880
Підписники
Немає даних24 години
-27 днів
-2630 днів
Архів дописів
Repost from N/a
በቀን 28/06/2017ዓም
በጨፌ ትምህርት ቤት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ114ኛ ጊዜ እና በሀገር ደረጃ ለ49ኛ ጊዜ የሚከበረውን የሴቶች ቀን (March 8) በደማቅ ሁኔታ ተከብረ። በዓሉ ፈጣን እና ቀልጣፋነት ያለው አገልግሎት በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል በሚል መሪ ቃል የሚከበር ነው።
በፕሮግራሙ ላይ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጽ/ቤት የአቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ውቢት ጌቱ, የትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ታደለ ዱሬሳ, የሴቶች እና ህፃናት ጽ/ቤት ባለሙያ እና የትምህርት ቤቱ የተለያዬ አደረጃቶች ተገኝተዋል። በትምህርት ቤቱ የስርዓተ ፆታ ክበብ አባላት አማካኝነት የተለያዩ አዝናኝ እና ትምህርት ሰጪ ፕሮግራሞች ተላልፈዋል።
Repost from cheffie primary school 2013
ቀን 01/06/2017ዓም
ለጨፌ ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች በሙሉ:-
የ2017ዓም የትምህርት ዘመን የ2ኛው መንፈቅ ዓመት ትምህርት የሚጀምረው ሰኞ በቀን 03/06/2017ዓም መሆኑን በደስታ እናበስራለን።
በዕለቱም መደበኛ ትምህርት የሚጀምር ስለሆነ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶችን አሟልተው እና ሙሉ ዝግጅት አድርገው እንዲመጡ እናሳውቃለን።
ለት/ቤታችን የ6ኛ ክፍል እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
📚 ⭕️ የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተናን ይመለከታል
✅ የ2017 ዓ.ም የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተና መረጃ ለ6ኛ ና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች
1️⃣ የ6ኛ ክፍል በተመለከተ
✍️ በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-
👉 አማርኛ/አፋን ኦሮሞ
👉 English
👉 ሒሳብ
👉 አካ/ሳይንስ እና
👉 ግብረ-ገብ
✍️ የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተና የሚዘጋጀው ከ6ኛ ክፋል first semester (5ኛ ክፍልን first semester ይጨምራል)
2⃣የ8ኛ ክፍል በተመለከተ
✅ የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተና የሚዘጋጀው ከ8ኛ ክፍል first semester (ከ7ኛ ክፋልን first semester ይጨምራል)
✍️ በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-
👉 English
👉 አማርኛ/አፋን ኦሮሞ
👉 Mathematics
👉 Social Studies
👉 General Science
👉 Citizenship
📚 በመሆኑም የፈተና ወቅት እየተቃረበ በመሆኑ ተማሪዎች በዚህ መረጃ መሰረት በአግባቡ ማጥናት ይጠበቅባቸዋል::
⭕️ በዚህ መረጃ መሠረት ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።
t.me/seed_coin_bot/app?startapp=723808219
SEED App – Meme Telegram app backed by top investors.
🔥 Burning SEED for inactive users after more than 30 days.
🚀 20M users in just 1 month!
🏆 Top-tier listing this December.
Don’t miss out — now’s the perfect time to join! 🎉
#የ6ኛ እና #8ኛ ክፍል ደረጃ የተማሪዎች ጥያቄ እና መልስ ውድድር ተደረገ
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር ትምህርት ፅ/ቤት የ2017 ትምህርት ዘመን በሁለቱም ስርዓተ ትምህርት #የ6ኛ እና #8ኛ ክፍል ደረጃ የተማሪዎች ጥያቄ እና መልስ ውድድር አደረገ።
የወረዳው የትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ዱሬሳ እንደተናገሩት ውድድሩ በአስተዳደራችን ተገድቦ የሚቆም ብቻ ሳይሆን በክፍለ ከተማ ደረጃ እንደሚከናወን በመጠቆም በጥያቄና መልስ ውድድሩ አሸናፊዎቹ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ መምህራን እና ወላጅም ጭምር እንደሆኑ አስረድተዋል።
በየክፍል ደረጃ እና ትምህርት ቤት ደረጃ ከ1ኛ-3ኛ የወጡትን ተማሪዎችን እና ትምህርት ቤቶችን በመሸለም ውድድሩን ተጠናቋል።
በትምህርት ቤት ደረጃ 1ኛ ጨፌ 2ኛ ምስራቅ 3ኛ ማሪዞና በመውጣት የዋንጫ እና የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆነዋል።
በ8 ክፍል 1ኛ ዲቦራ ወርቅነህ 2ኛ ሱመያ መሀመድ 3ኛ ሀናን ሙስጠፋ
በ6 ክፍል በአፋን ኦሮሞ 1ኛ ዮናስ ደኑ
2ኛ ሀብታሙ ደኑ 3ኛ ሴና ባለሚ
በ6 ክፍል አማርኛ 1ኛ ኬናን ጭንዲ
2ኛ ኤልዳና እንዳሻው 3ኛ ሀበን ፍቃዱ በመሆን አሸናፊ ሆነዋል።
ለሚ ኩራ ወረዳ 03 ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 8/2017 ዓ/ም
+6
ቀን 05/04/2017ዓ.ም
በጨፌ ቅድመ አንደኛ, አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት ተደረገ።
የውይይቱ አጀንዳዎች
1:- የሒሳብ እና እንግሊዝኛ ትምህርት የአንደኛ ዙር አጋማሽ ፈተና ውጤት ትንተና ቀርቧል።
2. እየተሰጠ ያለውን ማጠናከሪያ ትምህርት ትምህርት እያመጣ ያለውን ለውጥ መገምገም
3. የአራትዮሽ ስምምነት ያለበትን ደረጃ መገምገም ናቸው።
በውይይቱ ላይ የወረዳ 03 ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ታደለ ዱሬሳ ተገኝተው የእንግሊዝኛ እና የሒሳብ ትምህርት የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የጋራ ርብርብ ማድረግ አለባቸው ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ሃላፊው አክለውም በስነምግባር የታነፀ ተማሪ በውጤቱም የተሻለ ይሆናል በማለት ወላጆች የልጆቻቸው የስነ ምግባር ሁኔታ መከታተል እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
በውይይቱ ላይ ከወላጆችም ጥያቄዎች እና አሰተያየት ተነስተው
ርዕሰ መምህርት ኤልሳቤጥ አማካኝነት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
+6
ቀን 05/04/2017ዓ.ም
በጨፌ ቅድመ አንደኛ, አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት ተደረገ።
የውይይቱ አጀንዳዎች
1:- የሒሳብ እና እንግሊዝኛ ትምህርት የአንደኛ ዙር አጋማሽ ፈተና ውጤት ትንተና ቀርቧል።
2. እየተሰጠ ያለውን ማጠናከሪያ ትምህርት ትምህርት እያመጣ ያለውን ለውጥ መገምገም
3. የአራትዮሽ ስምምነት ያለበትን ደረጃ መገምገም ናቸው።
በውይይቱ ላይ የወረዳ 03 ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ታደለ ዱሬሳ ተገኝተው የእንግሊዝኛ እና የሒሳብ ትምህርት የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የጋራ ርብርብ ማድረግ አለባቸው ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ሃላፊው አክለውም በስነምግባር የታነፀ ተማሪ በውጤቱም የተሻለ ይሆናል በማለት ወላጆች የልጆቻቸው የስነ ምግባር ሁኔታ መከታተል እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
በውይይቱ ላይ ከወላጆችም ጥያቄዎች እና አሰተያየት ተነስተው
ርዕሰ መምህርት ኤልሳቤጥ አማካኝነት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
