.ና.ን.አ.› ማለት፤ /ዮሐ. ፲፱/ ‹‹የምስጉኖችና የታማኞች ንጉሥ የሆነው መድኃኒት የተለየና የተቀደሰ አክሊልን የተቀዳጀ ነው፡፡›› የሚል ነው፡፡ ልዩ ማስታወሻ፤ ዛሬም በአንገታችን ላይ የምናስረው መስቀል (በተለይም ከአኵሱም ተቀርጾ የሚመጣው ላይ ሊጻፍበት የሚገባው የጌታችን ስም (‹ኢ.ና.ን.አ.›) የሚለው እንጂ የራሳችን ስም መሆን የለበትም!!!! (እንዳይረሳ!!) ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለወላዲቱ ድንግል፤ ወለመስቀሉ ክቡር አሜን፡፡ ꔰ ወስብሐት ለእግዚአብሔርꔰ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share #like Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #ኢ. #ና. #ን. #አ. ‹‹#የጻፍሁትን_ጽፌያለሁ::›› #ኢ ፩ኛ) #፠#ኢየሱስ_፤ ፠ አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ከሥጋ ማርያም ጋር ተዋሕዶ፤ ከሁለት አካል አንድ አካል፥ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆኖ፤ በዘመነ ሥጋዌ ከተጠራባቸው ስሞች መካከል፤ ኢየሱስ፥ ክርስቶስ፥ አማኑኤል፥ መድኀኔ ዓለም፥ መድኅን፥ የሰው ልጅ፥ የእግዚአብሔር ልጅ፥ ቃል፥ እግዚአብሔር ወልድ፥ አንድዬ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ጌታ፥ … የሚሉ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ፠ ኢየሱስና ክርስቶስ የሚሉት ስሞች ከጥንት ጀምሮ (የሰው አእምሮ ገና ያልበሰለ፤ ክፉዎች አይሁድም ነገሩን ለፌዝ፥ ለቧልት ያውሉት ነበርና፤ ምንም እንኳን በግልጽ ባየገለጹም)፤ በነቢያት የተነገሩና በመላእክት የተበሠሩ፤ የጌታን አምላክነት የሚያሳዩ፤ የጌታን አዳኝነት የሚያመለክቱ ስሞች ናቸው፤ /አውሳብዮስ/፡፡ ለምሳሌ፤ ልበ አምላክ ዳዊት ‹‹እምቅድመ ፀሐይ ሀሎ ስሙ፤ ስሙ ከፀሐይ በፊት ነበረ፡፡›› /መዝ 71÷17/ ብሏል፤ እንዲሁም ነቢዩ ሙሴ በምሳሌ ጠርቶታል፤ የሊቀ ካህንነቱ አገልግሎት ሊቀ ካህኑ የክብርና የከፍታ ምልክት፣ የነዌ ልጅ ኢያሱም የአዳኛችንን ምሳሌ ተሸክሞ ነበር፡፡›› /ዘጸ. 25፥40፣ ዘሌ. 4፥5፡16፤ 6፥22/ ብሏል ይህንንም የመልክአ ኢየሱስ ደራሲም ‹‹አክሊለ ስምከ እንዘ ይትቄጸል በርእሱ፤ አኅጉረ ፀር ወረሰ ኢያሱ፡፡›› (የስምህን አክሊል በራሱ ላይ አድርጎ የጠላትን ሀገሮች ኢያሱ ወርሷል) ብሎ አመስጥሮታል፡፡ • ይህንን ከዓለም በፊት የነበረውን ስሙን ከሰማይ ተቀብሎ ለእመቤታችን እንዲናገር የተላከው መልአክ፤ መጋቤ ሐዲስ ቅዱስ ገብርኤል ሲሆን ‹‹ስሙን የመሰየም›› ሥልጣን የተሰጣት ደግሞ እመቤታችን ናት፡፡ ˝ኢየሱስ ትይዋለሽ˝ /ሉቃ 1÷31/ ፠ #ኢየሱስ_ማለትም(ትርጓሜውም)፤ ሀ) መድኃኒተ ሥጋ ፥ መድኃኒተ ነፍስ ማለት ነው፡፡ * በእብራይስጥ የሹኣ፥ ኢያሱ ወይም «ያሕዌ መድኃኒት ነው» የሚል ትርጉም አለው። ፠ እርግጥ ነው፥ በትንቢት፥ በምሳሌና በጥላ ቀድሞ ለተነሡት « አዳኞች» ኢያሱዎች ተሰጥቷል። (ለምሳሌ ዘካርያስ 3፥1 ላይ ሊቀ ካህናቱን ኢያሱን ያስታውሷል።) ሆኖም ግን እነዚህ « አዳኞች» ያዳኑት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ነው፡፡ ያዳኑትም የእግዚአብሔርን ኃይልና ረድኤት አጋዥ በማድረግ ነው፤ ያዳኑት(የታደጉትም) ከምድራዊ ጠላቶቻቸው ስለሆነ ማዳናቸው ውሱን ነው፡፡ *****አማናዊው ኢያሱ አዳኛችን ግን ያዳነው « ሕዝቡን» (የራሱን ሕዝብ) ነው። ያዳነውም እግዚአብሔር ተጠቅሞበት ሳይሆን ራሱ እግዚአብሔር ስለሆነ መድኃኒት ሆኖ ነው። ሕዝቡን ያዳነውም «ከኃጢአታቸው» ነው። ይህ አነጋገር የሚገባው ለእግዚአብሔር ብቻ ነው። በመሆኑም እንደቀድሞዎቹ እግዚአብሔር በምሳሌና በጥላ ሳይሆን ራሱ በመካከላችን በማደሩ ‹‹አማኑኤል እግዚአብሔር ከእኛ ጋር፡፡›› እንደ ሆነና በዚህም የነቢዩ የኢሳይያስ ትንቢት ፍጻሜ እንዳገኘ ነበር የእግዚአብሔር መልአክ የገለጠው። ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ማዳኑም የአምላክነቱ መገለጫ ነው። ለ) ሕዝቡን በኃጢአታቸው ከመጣባቸው ፍዳ የሚያድናቸው መድኀኒት ማለት ነው፡፡ /ማቴ 1፥21፣ ተረፈ ኤርምያስ) (ዳግመኛም ወገኖቹን ከኃጢአታቸው የሚያድናቸው ኢየሱስ ይባላል፡፡ /ቅ.ኤፍሬም/፡፡) (‹‹ኢየሱስ ስዱድ ተስፋሆሙ ለስዱዳን›› /ሰቈቃወ ድንግል/) ሐ) ኃጢአታችንን የሚያስተሠርይልን ማለት ነው፤ ‹‹አመ ይእኅዝዎ ለኢየሱስ ፀሐይ ጸልመ›› /ቅዱስ ያሬድ፥ ድጓ/ መ) ዳግማይ አዳም ማለት ነው (የኢየሱስ የስሙ ቊጥር ከአዳም የስም ቊጥር ጋር የተባበረ ነውና) *ኢየሱስ፡- አ=40, የ=90, ሰ=7, ሰ=7 ድምር =144፤ *አዳም፡-አ=40, ደ=100, መ=4 ድምር =144 *ዳግማይ አዳም የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ወደ ኤዶም ገነት አገባው ማለቱ ኤዶም፡-አ=40, ደ=100, መ=4 ድምር =144 #ና. ፪ኛ) #፠#ናዝራዊ_፤ ከናዝሬት የመጣ /ማቴ 2፥ 23/፤ በሌላም ትርጕምም ቸር፥ እረኛ፣ በዕብራይስጥ ደግሞ የተለየ ፣ አክሊል የተቀዳጀ ፣ የተቀደሰ ማለት ነው፡፡ ፠ ‹‹ኢየሱስ ናዝራዊ አምላኮሙ ለናዝራውያን›› እንዲል /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፤ መጽሐፈ ምሥጢር/ ፠ ማቴ. 2÷23 «በነቢያት ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጻም ዘንድ ናዝሬት ወደ ምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ፡፡›› ፠ ትንቢቱ (በማቴዎስ ወንጌል የተገለጠው) ልጄ እንደ ሶምሶን ናዝራዊ ይባላል የሚል ነው፤ ነገር ግን በ66ቱም ሆነ በ81ዱ መጻሕፍት አይገኝም፤ መጽሐፉ በምርኮ ጊዜ ጠፍቷል፤ ይህም ከ66ቱ መጻሕፍት ሌላ መጽሐፍ የለም ለሚሉ ወገኖች ማስረጃ እንደሆነ አስተውል፡፡ *፠* በመጽሐፍ ቅዱስ ስማቸው የተጠቀሰው ናዝራውያን 2ት ናቸው እነርሱም ሶምሶንና ጌታችን፤ በምን ይመሳሰላሉ ቢሉ:: **ሶምሶን በተናቀች በአህያ መንጋጋ ጠላቶቹን እንዳጠፋ፤ ጌታም አይሁድ፣ አጋንንት፣ መናፍቃን በናቁት ሞቱ ሞትን አጥፍቷል፡፡ /መሳ. 15÷9-19/ **ሶምሶን በሕይወተ ሥጋ ካጠፋቸው አሕዛብ ይልቅ በሞቱ ያጠፋቸው ይበዛሉ፡፡ ጌታም በሕይወተ ሥጋ ሳለ ካጠፋቸው አጋንንት ይልቅ በሞቱ ያጠፋቸው ይበዛሉ፡፡ /ምሳ. 16÷23-31/ #ና. ፫ኛ) #፠#ንጉሥ_፤ አፄ፣ ባለዘውድ፣ ሹም፣ አለቃ፣ ማለት ነው፡፡ /ንጉሦሙ ለእስራኤል ውእቱ ይብሉ ሆሳዕና በአርያም እንዲል፡፡/ #አ ፬ኛ) #፠#አይሁድ_፤ ማለት የታመኑ፣ ምስጉኖች፣ ምዕመናን ማለት ነው፡፡ ፠ አይሁድ የሚከው ቃል እስከ ባባሎን ምርኮ ድረስ ከ12ቱ ነገደ ያዕቆብ (እስራኤል) የይሁዳ ብቻ ነበረ፡፡ ከምርኮ በኋላ እስከ ክርስቶስ ድረስ ግን ለእስራኤል ሁሉ (ለ12ቱም ነገድ) መጠሪያ ሆኗል፡፡ /ዘፍ. 29፥ 35/ #የአይሁድ_ንጉሥ (#ማዕከላዊ_ስም) ፠ ሰብአ ሰገል ስም ማዕከላዊ (የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ) እያሉ ነው ለጌታ መብዓ ይዘው የመጡት፤ ስለምንድነው ቢሉ? * አምላክ (ስም ላዕላዊ) እያሉ ያልመጡበት፤ ሰማይና ምድር የማይችለው ምን ወስኖት ምን ችሎት ነው ብለው እንዳይዘባበቱባቸው፡፡ አንድም ትንቢት የተነገረልን ሱባዔ የተቈጠረልን እኛ እያለን እንዴት ለእነርሱ ተገለጠላቸው ብለው እንዳይዘባበቱባቸው፤ አንድም አሕዛብ ናቸው በየት አውቀውት ብለው እንዳዘብቱባቸው ነው፡፡ * የተወለደው ሕፃን (ስም ታህታዊ) እያሉ ያልመጡት፤ በእስራኤል ሃገር በአንድ ቀን ውስጥ ብዙ ሕፃናት ተወልደው ብዙ ሕፃናት ይሞታሉ፤ ስንቱን እናውቅላችኋለው ባሏቸው ነበርና፡፡ ፠ ሮማዊው ገዢ ጲላጦስ ጌታችንን በዳዊት ከተማ በጽዮን በቀራንዮ መካከል እንዲሰቀል አሳልፎ ከሰጠና ካሰቀለው በኋላ፤ ከመስቀሉ በላይ የሚጻፈውን የተለመደ የክስ ጽሕፈት (ሮማውያን በስቅላት የሚቀጡትን ሰው ለሞት ያበቃው ክስ ምን እንደሆነ በሰሌዳ ጽፈው በመስቀሉ ላይ ከፍ አድርገው የማሳየት ልማድ ነበራቸው፤ በዚያ ሥፍራ የሚያልፉ ሰዎችም ሁሉ የክሱን ጽሕፈት እያነበቡ ስለ ተሰቀለው ሰው ማንነትና ወንጀል ይረዱ ነበርና) ከቤቱ ቁጭ ብሎ ሲያስጨንቁት ያረፈዱትን የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ለመበቀል ነበር በሰሌዳ ላይ ያረቀቀው፡፡

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ (#ሥርዐተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘዐርብ_ስቅለት_፡፡) (እየሰገድን የምንላቸውም) ቃላት፡፡ ፠ #፩ኛ #ስግደት፤ የወንጌል ምንባብ እንዳበቃ በማስከተል ተግሣጽ ተነቦ እንደተፈጸመ፤ *‹‹#ጸልዩ_በእንተ_ጽንዐ_ዛቲ_መካን›› የሚለውን ካህኑ ሲመራና ዲያቆኑ በየምዕራፉ ቃጭል ሲደውል፤ #ሕዝቡ_እየተቀበሉ_እግዚኦ_ተሣሀለነ (አቤቱ ይቅር በለን) በማለት ፳፪ት ጊዜ በግእዝ፥ በዕዝልና በአራራይ ዜማ እየተዜመ ይሰገዳል፡፡ ፠ #፪ኛ #ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹#ለከ_ኃይል_ክብር_ወስብሐት›› የሚለውን ምቅናይ በመሪና በአንሺ ወገን መቀባበል ፮ት ፮ት ጊዜ (በድምሩ ፲፪ ጊዜ) ይበሉ፤ በመጨረሻም በ፲፫ኛው ከ‹‹ለከ ኃይል›› እስከ ‹‹ዕብል በአኰቴት›› ድረስ አንድ ጊዜ በኅብረት ይበሉ፡፡ /ከሆሳዕና ሠርክ እስከ ሰኞ ሰርክ መሪ በቀኝ፤ ተመሪ በግራ ሲሆን፡፡ ከማክሰኞ ሠርክ ጀምሮ ግን መሪ የነበረው ተመሪ፤ ተመሪ የነበረው መሪ ይሆናል፡፡/ እንዲህ እያሉ ይበሉ፤ + ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤ + አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፤ + ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤ + ኃይልየ ወፀወንየ ውእቱ እግዚእየ፤ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኰቴት፤ + አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ፥ ትምጻእ መንግሥትከ፥ ወይኩን ፈቃድከ፥ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር፥ ሲሳየነ ዘለለዕለትነ፥ ሀበነ ዮም፥ ኅድግ ለነ፥ አበሳነ ወጌጋየነ፥ ከመ ንህነኒ ንኅድግ፥ ለዘአበሰ ለነ፥ ኢታብአነ፥ እግዚኦ ውስተ መንሱት፥ አላ አድኅነነ፥ ወባልሐነ፥ እምኵሉ እኩይ፥ እስመ ዚአከ፥ ይእቲ መንግሥት፥ ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ ፠ #፫ኛ #ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹#ለአምላክ_ይደሉ››ን መጀመሪያ በመሪ እየቀደሙ በአንሺ እየተከተሉ አንድ ጊዜ ይዝለቁ፤ በ፪ኛው ክፍል ደግሞ እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይበሉ፡፡ እንዲህ እያሉ ይበሉ፤ + ለአምላክ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለሥሉስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለማሕየዊ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለዕበዩ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለዕዘዙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለመንግሥቱ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለሥልጣኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለምኵናኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለኢየሱስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለክርስቶስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለሕማሙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለመስቀሉ ይደሉ (ለዐርብ ብቻ)፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ቀጥሎ ያለውን የመዝጊያ ጸሎት እያዜሙና እየሰገዱ ፫ት ጊዜ መላልሰው ይዝለቁት፡፡ +*+ ለከ ይደሉ ኃይል፥ ወለከ ይደሉ ስብሐት፥ ወለከ ይደሉ አኰቴት፥ +*+ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ ፠ #፬ኛ #ስግደት፤ ዜማው አሁንም በቀኝና በግራ በመቀባበል ነው የሚባለው፡፡ በመሪ ወገን እየቀደሙ፤ በአንሺ ወገን ደግሞ እየተከተሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፤ ቀጥለውም በመሪና በተመሪ ወገን እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፡፡ * መሪ፤ ክርስቶስ አምላክነ፥ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ፥ በሕማማቲሁ ቤዘወነ፤ ተመሪ፤ ንሰብሖ፥ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፥ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በብዝኀ (በዕበየ) ሣህሉ፡፡ /በዐርብ፤ ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ/ * #ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ #ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #እብኖዲ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ * ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ታኦስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ማስያስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ * ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ኢየሱስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ክርስቶስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ * ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #አማኑኤል ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ትስቡጣ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፡፡ **** ኪርያላይሶን የሚለውን ብቻ በመሪ ፳፩ ጊዜ፥ በተመሪ ወገን ፳ ጊዜ ይበሉ፤ ድምሩ ፵፩ ኪርያላይሶን ይኾናል፡፡ ፠ የየሰዓቱን (የሌሊት፣ የነግህ፣ የጠዋት 3 ሰዐት፣ የቀትር/6 ሰዐት/፣ የተሰዐት/9ኝ ሰዐት/፣ የሰርክ /11 ሰዐት/፣ የንዋም) መልክአ ሕማማት በዜማ ይደርሳል፡፡ ፠ካህኑ ቡራኬ ሰጥቶ፤ ዲያቆኑ ደግሞ ‹‹ሑር በሰላም›› ብሎ ሕዝቡን ያሰናብታል፡፡ #share #share... ያድርጉ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ወስብሐት ለእግዚአብሔርꔰ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

ብጽዕ አባታችን #አቡነ_መልከ_ጼዴቅ ለ4ኛ ጊዜ ለደብራችን መመርያ አስተላለፉ:: ለብጽዕ አባታችን በእውነት ረጅም ዕድሜ ከጤና ጋር ተመኝን! ይህ ደብዳቤ በ13/08/2013 ዓ.ም የተላከ ቢሆንም ለማኀበራዊ ሚዲያ ተከታዮቻችን ከማሳወቃችን በፊት በድብዳቤው መሰረት የደብራችን አስተዳደር ጽ/ቤት ይፈጽማሉ ብንልም እስካሁን የተፈጸመ ነገር የለም ፡፡ በአሁኑ ሰዓት የብጹዕነታቸውን መመርያ ለመተግበር የደብራችን ሰበካ ጕባዔ ጽ/ቤት የቀረው 2 ቀን ብቻ ነው :: በደብዳቤው መሰረት፤ ሚያዝያ 20/2013 ዓ.ም የመዋዕለ ሕጻናቱ ውል መሻሻል ወይም መቋረጥ መቻል አለበት ፡፡ ውሳኔው ላይም የሰ/ት/ቤቱ ሕንጻ ቀድሞ ካለቀ የሰ/ት/ቤቱ የመጨረሻው ወለል ለደብሩ ጽ/ቤት ቢሮ በጊዜያዊነት እንዲሰጥና የደብሩ የልማት ሕንጻ ሲያልቅ ከሰ/ት/ቤቱ ወጥቶ እንዲዘዋውር ያዛል ፡፡ነገር ግን መዘዋወር ካልቻለ ለደብሩ ጽ/ቤት በቋሚነት እንዲቀጥል ያልተፈቀደለት ስለሆነ የራሱን መንገድ ፈልጎ እንዲወጣ በጊዜው እንደሚገደድ ያሳውቃል ፡፡ ሰ/ት/ቤቱ ይህ ሃሳብ ባይኖረውም ነገር ግን ሊቀ ጳጳሱ ግራ ቀኙን አይተው አመዛዝነው ፤ ለቤተክርስቲያን የሚጠቀመውን እና የሚበጀውን ተመልክተው የወሰኑት ውሳኔ ከመሆኑም በላይ ፤ የበላይ አካል እና በሀገረ ስብከታችንም በመጨረሻው ውሳኔ ሰጪ አባት የተወሰነ በመሆኑ በደስታ እንቀበለዋለን፡፡ ከዚህ ወጪም ነባሩ ሰበካ ጕባዔም ፤ለምዕመናን በ3 ዓመት ውስጥ ሲሰራ የቆየውን ስራ ሪፓርት እንዲያረጉ መመርያ ወርዶላቸዋል ፡፡ በአሁኑ ሰዓት ደብራችን ሰበካ ጕባዔ የለውም፤ ከተበተነም 3 ወራት አልፈውታል ፡፡ ቢሆንም ብፅዕነታቸው በሰጡት መመርያ መሰረት #ነባሩ_ሰበካ ጕባዔ ለምዕመናን ራፖርት ማቅረብ መቻል አለበት፡፡ የሰ/ት/ቤቱንም ጉዳይ ፣ የሰበካ ጕባዔውንም ጕዳይ፤ አፈጻጸሙን እየተከታተልን በየጊዜው የምናሳውቃቹሁ ይሆናል፡፡ ሰ/ት/ቤቱ ይህንን ጕዳይ በበላይነት እየመሩ የነበሩት የአ.አ ሰ.ት.ቤቶች ማደራጃ ዋና ክፍል እና የሰንበት ት/ት ቤቶች እንድነትን ከልብ እናመሰግናለን፡፡ ስለ ሁሉም ነገር ፤ክብር ለመድኀኔዓለም ይሁን ፡፡ www.Finotehiwotsundayschool.com

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት - Статистика та аналітика Telegram каналу @finotehiwott