Ministry of Urban and Infrastructure 🇪🇹🇪🇹
Відкрити в Telegram
This is the official Telegram page of Ministry of Urban and Infrastructure
Показати більше9 932
Підписники
+524 години
+67 днів
+11330 днів
Архів дописів
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
🇪🇹 Come to Ethiopia — get a 7-year age discount!
It’s 2026 in much of the world, but on September 11, Ethiopia welcomed 2019.
Come for the 7-year age discount. Stay for the ancient history, epic landscapes, legendary coffee, vibrant culture, and unforgettable hospitality.
Ethiopia — where time is younger and the adventure is timeless.
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
በ18ኛው የብሪክስ ጉባኤ የነበረን ቆይታ ቅኝት፦
አዲሱን ዓመት የጀመርነው ስትራቴጂካዊ ጥቅሞቻችን በተረጋገጡበት እና የአፍሪካ ድምፅ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ባለበት ታሪካዊ ስኬት ነው!
🇪🇹
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
Economic uncertainty is testing our countries. BRICS has already reshaped
the global conversation. Our responsibility now is to help shape a fairer international system and widen economic opportunity.
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
የብሪክስ ጉባኤ ሁለተኛው ቀን ላይ ከካዛኪስታን ፕሬዚዳንት ቃሲም ጆማርት ቶካዬቭ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገናል።
በዲጂታላይዜሽን፣ በንግድና ኢንቨስትመንት እንዲሁም በመከላከያ መስኮች የትብብር ዕድሎችን ለማስፋት እና በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን አጋርነት ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ መክረናል።
🇪🇹 🇰🇿
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
ከብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን የቪየትናም ጠቅላይ ሚኒስትር ሌ ሚን ሁንግን አግኝቸ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። በኢትዮጵያ እና ቪየትናም መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር እና የጋራ ትብብራችንን ማስፋት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መክረናል።
🇪🇹 🇻🇳
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+1
ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተገናኝተን በኢትዮጵያ እና ሩሲያ መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።
ውይይታችን በመከላከያ እና ደኅንነት፣ በንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ በትምህርት እንዲሁም በቴክኖሎጂ መስኮች ያለንን ትብብር ለማሳደግ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋገጥንበት ነው። እንዲሁም የትምህርት ልምድ ልውውጦችን ማስፋት፣ በባህል እና በሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ላይ ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያ መክረናል።
በተጨማሪም ለኮፕ 32 በምናደርገው ዝግጅት ያለንን አጋርነት ጨምሮ ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በልማት ግቦች ዙሪያ ትብብሮችን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ ተወያይተናል። በወል ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረቱ የንግድ እና የኢኮኖሚ ልውውጦችን ይበልጥ ለማስፋፋትም በጋራ ለመሥራት ተስማምተናል።
🇪🇹 🇷🇺
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
ከ18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን፣ ከአቡ ዳቢ አልጋ ወራሽ ከልዑል ሼህ ኻሊድ ቢን ሙሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር መክረናል።
በቆይታችንም በዋና ዋና የብሪክስ ቅድመ-አጀንዳዎች እና በኢትዮጵያና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን ሁለገብ ትብብር የበለጠ በሚያጠናክሩ ሂደቶች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።
🇪🇹 🇦🇪
Repost from FDRE Government Communication Service
+3
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
"ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት በሚል መሪ ቃል በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ በሚገኘው 18ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ አካል በመሆናችን ኩራት ይሰማናል።
በብሪክስ አባል ሀገራት ዘንድ ሀብት፣ ቴክኖሎጂ እና ሰፊ ገበያ አለን፤ አሁን ያለው መልካም ዕድል እነዚህን አቅሞች በማስተሳሰር የላቀ እሴት መፍጠር እና ይህ እሴት ደግሞ ሀብቱ በሚገኝበት ቦታ መመረት እንዲችል ማድረግ ነው። ኢትዮጵያ በማዕድን ልማት፣ በታዳሽ ኃይል እና እያደገ በሚገኘው የኢንዱስትሪ መሠረቷ ላይ እነዚህን አጋርነቶች ለመገንባት ዝግጁ ናት።
በተጨማሪም በአሠራር ሥርዓቶቻችን ውስጥ ጽናትን መገንባት፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የአህጉራችንን ፍላጎት እንዲያገለግል ማድረግ፣ አስተማማኝ የዕዳ እፎይታ ሒደትን ማሳደግ እንዲሁም የአየር ንብረት ጥበቃ ሥራዎችን ከኢኮኖሚ ሽግግር ጋር ማስተሳሰር ይኖርብናል።
የብሪክስ መድረክ የጋራ ትብብርን ወደ የጋራ እሴት፣ ጽናት እና ዘላቂ ዕድገት የመለወጥ ሰፊ አቅምና ቁርጠኝነት አለው።"
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication
Repost from FDRE Government Communication Service
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከብሪክስ ጉባኤ ጎን ጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ያደረጉት ውይይት
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
ከብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም ጋር ተናኝተን መክረናል።
በሕዳር 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ካደረጉት ታሪካዊ ጉብኝት የተገኘውን መልካም ዕድል ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተናል።
ውይይታችን ኢንቨስትመንትን፣ ቱሪዝምን፣ የታዳሽ ኃይል አጋርነትን ማስፋፋት እና ወደ ኮፕ 32 በሚደረገው ጉዞ ላይ ያለንን ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። በተጨማሪም በማሌዢያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት፣ ምርታማነት እና የአምራች ዘርፍ ተሞክሮዎችን መውሰድ በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያ መክረናል።
ኢትዮጵያና ማሌዢያ ጠንካራ የኢኮኖሚ አጋርነት ለመመስረት የሚያስችል ከፍተኛ አቅም አላቸው፤ ይህም በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በክህሎት እና በዘላቂ ልማት ማዕቀፎች አዳዲስ ዕድሎችን የሚፈጥር ነው።
🇪🇹 🇲🇾
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
በብሪክስ ፕላስ የቤተሰብ መድረክ ማዕቀፍ ውስጥ፣ ከኢራኑ ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ጋር ተወያይተናል።
ከጉባኤው ጎን ለጎን ባደረግነው ውይይት በቀይ ባሕር አካባቢ ባሉ ወቅታዊ ሁነቶች እና አጠቃላይ በቀጣናው የደኅንነት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ የውይይትን አስፈላጊነት እና የቀጣናውን መረጋጋት እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያም መክረናል።
🇪🇹 🇮🇷
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+1
በሕንድ ይፋዊ የሥራ ጉብኝቴ ከጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር በመገናኘት፣ የኢትዮጵያ-ሕንድ አጋርነትን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ፍሬያማ ሃሳብ ተለዋውጠናል።
ውይይታችን የመከላከያ ትብብርን ማሳደግ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የአቅም ግንባታ፣ የማዕድን ልማት እና ወደ ኮፕ 32 በሚደረገው ጉዞ ላይ ያለንን አጋርነት ማጠናከር በሚሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እነዚህ መስኮች በተግባር የታገዘ ትብብራችንን ይበልጥ ለማሳደግ እና ለሕዝቦቻችን አዳዲስ ዕድሎችን ለመፍጠር ከፍተኛ አቅም አላቸው።
ኢትዮጵያና ሕንድ ጥልቅ ታሪካዊ ትስስር፣ የዘመናት የባህል ግንኙነት እና በሕዝቦቻችን መካከል ጠንካራ ወዳጅነት አለን፤ ይሁን እንጂ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያሉት በርካታ አቅሞች ገና ያለተነኩ ናቸው። ያለንን የጋራ ታሪክና ትብብር በቴክኖሎጂ፣ በክህሎት፣ በኢንቨስትመንት፣ በዘላቂ ልማት እና ይበልጥ በጠነከረ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ላይ ወደተመሠረተና የላቀ የጋራ ተጠቃሚነትን ወደሚያረጋግጥ አጋርነት ለመለወጥ አሁን ትክክለኛው ጊዜ ነው ብዬ አምናለሁ።
🇪🇹 🇮🇳
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+9
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ጉዞ፡ በተግባር የታነጸበት ስራ
ዛሬ በሞጆ ተገኝተን ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬት ትልቅ ሚና የሚጫወተውንና በ60 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ዘመናዊ የሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፍያ የመጀመሪያ ምዕራፍ አስመርቀናል። ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በዓመት እስከ 1 ሚሊዮን ባለ 20 ጫማ ኮንቴነሮች የማስተናገድ አቅም ያላቸው ጣቢያዎችና ዘመናዊ መጋዘኖች ያሉት ሲሆን፣ የደረቅ ብትን ጭነቶችን በሀገር ውስጥ እንድናሽግ ማስቻሉ፣ የውጭ ምንዛሬን ከመቆጠብ ባለፈ ለዜጎቻችን ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል። የማዕከሉን የአሰራር ፍጥነት ለማሳደግ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የተተከለው የባቡር ላይ ክሬን ከባቡር መስመር የሚደረገውን የኮንቴነር ዝውውር በከፍተኛ ፍጥነት ያከናውናል።
ሙሉ አሰራሩ በዘመናዊ ዲጂታል መሰረተ ልማት የተሳሰረ በመሆኑ፣ ለተገልጋዮች ፈጣን እና አስተማማኝ አገልግሎትን ያሳልጣል። ይህ ማዕከል ከኢትዮ-ጅቡቲ መስመር ባሻገር ኢትዮጵያን፣ ደቡብ ሱዳንን እና ዩጋንዳን የሚያስተሳስረው የ‘ደሱ’ ኮሪደር አካል ሲሆን፤ ይህም ሀገራችን በዓለም አቀፍ የሎጂስቲክስ ደረጃ ላይ ያላትን ስፍራ የሚያሻሽልና የቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስራችንን ወደ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ የሚያሸጋግር ትልቅ ድል ነው።
የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ መረጃ መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የስምምነት ፊርማ ተፈራረመ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም፣ (ከመልሚ)
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር የስራ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር እና የትብብር ስምምነት የፊርማ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ፡፡
ስምምነቱን የተፈራረሙት በሚኒስቴር መ/ቤቱ በኩል የመሬትና ካዳስተር መሪ ስራ አስፈጻሚው አቶ ብዙዓለም አድማሱ በመግቢያቸው ላይ እንደተናገሩት ስምምነቱ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አካል እንደሆነና ሀገራዊ የመሬት መረጃዎችን በአንድ ቋት በማስተሳሰር የዜጎችን፣ የመንግስትን እና የባለሃብቱን ጥቅም ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነና ይህም በሀገራችን የከተማ መሬት አስተዳደርና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞን ወደ ትልቅ ምዕራፍ የሚያሸጋግር እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ከዚሁ ጋር በማያያዝ ስምምነቱ የሀገራችንን የከተሞች የመሬት መረጃ ሥርዓት ለማዘመን፤ የካዳስተር ምዝገባዎችን ዘመናዊና አስተማማኝ ለማድረግ እንዲሁም የመሬት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ የታሰበውን አገራዊ ራዕይ ለማሳካት የሚረዳ ነው ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ መረጃ መረብ ደህንነት አስተዳደርን ወክለው የተገኙት አቶ ቢኒያም አበባው በበኩላቸው ስምምነቱ የሲስተም ልማትን በማዘመን ዲጂታል ካዳስተርን ወደ ተቀናጀ ሁሉን አቀፍ ካዳስተር በማሳደግ ለሁሉም ከተሞች ለማድረስ ያለመ በመሆኑ ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ስምምነቱ የመሬት ምዝገባን ዲጂታላይዝ በማድረግ የካዳስተር እድገት ደረጃዎችን ለማስጠበቅ፤ በዋናነትም ከህጋዊ እና ከፊዚካል ካዳስተር ወደ ተቀናጀ ሁሉን አቀፍ ካዳስተር የማሸጋገር ምዕራፍ እንደሆነና ይህም የንብረት ግብር አሰባሰብን ለማጠናከርና የከተሞችን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ፤እንዲሁም የዜጎችን የይዞታ ዋስትና ለማረጋገጥ እና የንብረት መብትን ለማስከበር የሚረዳ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ለመላው ኢትዮጵያውያን አዲሱ ዓመት 2019 ዓ.ም የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የብልጽግና፣ የደስታ ዘመን እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልጻል።
መልካም አዲሰ ዓመት
