uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 383 підписників, посідаючи 5 582 місце в категорії Релігія і духовність та 2 194 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 383 підписників.

За останніми даними від 09 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 38, а за останні 24 години на -1, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 21.91%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 9.42% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 370 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 449 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 25.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 10 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 383
Підписники
-124 години
-67 днів
+3830 день
Архів дописів
✤✤ #በአዲስ አበባ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ልደት የሚከበርባቸው፤ 1.# ጥንታዊው ዋሻ ሚካኤልና ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ #በአዲስ_አበባ_የመጀመሪያው_ቤ/ክ፡፡ (በ320ዓ.ም. የተመሠረተ፡፡) 2
+2
✤✤ #በአዲስ አበባ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ልደት የሚከበርባቸው፤ 1.# ጥንታዊው ዋሻ ሚካኤልና ተክለ ሃይማኖት ገዳም፤ #በአዲስ_አበባ_የመጀመሪያው_ቤ/ክ፡፡ (በ320ዓ.ም. የተመሠረተ፡፡) 2.#ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም (በ1898ዓ.ም. የተመሠረተ) 3.#መንበረ ክብር ደብረ ታቦር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም 4.#ፊሊዶሮ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሀይማኖት 5.#ቤቴል ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ፤ በድርብነት ይከብራል፡፡ 6.#ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሩፋኤል ቤ.ክ፤ በድርብነት ይከብራል፡፡ 7.#ካራ ምሥራ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤልና 24ቱ ካህናተ ሰማይ 8.#ሲምሲ ተክለ ሃይማኖት 9.#ቦሌ ቡልቡላ ተክለ ሃይማኖት 10.#መልካ ቆራኒ አቡነ ተክለ ሃይማኖት 11.#ምስካበ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት 12.#ቦሌ ለሚ ተክለ ሃይማኖት 13.# ፈለገ ሰላም ቤላ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና አቡተ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ ሌሎች ካሉ ጨምሩባቸው፤ ፎቷቸውንም ላኩልን፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

በእጨጌ የሚመሩት 2ቱ ደብረ ሊባኖሶች፤ 1ኛ) ደብረ ሊባኖስ ገዳም፤ (ሰሜን ሸዋ) 2ኛ) አዘዞ ደብረ ሊባኖስ ገዳም፡፡ (ጎንደር) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com
+3
በእጨጌ የሚመሩት 2ቱ ደብረ ሊባኖሶች፤ 1ኛ) ደብረ ሊባኖስ ገዳም፤ (ሰሜን ሸዋ) 2ኛ) አዘዞ ደብረ ሊባኖስ ገዳም፡፡ (ጎንደር) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

የጠቅላላ ጕባኤ ጥሪ፤ ለአባላት በሙሉ፡፡ የአራዳና ጉለሌ ክ/ከተማ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በሰ/ት/ቤታችን አገልግሎትና መማርያ ቦታን በተመለከተ ቅዳሜ #ታኅሣሥ_25 #ከቀኑ_በ10_ሰዐት እንድንወያይ
የጠቅላላ ጕባኤ ጥሪ፤ ለአባላት በሙሉ፡፡ የአራዳና ጉለሌ ክ/ከተማ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በሰ/ት/ቤታችን አገልግሎትና መማርያ ቦታን በተመለከተ ቅዳሜ #ታኅሣሥ_25 #ከቀኑ_በ10_ሰዐት እንድንወያይ ጥሪ ስላደረገ፤ አባላት በሙሉ በተጠቀሰው ሰዐት በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ (የቀ/ደ/ሰ መድኀኔዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት)

✤✣✤ #በዓለ_ልደቱ_ለሐዲስ_ሐዋርያ_ፀሐይ_ማር_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት #ታኅሣሥ_24_1196ዓም_በሰሜን_ሸዋ_ቡልጋ_ጽላልሽ_እቲሣ_ተወልደው_በአጠገቡ_በምትገኛወ_ደብረ_አጋዕዚት_ክርስትና_ተነሡ፡፡ #አባታቸው ቅዱስ ጸጋ ዘዓብና እናታቸው ቅድስት እግዚእ ኀረያ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሲያስተምሯቸው በአካባቢያቸው ደግሞ በዘመኑ የነበሩ ልጆች ይማሩ የነበረውን ፈረስ መጋለብን፣ ቀስት መወርወርን፣ እርሻንና አደንን አስተምረዋቸዋል፡፡ #በ7ት ዓመታቸው ከግብፃዊው ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ ዲቁናን ከተቀበሉ በኋላ እግዚአብሔር በክህነት ሕዝቡን እንዲያገለግሉ መረጣቸው፡፡ ከዮዲት ጉዲት በኋላ ሃገራችን ሰሜኑና ደቡቡ ተቆራርጧል፤ የሐሳብን ልዕልና የሚያመጣው የመንፈስ ልዕልና ተዳክሟል፡፡ ለዚህም ኢትዮጵያን የሚዋጅ ሐዲስ ሐዋርያ ያስፈልግ ነበርና አምላካችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ጠራ፡፡ #አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅስናን ከአቡነ ቄርሎስ ተቀብለው በጽላልሽ አካባቢ በክህነት ከአባታቸው ጋር አገልግለዋል፡፡ አባታቸው ሲያርፉ በወንጌሉ ማንም ሊከተለኝ የሚወድድ ቢኖር ያለውን ሁሉ ትቶ መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ ያለውን በመከተል ሀብታቸውን ለድኾች መጽውተው በሸዋና በዳሞት በስብከተ ወንጌል አገለገሉ፡፡ ከዚያም፤ #በመጀመርያ ደቡብ ወሎ ቦረና ላይ ገዳማቸውን ደብረ ጎል ገድመው ወደሚገኙት ታላቁና ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ወደኾኑት ጻድቅ አባት አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው ዐሥር ሁለት ዓመታት በትምህርትና በሥራ (በአርድእትነት) አሳልፈዋል፡፡ በዚያም ዋሻ ፈልፍለው አስደናቂ ሕንፃ ሠርተው ነበር፡፡ #በ1216 ዓ.ም. አካባቢ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገሳም ገብተዋል፤ በዚሁ ገዳምም ከመመንኰሳቸው በፊት ሰባት ዓመት ከመነኰሱም በኋላ ሦስት ዓመት በድምሩ ለ10 ዓመታት በትምህርት፣ በእደ ጥበብ ሥራ፣ በአገልግሎትና ሥርዐተ ምንኵስናን እያጠኑ ቆይተዋል፡፡ #ከሐይቅ ወጥተው በዘመኑ በሥርዐተ ምንኵስናና በትምህርት ብሎም በጥበበ እድ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ወደ ነበረው ወደ ደብረ ዳሞ በመሄድ በየገዳሙ አበምኔት ከሆኑት ከአቡነ ዮሐኒ ዘንድ መንፈሳዊ ትምህርት፣ ሥርዐተ ምንኵስናና ጥበበ እድ ሲማሩ ለ12 ዓመታት ቆዩ፡፡ ያነጹት ፍልፍል ድንጋይ ዋሻ፣ መጻሕፍት ሲጽፉ ቀለማቸውን ያስቀምጡባቸው የነበሩትን ሽንቁሮች ዛሬም በደብረ ዳሞ ማየት ይቻላል፡፡ #በደብረ ዳሞ የነበራቸውን ቆይታ ጨርሰው በገመድ ሲወርዱ ሰይጣን በቅንዐት መጥቶ ገመዱን በጠሰባቸው እግዚአብሔር አምላክ በዚህ ወቅት የሚበሩበትን እንደ መላእክት ክንፍ ሰጣቸው፡፡ #ለአምስት ዓመታት #አኵስምን_ዋልድባን እንዲሁም ሎሎች የትግራይ ገዳማትን እየተዘዋወሩ ሲመለከቱ ቆዩ #ከሸዋ በወጡ በሃያ ሁለት ዓመት (እድሜያቸው ሃምሳ ሁለት ሲሆን) ለበለጠው ክብር እና ርእይ በግብጽ በኩል ወደ ኢየሩሳሌም ተሻገሩ፡፡ #ከኢየሩሳሌም ሲመለሱ በሐይቅ በኩል አድርገው ደብረ ጎልን ተሳልመው በሚዳ እና በመርሐ ቤቴ በኩል ወደ ሸዋ በመምጣት ከዮዲት ዘመን በኋላ በመንፈሳዊ ሕይወት የተጎዳውን ሸዋን እና ደቡብ ኢትዮጵያን በመዘዋወር ለዐሥር ዓመታት ያህል አስተምረዋል፡፡ #አቡነ ተክለ ሃይማኖት ተግተው በማስተማራቸው የተኛው ሁሉ ነቃ፣ የደከመው በረታ፣ የጠፋውም ተገኘ፡፡ ሐዋርያትን ለማፍራት እንዲችሉ አንድ ገዳም ለመመሥረትና ደቀ መዛሙርትን ለማስተማር አሰቡ፡፡ እናም ወደ ደብረ አስቦ ገዳም ገቡ፡፡ ቦታውን አስተካክለው እና ከደብረ ዳሞ እና ከሐይቅ የተከተሏቸውን ጥቂት ደቀ መዛሙርት ይዘው በደብረ ሊባኖስ ገዳም ልክ እንደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ሁሉ ሦስቱን ነገሮች ያካተተ አገልግሎት ጀመሩ፡፡ ምንኵስና፣ ትምህርትና ሥራ፡፡ መነኰሳቱ መንፈሳዊ ትምህርት ይማራሉ፤ በሕገ ገዳም ይመራሉ፤ ለራሳቸው እና ለአካባቢው ሕዝብ ርዳታ የሚሆን እርሻ ያርሳሉ፡፡ #ደቀ መዛሙርትን አፍርተው፣ ገዳማቸውን አደራጅተው፣ ስብከተ ወንጌልንም አስፋፍተው ካደላደሉ በኋላ በሕይወታቸው የመጨረሻ ዓመታት ወደ ደብረ አስቦ ዋሻ ገብተው በአንድ እግራቸው በጾም እና በጸሎት ተወሰኑ፡፡ #አገልግሎታቸውን ፈጽመው ነሐሴ 24 ቀን 1297 ዓ.ም. በ99 ዓመታቸው ዐረፉ፡፡ ✤✤ #እቲሣ_ገዳም_ #በቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃና አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን የተመሠረተ፤ ሲመሠረትም በታቦተ ኢየሱስና አርባዕቱ እንስሳ ነው፤ #ሊቀ ካህናት አበይድላ ከአኵስም 300 ታቦታትና 300ካህናት ይዞ መጥቶ በጽላልሽ የተቀመጠባት ናት፤ #ፀሐይ አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱባት (የተወለዱባት ጠፍጣፋ ደንጊያ አሁንም በቦታው አለች)፣ #አባታቸውና ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእኀረያ የተወለዱበት፤ ኋላም ክብሩ አጽማቸው ያረፈበት ነው፡፡ #ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ጸልዮባታል፤ #ቅዱስ ላሊበላ 7 ዓመት ጸልዮባታል፤ #ተሰዓቱ ቅዱሳን 20 ዓመት የጸለዩበት፤ #ሐርቤ በሚባለው ቦታ ላይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ 7 ዓመት ጸልየውበታል፤ #ታቦተ ጽዮን 12 ዓመት (ከ9ሺህ ሕዝብ) ጋር መጥታ ኖራበታለች፤ #በአምሳለ ሲዖል የተሠራ አስደናቂ የጨለማ ዋሻ ያለበት ነው፤ #ብዙ የታሪክ ቅርስ ያለበት ነው፤ #በቅዱስ ሚካኤልና ጸጋ ዘአብ ቤተ ክርቲያን ውስጥ ካየን በኋላ፤ እዚሁ ቦታ በሚገኘው ፈዋሽ ጠበል ተጠምቀንና ጠጥተን ጕዟችንን ወደ #ቦታው_ከአአ_በቅርብ_ርቀት_በደብረ_ብርሃን_መንገድ_አሌልቱ_ከተማ_ላይ_በመታጠፍ_ይገኛል፡፡ #ሥርዐተ_ማኅሌቱን_እንደየደብራችሁ ይትበሃል እንድትጠቀሙበት በማሰብ ሁሉንም (በላይ ቤትና በታች ቤት) (#ዘአባጃሌ_ተክለ_ሃይማኖትና_ዘአደባባይ_ተክለሃይማኖት) አዘጋጅተነዋል፡፡ ጸሎትና በረከታቸው፤ ረድኤትና ምልጃቸው በመላው ሕዝበ ክርስቲያንና በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ አድሮ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ታኅሣሥ_23 #ቅድመ_ልደተ_ክርስቶስ_በ1080_ቅዱስ_ዳዊት_አረፈ_፡፡ ፠ እግዚአብሔር እንደ ልቤ ብሎ የጠራው ፤ በዚህም ልበ አምላክ ተብሎ የሚጠራ፤ ፠ 10ር አውታር ባለው በገና የሚያመሰግን፤ መዘምር፤ ፠ ከ15ቱ ነቢያት አንዱ፤ ፠ 40 ዓመታት እሥራኤልን የገዛ፤ አምላኩ ኪዳንን የሰጠው፤ ፠ የዋህ፣ ደግ፣ ትሁትና ርህሩህ (በየዋህነቱ ከሙሴ ጋር፤ በደግነቱ ከአብርሃም ጋር የሚነጻጸር) ፠ ኃይል የሆነ (በኃያልነቱ ከሶምሶን ጋር የሚነጻጸር) ፠ ጀግና (ከጀግንነቱ የተነሣ ዳዊት መጣ ሲባል ደንግጦና ፈርቶ የሚሞት የነበረ) ፠ አስተዋይና ብልህ መሪ (በርካታ አስተዋዮችና ብልህ መሪዎች በሥሩ የነበሩት) ፠ መዝሙሩ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ዕለት ዕለት የሚጸለይ (አንድ ክርስቲያን ግዴታ በየቀኑ ሊጸልየው የሚገባ ጸሎት ተብሎ በፍትሐ ነገሥት የተደነገገ) ፠ ከደረሰው መዝሙር የተውጣጡ ምስባኮች ከዓመት ዓመት በቅዳሴ ጊዜ በዜማ ጭምር የሚባሉለት ፠ የንስሐ አባት (ቶሎ ብሎ ንስሐ በመግባት ከፈጣሪው ጋር የሚታረቅ) * ትውልዱ ከእሥራኤልና እንዲሁም ከሞዓባውያን ወገን ከሆነችው ከደገኛይቱ ሩት ነው * እሥራኤልን በንግሥና መመምራት ከሳዖል ቀጥሎ ሁለተኛ ነው፡፡ (ነገር ግን የሳዖል መንግሥት የይንቆሽ ስለሆነ ዳዊት የመጀመሪያው የእሥራኤል ንጉሥ በመባል ይታወቃል)፤ * ገና በወጣትነት በእረኛ እጅ በፈጣሪው መራጭነት በጠንካራው እምነቱ ወደ ጦር ሜዳ በመጓዝ በግዝፍነቱና በጀግንነቱ ተወዳዳሪ የጠፋለት የዕብራውያንን ልብ እንደሰም ያቀለጠ፥ ንጉሣቸው ሳዖልንም ያሸበረና ያስደነገጠ፤ መምለኬ ጣዖት፥ መዝግበ ኃጢአት ፥ ትዕቢትን የተሞላ ፥ የጣዖት ድልብ ቁመቱ ስድስት ክንድ ከስንዝር የሚሆን ረአይታዊ ጎልያድን በፈጣሪው ኃይል በወንጭፍ ደንጊያ ግንባሩን መቶ ገርስሶ በመጣል ቸብቸቦውን በሰይፍ በመገንጠል እያንዳንዱ ዕብራውያንን ከጎልያድ ሰይፍ ታድጓል፡፡ (መዝ 151) ዳዊት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከጦር ሜዳ ሳይለይ አያሌ ዘመናት አሳልፏል፡፡ * የእስራኤል ሴቶችም ‹‹ሳዖል ሺህ ገደለ፤ ዳዊት ዕልፍ ገደለ /ጎልያድ የእልፍ ያህል ነውና/ እያሉ በመዝፈናቸው በሳዖል ልብ ቅንዐት አደረ፡፡ * በሽፍትነት በረሀ ለበረሀ በመንከራተት ብዙ ዘመን ካሳለፈ በኋላ ሳዖል ሲሞት መሪነቱን ይዟል፤ ነገር ግን እሥራኤልን ለመምራት የተመረጠው ገና ሳዖል በሕይወት እያለ በእግዚአብሔር ትዕዛዝ በሳሙኤል ቀባዒነት ነው፡፡ * ከጀግንነቱ የተነሣ ዳዊት መጣ ሲባል ደንግጦ እና ፈርቶ የሞተም እንዳለ ታሪክ ይነግረናል፡፤ 1ኛ ሳሙ 25፥1-39፡፡ ነገር ግን ዳዊት እንደ ጀግንነቱ ሁሉ ጨቃኝ አይደለም ርህራሄም የተሞላ መሪ ነበር ከአንዴም ሁለቴ ሳዖልን መግደል ሲችል ራርቶ የመረጠውን እግዚብሔርን ፈርቶ ትቶታል፡፡ * ዳዊት ትልቅ ኃጢአት የሠራው የጦር ጀግናው የኦርዮን ሚስቱን ከመቀማቱም ባሻገር በጦር ሜዳ ለጠላት ጦር አሳልፈው ሰጥተው ወደኋላ እንዲያፈገፍጉ ለእስራኤል በመምከር ኦርዮን ባልተረዳው ነገር ተደብድቦ እንዲሞት አስደርጓል፡፡ በዚህም እግዚአብሔርንም ሆነ የጦር መሪው ኢዮአብን አሳዝኗል፡፡ በዚህም እግዚአብሔር እውነተኛ ፈራጅ በመሆኑ በዳዊት ላይ ከበድ ያለ መከራና ኃዘን አምጥቶበታል፡፡ ለአነብነትም፤ 1ኛ) አምኖን የገዛ እኅቱን ከክብር አሳንሶ አዋረደ ፤ ዳዊት የሰው ሚስት በግፍ ደፍሮ ነበርና፤ 2ኛ) በዚህ ምክንያት አቤሴሎም ወንድሙ አምኖንን ገደለ ፤ ዳዊት ኦርዮንን በግፍ አስገድሎ ነበርና፤ 3ኛ) አቤሴሎም የዳዊትን መንግሥት ገልብጦ የአባቱን እቁባት ሁሉ በአደባባይ አረከሰ፤ ዳዊት የኦርዮንን ሚስት በድብቅ ተገናኝቷታልና እንዲሁም ዳዊት የሳዖልን መንግሥት አስቸግሮ ነበርና፤ 4ኛ) አቤሴሎም በአባቱ የጦር አበጋዞች ተደብድቦ ሞተ፤ በዚህም ዳዊት እጅግ አዝኖ ነበር፡፡ 5ኛ) አዶንያስም በአባቱ ላይ መፈንቅል አድርጎ ለጊዜው ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ ነገር ግን ከላይ የተዘረዘሩት 5ት ሐዘኖች ቢገጥሙትም ዳዊት በለመደው የንስሐ ልቅሶ ችግሩን አስተካክሎ ወደ ፈጣሪው ተጠግቷል፡፡ * ኃጢአቱን ይቅር ያለው ፈጣሪው ግን ቤተ መቅደስን እንዳይሠራ በነቢይ አማካይነት ከልክሎታል፤ ዳዊትም ይህን የፈጣሪውን መመሪያ አልተጋፋም ሥራውን አቁሟል፡፡ የእግዚብሔር እንደራሴ ስለነበረ፡፡ •+++• ዳዊት እግዚአብሔር ለሰው ከሚሰጣቸው ልዩ ሐብታትም ባለቤት ነበር፡፡ እነርሱም፤ 1ኛ. ሀብተ ጥበብ ወአዕምሮ 2ኛ. ሀብተ ትንቢት 3ኛ. ሀብተ ኃይል (ገና በእረኝነት ግሩማን አራዊት ድብና አንበሳን ጉሮሯቸውን እያነቀ በመግደል ኋላም ግዙፍ ጎልያድን በአልባሌ መሣሪያ ገርስሶ በመጣል) 4ኛ. ሀብተ ምክር 5ኛ. ሀብተ ልቡና 6ኛ. ሀብተ ፈሪሃ እግዚአብሔር 7ኛ. ሀብተ ፈውስ #መዝሙረ_ዳዊት_፤ ፠151 መዝሙራት ሲኖሩት 88ቱ እርሱ የዘመራቸው ሲሆኑ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ ሌሎች የዘመሩትን ሲሆን የሌሎችንም መዝሙራት 10ር አውታር ባለው በበገና ይዘምራቸው ስለነበረ 151ዱም የዳዊት መዝሙራት ተብለዋል፡፡ ፠ መዝሙረ ዳዊት ምሥጢራዊ ነገር ያለበት፥ በምሥጢሩ የጠለቀ፥ በትንቢታዊነቱ የረቀቀ፥ መንፈሳዊ ስብከት ፥ ትንቢታዊ ትምህርትን የተሞላ፥ ቊጥሩ አንድ ውስጡ ብዙ፥ የማይጠቅሰውና የማይናገረው የሌለ ዕፁብ ድንቅ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ ፠ መዝሙረ ዳዊት ባሕር ነው፤ አንድ ሰው ከጥልቅ ባሕር ገብቶ እንደ አቅሙ ትንሽ ዓሣ ይዞ ሊወጣ ይችላል፤ ፠ነቢዩ ዳዊት እግዚብሔር ብዙ ረቀቁ ትንቢቶችን ስለተናገረበት በፈጣሪው ዘንድ #የእግዚአብሔር_ልብ የመባል ልዩ ስያሜ ያገኘ ብቸኛ ሰው እንደነበር ዜና ነገሥት ይናገራል፡፡ /1ኛ ሳሙ 13፥14፣ የሐዋ ሥራ 13፥22/ ፠ ዳዊት በመዝሙሩ አምስቱን አዕማደ ምሥጢር መዝግቦ ያስነብበናል:: ፠ መዝሙረ ዳዊት ከተለያዩ መመዘኛዎች አንጻር በተለያዩ አከፋፈሎች ይከፈላል፡፡ #በቅዳሴ_ጊዜ_የዳዊት_መዝሙር_በዜማ_ይዜማል_ለምን? የዳዊት መዝሙር ለሌሎች የነቢያት መጻሕፍት ተለይቶ ቅድመ ወንጌል በዜማ እንዲሰበክ የተደረገበት ምክንያት፤ በርካታ ነገሮችን በወንጌል የተመዘገቡትን ስለያዘ ነው፡፡ በዚህም መዝሙረ ዳዊት ደረቅ ሐዲስ በመባል ይታወቃል፡፡ ስለ መዝሙረ ዳዊት ታላቁን ሊቅ ቅዱስ ያሬድን (በክስተተ አርያም፣ በመስተጋብዕ፣ …) ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫን (በመጽሐፈ ሰዐታቱ፣ በመዝሙረ ድንግል) ይጠይቁ፤ 151ዱን መዝሙር በቀጥታና በተዘዋዋሪ መንገድ በንባብ ብቻ ሳይሆን በጣዕማዊ ሰማያዊ ዜማ ከእግር እስከ ጫፍ ከጽንፍ አስመልክታ መልዕክቷን ወደ ፈጣሪዋ እንደታቀርብበት ለቤተ ልርስቲያናችን አስረክበዋልና፡፡ ፎቶ ላይ ይምትመለከቱት ቤ/ክ፤ ከ300 ዓመት በላይ የሆነውና #በአድያም #ሰገድ #አፄ #ኢያሱ (1674-1698) የታነጸውን የቅዱስ ዳዊት ቤተ ክርስቲያን ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያኑ የሚገኘው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ዳዊት ቀበሌ ነው፡፡ (ወደ ቦታው ለመሄድ ከፈለጉ ከአዲስአበባ ተነስተው ፡ #በእንጅባራ አልፈው ፡ #ቻግኒና #ግልገል በለስንም ተሻግረው #ማንቡክ ወደምትባል ከዚያም #በላያ የሚባል አካባቢ ላይ ንጉሥ ዳዊት ቀበሌንና የቅዱሱን ደብር ያገኛሉ፡፡) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ዜና_ዕረፍት_ የትህትና አባት ፣ የደብረ ዐባይ ቅዳሴ ሊቅ የሆኑት #ብፁዕ_አቡነ_ዳንኤል_የድሬዳዋና_የጅቡቲ_ሀገረ_ስብከት_ሊቀ_ጳጳስ_ዐረፉ፡፡ ትላንት ማምሻውን በመንበረ ፓትርያርክ በሚገኘው መኖሪያ
+1
#ዜና_ዕረፍት_ የትህትና አባት ፣ የደብረ ዐባይ ቅዳሴ ሊቅ የሆኑት #ብፁዕ_አቡነ_ዳንኤል_የድሬዳዋና_የጅቡቲ_ሀገረ_ስብከት_ሊቀ_ጳጳስ_ዐረፉ፡፡ ትላንት ማምሻውን በመንበረ ፓትርያርክ በሚገኘው መኖሪያቸው ያረፉት ብፁዕነታቸው፣ ከልብ ሕመም ጋራ በተያያዘ በሀገር ውስጥ እና በአሜሪካ የሕክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቆይቷል፡፡ ከሳምንት በፊት በአሜሪካ በነበሩበት ወቅት የልብ ቀዶ ሕክምና እንዲደረግላቸው ቢጠየቁም፣ "አልፈልግም፤ አገሬ ገብቼ ልሙት፤" ብለው እንደተመለሱ ታውቋል፡፡ የቀብራቸው ሥነ ሥርዐት ነገ ዐርብ፣ ታኅሣሥ 24 ቀን 2012ዓ.ም. በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን እንደሚከናወን ተጠቁሟል፡፡ (ዘግይቶ በደረሰን መረጃ፤ በቃላቸው መሠረትና በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ግብዐተ መሬቱ የሚከናወነው በደብረ ሊባኖስ ገዳም ነው፡፡ በቀድሞ ስማቸው አባ ፍቅረ ማርያም ይባሉ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ዳንኤል በምሥራቅ ኢትዮጵያ አህጉረ ስብከት አድባራት(ገለምሶ፣ ጎዴ፣ ድሬዳዋ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል) በአስተዳዳሪነት፣ በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ት/ቤት ዲን ኾነው ሠርተዋል፡፡ በሐምሌ ወር 1997 ዓ.ም. በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አንብሮተ እድ ኤጲስ ቆጶስነት ከተሾሙት 17 አባቶች አንዱ ሲሆኑ፤ ኤጲስ ቆጶስነት ከተሾሙ በኋላ፣ በምሥራቅ አፍሪቃ አህጉረ ስብከት(ኬንያ እና ጅቡቲ)፣ በምዕራብ ሐረርጌ፣ በመጨረሻም የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት እና የጅቡቲ አብያተ ክርስቲያናት ሊቀ ጳጳስ ኾነው በአባትነት አገልግለዋል፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያን በበላይ ሓላፊነት መርተዋል፡፡ #የብፁዕነታቸው_በረከት_ይደርብን፤ #ቅድስት_ጸሎታቸው_ትጠብቀን፤ አሜን፡፡

የአርሲ ነገሌ የመስቀል አደባባይና ባሕረ ጥምቀት የቦታው ምልክት መስቀል እንዲነሳ የኦሮሚያ ክልል ወስኗል Share/ሼር በምዕራብ አርሲ ሃገረ ስብከት አርሲ ነገሌ ቅድስት ቤተክርስቲያን ለበርካታ ዓመ
የአርሲ ነገሌ የመስቀል አደባባይና ባሕረ ጥምቀት የቦታው ምልክት መስቀል እንዲነሳ የኦሮሚያ ክልል ወስኗል Share/ሼር በምዕራብ አርሲ ሃገረ ስብከት አርሲ ነገሌ ቅድስት ቤተክርስቲያን ለበርካታ ዓመታት በመስቀል አደባባይና ባሕረ ጥምቀት ትጠቀምበት የነበረበት ይዞታዋ ላይ በርካታ አመታት የቦታው ምልክት የሆነው መስቀል እንዲነሳ የክልሉ መንግስት ወስኗል፡፡ ይህ አሳፋሪ ድርጊት ነው፡፡ መልስ ያጣው የመስቀሉ ጉዳይ ... ባለፈው በጽንፈኞች በኃይልና በጉልበት አንስተውት የነበሩ ቢሆንም ሕዝበ ክርስቲያኑ በላቀ መንፈሳዋ ወኔን ተላብሰው መልሰው መትከላቸው አይዘነጋም፡፡ የአርሲ ነገሌ የአደባባይ መስቀል ለበርካታ ዓመታት መንግሥት አነሳዋለሁ ምዕመናን አይነሳም በሚል ሰጣ ገባ እስከ ፌደራል ድረስ በመሄድ ባለበት ይቆይ አይነካ የተባለበት ደብዳቤ እንደሚገኝ መረጃዎች እየጠቆሙ ለኦርቶዶክስ ካላቸው የከፉ ጥላቻ የተነሣ መስቀል ይነሳ ብለው ወስነዋል፡፡ ታሪክን የመደለዝ ፀረ ኦርቶዶክስ እንቅስቃሴ ስለሆነ እንቃወማለን ፥ እንቃወማለን፡፡ (ከፈለገ ጎርጎርዮስ ገጽ የተወሰደ) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ይኩነኒ_በከመ_ትቤለኒ_ (#እንደ_ቃልህ_ይሁንልኝ_)፤ #ታኅሣሥ_22_ብሥራት_ … በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥ ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው
+4
#ይኩነኒ_በከመ_ትቤለኒ_ (#እንደ_ቃልህ_ይሁንልኝ_)፤ #ታኅሣሥ_22_ብሥራት_ … በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥ ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ፡፡ …… መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት። መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ያጸናሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል። እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ፥ እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፥ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፤ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና። ማርያምም። እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ አለች፡፡ መልአኩም ከእርሷ ሄደ… /የሉቃስ ወንጌል 1፥26-38/ ይህቺም እለት የበዐላት ሁሉ በኵር ናት፤ በእርሷም የዓለም ድኅነት ተጀምሯልና ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስም ከቸር አባቱና ይቅር ባይ ከሆነው ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብር ምስጋና ለዘላለሙ ይሁን አሜን፡፡ /ስንክሳር ዘታኅሣሥ 22/ በመዲና ከተማችን በአዲስ አበባ ታኅሣሥ_22_ብሥራት_የሚከበርባቸው፤ ፠ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል) ፠ መንበረ ፓትርያርክ ቅዱስ እንጦንስ (ኋላ ቅድስት ማርያም እየተባለ በመጠራት ላይ ያለ) ሲሆን በታላቁ ደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ካልዕ መልክአ ቅዱስ ገብርኤልን በማኅሌት በመቆም ይከበራል፡፡ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/med

SHAREEEEEEE, SHAREEEEEEE፤ እንወያይበት፡፡ ✣✤✣ #ክብር_ለሚገባው_ክብርን_እንስጥ_ለቅዱሳት_ሥዕላት_፡፡ (ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ፤ በማስተዋልም እንጓዝ) በቤተ ክርስቲያናችን ክብር
+3
SHAREEEEEEE, SHAREEEEEEE፤ እንወያይበት፡፡ ✣✤✣ #ክብር_ለሚገባው_ክብርን_እንስጥ_ለቅዱሳት_ሥዕላት_፡፡ (ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ፤ በማስተዋልም እንጓዝ) በቤተ ክርስቲያናችን ክብር ከሚገባቸውና በቅድስና ከሚጠሩት መካከል ቅዱሳት ሥዕላት አንዱና ዋነኛው ናቸው፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ ክብረ በዓላት በይበልጥም በጥምቀት በዓል ላይ፤ በተለይ በባነርና በቲሸርት ላይ የሚታተሙ ቅዱሳት ሥዕላት እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡ በባነርና በቲሸርት ላይ የሚታተሙ ቅዱሳት ሥዕላት ለፀሐይ፣ ለአቧራ፣ ለዝናብ፣ … የተጋለጡ፣ የሚሰቀሉበት ቦታም መጥፎ ሽታ ያለበትና ለቅዱሳት ሥዕላት አመቺ ያልሆነ፤ እንዲሁም ከክብረ በዓሉ በኋላም ተጣጥፈው የሚቀመጡ ስለሆነ፤ የታቦታት መተላለፊያ መንገዶችን የምታስውቡ የተለያዩ የወጣት ማኅበራት ወንድሞቻችንና እቶቻችን በባነርና በቲሸርት ላይ በዓሉን የሚገልጹ ትዕይንቶችና ጥቅሶችን እንጂ ቅዱሳት ሥዕላትን እንዳታትሙ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስም እናሳስባለን፡፡ ሌሎቻሁም ይህን መልእክት ላልሰማ አሰሙ!!!፡፡ (የለጠፍናቸው ፎቶች፤ የቀ.ደ.ሰ. መድኀኔ ዓለም ታቦት ከሚጓዝባቸው መንገዶች መካከል በፎቶ ካሜራ ዓይናችን ላይ የገቡልን ናቸው፤ ልብ በሉ በአጠቃላይ ታቦታት በሚያልፉባቸው መንገዶች ሁሉ ላይ የሚሰቀሉትን ቅዱሳት ሥዕላት!!!) #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

ለእመ አምላክ ፥ ለወላዲተ አምላክ፥ ለቅድስት ድንግል ማርያም ወርኀዊ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን ፥ አደረሳችሁ፡፡ (ፎቶው ላይ የምትመለከቷት፤ ደብረሲና ማርያም 700 ኛ ዓመቷን ኅዳር 21 ቀን
+3
ለእመ አምላክ ፥ ለወላዲተ አምላክ፥ ለቅድስት ድንግል ማርያም ወርኀዊ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን ፥ አደረሳችሁ፡፡ (ፎቶው ላይ የምትመለከቷት፤ ደብረሲና ማርያም 700 ኛ ዓመቷን ኅዳር 21 ቀን 2012 ዓ.ም ያከበረች ናት፤ የተመሠረተችው በ1312 ዓ.ም. በአፄ ዐምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት ነው፡፡ የምትገኘው ከጎንደር ከተማ በ64 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ጎርጎራ ከተማ ጣና ባሕር ዳር ላይ ነው፡፡ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፬_ (#ሰይጣን_የቅዱሳን_መላእክትን_ቃል_ምሥጢር_እንደሚሰማና_ #የሰማው_ከመደረጉ_በፊት_ለሰዎች_በመናገር_እንደሚያስት፤ #ሰይጣን_ከተፈጠረ_ጀምሮ_በዘመን_ብዛት_ሰውን_ያሚያስትበት_ብዙ_ጥበብ_እንዳለው፤ #የክርስቶስ_ሰው_መሆን_ከሰይጣን_የተሰወረ_እንደነበር) +አባ ጳውሊ፤ ወደ ሰማይ ወጥታችሁ የመላእክትን ቃል ትሰማላችሁን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ፈጽመን አንወጣም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ስለምንድነው የማትወጡት? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከክብራችን ከተዋረድን በኋላ በቧለሟልነት ሥልጣን ወደዚያ እንቀርብ ዘንድ አይፈቀድልንም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ሰዎች እናንተ ወደ ሰማይ እንደምትወጡና ከመላእክት ጋር እንደምትነጋገሩ የሚናገሩት ዋሽተው ነውን? አለው፡፡ ሰይጣን፤ መላእክት ከምስጋና በቀር አይናገሩምና አዎን ዋሽተው ነው አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ እንግዲያ ከመደረጉ በፊት አስቀድመህ ለሳኦል ምሥጢር የገለጥክለት በምን አውቀህ ነው? አለው፡፡ /፩ሳሙ.፳፰፥፲፯/ ዲያብሎስ፤ እግዚአብሔር ለሳሙኤል ሲነግረው ሰምቼ ነው አለው፡፡ /፩ሳሙ.፲፮፥፩) እግዚአብሔር ለመላእክቶቹ ምሥጢር ሲነግራቸው እኛም ባለንበት ሆነን እንሰማለን፡፡ ያን ጊዜ ፈጥነን ሄደን ከመደረጉ በፊት ለሰዎች እንነግራቸዋለን፡፡ ሰዎች ሁሉ በየሀገሩ እኛ የነገርናቸውንና በሕልም ያሳየናቸውን ይናገራሉ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ሰዎች ነገርህን እንደምን አምነው ይቀበሉሃል? የመልክህን ክፋት የመዓዛህን ክርፋት አያውቁምን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ሰዎች ሁሉ እንደ አንተ ክፉ መሰሉህ? ለአንተ ክፉ መስዬ እታይሃለሁ እንጂ በዚህ ዓለም መዓዛዬን ለማሽተትና መልኬን ለማየት እኔን የሚሹ ብዙ ሰዎች እንዳሉ እነግርሃለሁ፡፡ እነርሱ ወደ እኔ መጥተው እገለጽላቸው ዘንድ ይለምኑኛል እንጂ እኔ ወደ እነርሱ አልሔድም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ሰዎች ስለምን ይወዱሃል? ይህ የሚሆነው ለምንድን ነው? ዲያብሎስ፤ እኔን ለማየት በሚፈልጉት መልክ ተመስዬ በመገለጽ ስለማስደስታቸው ነው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ መልክህን መለወጥ እንደምን ይቻልሃል አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ይህ የሚያስደንቅ አይደለም ሰይጣን የብርሃን መልአክን ይመስላል ብሎ ጳውሎስ የተናገረውን አልሰማህምን፡፡ /፪ቆሮ.፲፩፥፲፬/ ++አባ ጳውሊ፤ የማታውቀውን ምሥጢር ማስመሰል እንደምን ይቻልሃል አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በዘመን ብዛት የሰበሰብኩትና የማውቀው ብዙ ጥበብ አለኝ፡፡ #ነገር ግን የክርስቶስ ሰው መሆን ብቻ ተሰወረብኝ እንጂ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ የክርስቶስ ሰው መሆን ስለምን ተሰወረብህ? ዲያብሎስ፤ ከእኔ የተሰወረበትን ምክንያት አላውቅም፡፡ ነገር ግን አውቄስ ቢሆን ክፉና በጎ ለይተው ያላወቁ ብዙ ሕፃናትን በሄሮድስ አድሬ ባላስገደልኩም ነበር አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ በገዳመ ቆሮንቶስ አንተ ፈትነኸዋልና አላውቅም አትበል አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ በሰውነቱ ስለሚሠራው ሥራ እንደ ነቢይ፥ እንደ ንጉሥ ይመስለኝ ነበርና ባውቅም እጠራጠር ነበር፡፡ ስለዚህ እፈትነው ዘንድ በእርሱ ላይ ተነሳሁ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ እርሱ በእውነት አምላክ መሆኑን ያወቅኸው መቼ ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ኃይሌን እስከሚያደክመው ድረስ አላወቅሁም ነበር፡፡ መላእክት ሲያመሰግኑት፥ ሙታን ሲነሡ፥ ምድር ሲነዋወጥ፥ ፀሐይ ሲጨልም አየሁ፤ ያን ጊዜ የዓለም ብርሃን፥ የፍጥረታት ፈጣሪ እርሱ በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ አወቅሁ አለው፡፡ #የሰይጣናት_አለቃና_ታዛዥ_እንዳላቸው፤ #ገሃነም_ስለመኖሩና_ዲያብሎስ_ለምን_ንስሐ_እንደማይገባ) #ክፍል_፭.…#ይቀጥላል_ይጠብቁን/ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

በቀ.ደ. ሰ መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. የታኅሣሥ 19 የክብረ በዓሉ ድባብ ይህን ይመስላል፡፡
+7
በቀ.ደ. ሰ መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. የታኅሣሥ 19 የክብረ በዓሉ ድባብ ይህን ይመስላል፡፡

25ት የሚሆኑ በመናገሻ ከተማችን በአዲስ አበባ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል የሚከብርባቸው ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት (ያልጠቀስናቸውን ጨምሩበት፤ ፎቶም ካላችሁ ላኩልን ወይም ለጥፉልን፡፡) ፠ መ.መ.ገ. መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ በ1889 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ፠ አስኮ ቅዱስ ገብርኤል፤ ፠ ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል፤ ፠ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል) ፠ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ፠ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኮተቤ ዳግማዊ ቁልቢ ደብረ ልዑል ቅዱስ ገብርኤል በ.ክ. ፠ ደብረ ገነት ፉሪ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ጋራ ኦዳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አንቆርጫ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ፈረንሣይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ አቃቂ ፈለገ ግየን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ (የቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. በድርብነት በውስጥ አለ) ፠ ቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ፠ ፠ …… ሌሎችንም ጨምሩባቸው፡፡ /እንደ መነሻነት ሐሳቡን የወሰድነው ከገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ ሰ/ት/ቤት የሰሌዳ መጽሔት ‹‹ቀጠሮ›› ከሚለው ዐምድ ነው፡፡) በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem