EthioTube
Відкрити в Telegram
ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ። Follow us on other our social media networks: Facebook.com/EthioTube Twitter.com/EthioTube Youtube.com/EthioTube Instagram.com/EthioTube
Показати більше8 085
Підписники
-324 години
-247 днів
-9330 днів
Архів дописів
8 085
ማንችስተር ዩናይትድ በ10 ተጨዋቾች ጨዋታውን ለመጨረስ በተገደደው ማንችስተር ሲቲ በሜዳው 1-0 ሽንፈትን ተከናነበ
ማንችስተር ዩናይትድ ዘንድሮ ስንተኛ ሆኖ ይጨርሳል?
#PremierLeague #ManchesterUnited #ManchesterCity #EPL #Football
8 085
እነ ክርስቲያን ታደለ ተፈቱ
አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ ከ600 በላይ እስረኞች ከእስር መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አሳወቀ።
ዛሬ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲፈቱ የተደረጉት እስረኞች የታገዱ መብቶቻቸው እንዲመለሱ ተደርጓል።
ኢሰመኮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ የፖለቲከኛ እስረኞቹ እንዲፈቱ ከመንግሥት ጋር ላለፉት 5 ወራት ጥረት ሲደረግ ነበር ብሏል።
#Ethiopia #EthiopianNewYear #ChristianTadele #PoliticalPrisoners #EthiopianPolitics #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
የበሬ ዋጋ እስከ 300 ሺህ ብር
1 ኪሎ የበሬ ሥጋ በ1,200ብር ለሽያጭ እንደሚቀርብ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አስታውቋል። ድርጅቱ 4500 የቁም የእንስሳትን እርድ አከናውናለሁ ብሏል።
የከተማዋ ነዋሪዎችም በግ እና ፍየል ማሳረድ ከፈለጉ 300 ብር፣ እንዲሁም በሬዎችን ደግሞ በ2100 በድርጅቱ ማሳረድ እንሚችሉ ጠቁሟል።
ለዐዲሱ ዓመት ከ4 ሚሊዮን በላይ እንቁላል ለገበያ እንደሚቀርብ የገለጸው ደግሞ የአዲስ አበባ አርሶአደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ነው።
ኮሚሽኑ በሸማቾች ኀብረት ሥራ ማኀበራት በኩል አንድ እንቁላል ከ15 እስከ 22 ብር ለማኅበረሰቡ እየቀረበ መሆኑን አስውቋል።
በከተማዋ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የቁም እንሰሳ ገበያ የበሬ ዋጋ ከ 90 ሺህ እስከ 300 ሺህ ብር እየተሸጠ ነው።
በዚሁ ገበያ ትልቅ ሙክት በግ ደግሞ ከ 35 ሺህ እስከ 40 ሺህ ብር ለገበያ ቀርቧል።ዝቅተኛ ጠቦት በግ ከ10 እስከ 20 ሺህ ብር እየተሸጠ ይገኛል።
በተመሳሳይ፣ ሙክት ፍየል ዋጋ ከ35 እስከ 45 ሺህ ብር ሲሸጥ፤ ዝቅተኛ ጠቦት ፍየል ከ15 እስከ 20 ሺህ ብር ዋጋ አለው ተብሏል።
#Ethiopia #Enqutatash #EthiopianNewYear #HolidayMarket #EthiopianEconomy #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
የነሐሴ ወር የዋጋ ግሽበት 15.1 በመቶ ሆኖ ተመዘገበ
የዘንድሮ ዓመት የነሐሴ ወር የዋጋ ግሽበት 15.1 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ።
ይህ መጠን ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነፃጸር ከፍ ያለ ጭማሪ አለው። በ 2017 ዓ.ም. የነሐሴ ወር የነበረው የዋጋ ግሽበት 13.6 በመቶ ነበር።
በዚህ ወር በሀገሪቱ ምግብ እና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 14.9 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
አትክልት 12.1 በመቶ፣ ስጋ 22.6 በመቶ፣ የወተት እና እንቁላል ተዋጽኦ 18.7፣ዘይትና ቅቤ 18.8፣ ዳቦ እና እንጀራ 8.1 በመቶ ያህል ዋጋቸው ጨምሯል።
ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶች ደግሞ በ 15.4 በመቶ ዋጋቸው አሻቅቧል ሲል ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል።
#Ethiopia #EthiopianEconomy #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን አስተዳደር ለማስወገድ የተፈጠረው ጥምረት በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ የህወሓት ሊቀመንበር ተናገሩ
የተፈጠረው ጥምረትና ትብብር ተቋማዊ ሁኗል፤ የራሱ ስያሜና አመራር ያለው ነው ሲሉ የትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል በሰጡት መግለጫ አስታወቁ።
ዶ/ር ደብረፂዮን አያይዘውም መቀላቀል የሚገባቸው ሌሎችም የጥምረት ሃይሎች እንዳሉና በቅርቡ ይፋ እናድርገዋለን ብለዋል። አክለውም የተፈራረምንበት ሰነድም አለ ማለታቸው ተገልጿል።
በአጠቃላይ አሁን ወዳጅ ድርጅቶችና ሕዝቦች አሉን። ይህ ጥምረት ተጀምሯል፤ በጋራም እየሠራ ነው። ስለዚህ ወደ ኋላ የምቀለበስበት ሁኔታ የለም ሲሉ ተናግረዋል።
"ይህ ጥምረት እኛ በፈለግነው ጊዜ የምንለያየው ሳይሆን፣ የራሱ አካሄድ ያለው ነው። ይህ ማለት ጠላትን ወይም አገዛዙን ካስወገድን በኋላ ምን እንደምናደርግ በስምምነትና በመግባባት ላይ እንደሚሆን ተደርሷል ወደ ማይቀለበስና ማይሰበር ደረጃ ተሸጋግሯል" ማለታቸው ተሰምቷል።
ደብረጽዮን (ዶ/ር) " አንድ፣ ሁለት ተብለው የተቀመጡ አማራጮችም አሉ" ሲሉ መናገራቸውን ትግራይ ቴቪ ዘግቧል።
#Ethiopia #TPLF #DebretsionGebremichael #AbiyAhmed #PMAbiy #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
ታዋቂው ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው ለዐዲስ ዓመት “ሃሳብን በዜማ” የሚል የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው
ላለፉት 30 ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ አያሌው በ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ የሙዚቃ አልበም ለአድማጭ ሊያቀርቡ እንደሆነ ተናግረዋል።
“ሃሳብን በዜማ” የሚል መጠሪያ የሰጡት አልበም 12 ሙዚቃዎችን የያዘ ሲሆን “የፖለቲካ ፍልስፍናዬን፣ በሌሎች ዘርፎችም ያለኝን እይታ የምገልጽበት ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ ሙዚቃ በቀን አንድ የሚለቀቅ ሲሆን በ 12 ቀን ወስጥ ሁሉም ሙዚቃ ለአድማጭ ይቀርባል ብለዋል።
“ለዐዲስ ዓመት አንድ አነስተኛ ስጦታ አለኝ የኪነ ጥበብ ሰው ባልሆንም አንዳንድ ዝንባሌዎች አሉኝ ሃሳብን በዜማ የሚል አልበም ሰርቻለሁ” ሲሉ በጉዳዩ ላይ በሰጡት አጠር ያለ መግለጫ አሳውቀዋል።
#Ethiopia #EthiopianMusic #EthiopianPolitics #LidetuAyalew #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
አርሰናሎች ለንደን ቀይ ነው እያሉ ነው
ዮናይትድ ነጥብ በጣለበት ቀን መድፈኞቹ ቸልሲን 2ለ1 ረቱ
#PremierLeague #Arsenal #EPL #Football #Chelsea
8 085
በአዲስ አበባ ከተማ 81 አዳዲስ የሰንበት ገበያ ማዕከላት ይከፈታሉ ተባለ
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የሰንበት ገበያ ማዕከላትን ቁጥር ለመጨመር 81 አዳዲስ የገበያ ሥፍራዎች እንደሚከፈቱ የከተማዋ ንግድ ቢሮ አስታውቋል።
በአዲስ አበባ የሚስተዋለውን የዋጋ ንረት ለመቆጣጠር በሚል 264 የሰንበት ገበያ ማዕከላት አገልግሎት እየሰጡ ነው። በ 2019 ዓ.ም. ይህን ቁጥር ወደ 345 ለማሳደግ ታቅዷል።
በቅዳሜ እና በእሁድ ገበያዎች በሕገወጥ መንገድ የተሰማሩ የንግድ ድርጅቶች ላይ ሕጋዊ እርምጃተወስዷል ተብሏል።
የንግድ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደተናገሩት ከ 24,500 በላይ ድርጅቶች፣አመራሮች እና ሠራተኞች ላይ እርምጃ ተወስዷል።
መጪውን ዐዲስ ዓመት ተከትሎ ሁሉም የሰንበት ገበያ ሳምንቱን ሙሉ የአትክልት እና ፍራፍሬ፣የሰብል፣የፋብሪካ እንዲሁም ሌሎችምርቶች ለሸማቾች ያቀርባሉ መባሉን ሪፖርተር ዘግቧል።
#Ethiopia #AddisAbaba #Market #Economy #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
ግብይትን ፈታኝ ያደርገው ያረጀው የአስር ብር ኖት
አብዛኛው የኢትዮጵያ 10 ብር ኖት ያረጀ እና የተቀደደ መሆኑ በሚፈጸሙ ግብይቶች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ፈጥሯል። ፎርቹን ጋዜጣ በጉዳዩ ላይ በሰራው ዘገባ። አነስተኛ መጠን ያላቸው የብር ኖቶች ላይ ያለው ፍላጎት ከፍተኛ ቢሆንም አቅርቦታቸው ግን ዝቅተኛ መሆኑን አመላክቷል። ለአብነት አዋሽ ባንክ እነዚህን የብር ኖቶች በተመለከተ ያቀረበው ጥያቄ ለ 6 ወራት ያህል መልስ ሳያገኝ መቆየቱን ገልጿል።
ስማቸው ያልተጠቀሰ አንድ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኃላፊ ይህን አስተያየት ይጋሩታል። በ2013 ዓ.ም. ሀገሪቱ የብር ኖት ለውጥ ከተደረገ በኋላ አዳዲስ የ10 ብር ኖቶች ሲሰራጩ እንዳላዩ የገለጹት እኚህ ኃላፊ፤በወቅቱ ይህ የገንዘብ ኖት ከነበረው ፍላጎት በላይ በሆነ ከፍተኛ መጠን ለባንኮች ቀርቦ እንደነበር አስታውሰዋል።
ጋዜጣው ያናገራቸው በብሔራዊ ባንክ የሚሰሩ አንድ ምንጭ፤ የመጀመሪያው የቀረበው የ 10 ብር ኖት ከነበረው ፍላጎት ጋር ተመጣጣኝ የነበረ ቢሆንም፣ ከዚያን ጊዜ ወዲህ ግን ፍላጎቱ እያደገ መጥቷል ብለዋል።
እንደ ብሔራዊ ባንክ መረጃ ከሆነ፤ በአውሮፓውያኑ ሰኔ 2025 መጨረሻ በስርጭት ላይ የነበረው የብር ኖት መጠን 346.9 ቢሊዮን ብር ገደማ የነበረ ሲሆን፤ ይህም ከአንድ ዓመት በፊት ከነበረው 257.2 ቢሊዮን ብር ብልጫ አለው።
ከዚህ ውስጥ ባለ 200 ብር ኖት 64.4 በመቶውን በመያዝ ከፍተኛውን ድርሻ ሲኖረው፤ ባለ 100 ብር ኖት በ27.3 በመቶ፣ እንዲሁም ባለ 50 ብር ኖት በ5.5 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
#Ethiopia
8 085
🚨 «የጫት ጉዞ በዲሲ አውሮፕላን ማረፊያ ተቀጨ!» ✈️📦
ጉዞው ከፓሪስ እና ከካዛብላንካ ተጀምሮ መዳረሻውን አሜሪካ ቨርጂኒያ ግዛት አድርጎ ነበር።
በዋሽንግተን ዳላስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ (Dulles International Airport) ያረፉት ሁለት መንገደኞች፣ እያንዳንዳቸው ሰባት ሰባት ግዙፍ ሻንጣዎችን አንጠልጥለው የመፈተሻውን መስመር ሲያልፉ በጉምሩክ እና የድንበር ጥበቃ (CBP) ፖሊሶች ጥርጣሬ ያጭራሉ።
ሻንጣዎቹ ተከፍተው ሲፈተሹ የታየው ነገር አስገራሚ ነበር—ሙሉ በሙሉ በጥቅል የደረቁ ቅጠሎች ተሞልተዋል! የተደረገው ፈጣን ምርመራም ቅጠሉ ጫት (Khat) መሆኑን አረጋገጠ።
⚖️ የተያዘው የጫት መጠንና ዝርዝር፡
- ክብደት፦ 764 ፓውንድ (ወደ 346 ኪሎ ግራም ገደማ)
- የገበያ ግምት፦ ወደ 90,000 የአሜሪካ ዶላር
- ተጠርጣሪዎች፦ የ33 ዓመቶቹ ዶሪያን ላሚን ቻም እና ዳማ ጃዋራ
የአሜሪካ የድንበር ቁጥጥር ባለስልጣናት ጫቱን ሙሉ በሙሉ ሲወርሱ፣ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች በቨርጂኒያ ስቴት ፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው በከባድ ወንጀል (ህገ-ወጥ እፅ በማዘዋወር) ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የጉምሩክ ባለስልጣናት በሰጡት ማሳሰቢያ፡ «የአደንዛዥ እፅ አዘዋዋሪዎች የሚከፍሏችሁ ጥቂት ገንዘብ እጅ ከፍንጅ ስትያዙ ከሚጠብቃችሁ ከባድ የህግ ቅጣት አያድናችሁም!» ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
📍 ምንጭ፦ የዩናይትድ ስቴትስ የጉምሩክ እና ድንበር ጥበቃ (CBP) / WJLA News
#Ethiopia #Khat #Dulles #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ለእያንዳንዱ ተሳፋሪ መንግሥት ድጎማ እያደረ መሆኑን ገለጸ
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ለእያንዳንዱ ተሳፋሪ በመንግሥት ድጎማ እንደሚደረግለት ተናግሯል። ይህን ድጎማ የከተማ አስተዳደሩ የሚሸፍነው ሲሆን፤ ለድጎማው በዓመት 500 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደሚደረግ አስታውቋል።
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርሃን አበባው (ዶ/ር) ለሪፖርተር እንደተናገሩት የባቡር ትራንስፖርት ዋጋ አነስተኛ የሆነው በድጎማው ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።
ከቃሊቲ ፒያሳ የባቡር ትራንስፖርት ዋጋ 20 ብር መሆኑን በምሳሌነት ያነሱት ሥራ አስፈፃሚው፣ በታክሲ ቢሆን ከ 80 እስከ 100 ብር ሊያስወጣ እንደሚችል አብራርተዋል።
በ 475 ሚሊዮን ዶላር ብድር የተገነባው የባቡር ፕሮጀክት በመጀመሪያዎቹ 10 ዓመታት ውስጥ ወጪውን ይሸፍናል ተብሎ ነበር። ይሁን እንጂ እስካሁን ድረስ ክፍያውን ማጠናቀቅ አልቻለም።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ብርሃን አበባው (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ አሁን ላይ በሚከፈለው አነስተኛ የባቡር የትራንስፖርት ዋጋ የፕሮጀክቱን ወጪ መሸፈን አይቻልም ብለዋል።
#Ethiopia #AddisAbaba #Train #Transportation #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ የ 5000 ብር ቅጣት ሊጥል ነው
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ በከተማዋ እየተስተዋለ ያለውን ያልተገባ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪና የመስመር ማሳጠር ችግሮችን ለመቅረፍ የ 5000 ብር ቅጣት ሊጥል መሆኑን አስታውቋል።
የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ለኢትዮኤፍም እንደገለጹት በከተማዋ ከሚንቀሳቀሱ ከ15 ሺህ በላይ የህዝብ ትራንስፖርት ሰጪዎች መካከል አብዛኞቹ በሕጋዊ መንገድ አገልግሎት እየሰጡ ቢሆንም፣ አንዳንድ አሽከርካሪዎች ግን ህዝቡን እያማረሩ ነው ብለዋል።
ባለፈው ዓመት ብቻ ከ120 ሺህ በላይ በሚሆኑ አሽከርካሪዎች ላይ የተለያየ ደረጃ ያለው አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።
ከእነዚህ አሽከርካሪዎች መካከል 25 በመቶ ያህሉ ከታሪፍ በላይ ሲያስከፍሉ የተገኙ መሆናቸውንና ቀሪዎቹ ደግሞ መስመር በማሳጠርና መሰል ጥፋቶች የተመዘገቡባቸው ናቸው ብለዋል።
እርምጃው በገንዘብ ቅጣት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን፣ ጥፋቱ ተደጋጋሚ ሆኖ ሲገኝ እስከ ሥራ ማገድ የሚደርስ ጥብቅ ውሳኔዎች እየተወሰዱ መሆኑም ተገልጿል።
#Ethiopia #AddisAbaba #Transportation #Taxi #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
በዘንድሮ የ 12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና 565 ትምህርት ቤቶች ምንም ዓይነት ተማሪ ማሳለፍ አለመቻላቸው ተገለጸ
ትምሕርት ሚኒስቴር የዘንድሮውን የ 12 ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ በሀገር አቀፍ ደረጃ 565 ትምህርት ቤቶች ምንም ዓይነት ተማሪ ማሳለፍ አለመቻላቸውን አስታውቋል።
እነዚህ ትምሕርት ቤቶች በክልል እና በከተማ መስተዳድሮች ደረጃ ሲገለጹ በኦሮሚያ ክልል 156፣ በአማራ 98፣ ደቡብ ኢትዮጵያ 86 ፣ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 69 ትምሕርት ቤቶች ምንም ዓይነት የ12 ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪ አላሳለፉም።
በተመሳሳይ ሁኔታ ትግራይ ክልል 48 ትምሕርት ቤቶች ቤኒሻንጉልጉሙዝ 29፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 22፣ አፋር 21 ሲዳማ ፣ ሶማሌ 9፣ ድሬዳዋ 5 ፣ ሀረሪ 3 ፣ ጋምቤላ 2 እና አዲስ አበባ 1 ትምሕርት ቤት ተፈታኝ ተማሪ ማሳለፍ ያልቻሉ ናቸው ተብሏል።
#Ethiopia #BerhanuNega #MinistryOfEducationEthiopia #HighSchoolEthiopia #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
ክብረ ወሰኑ በዮሚፍ በኩል ወደ ኢትዮጽያ ተመልሷል! 💚💛❤️
የቀድሞው የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቦነስ አይረስ 56:51 በመግባት የግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን ከጃኮብ ኪፕሊሞ መልሶ ተቆጣጥሯል 💪
ይህም ከቀደመው ክብረ ወሰን በ29 ሰከንድ የፈጠነ ነው 💥
#Ethiopia #Athletics #HalfMarathon #YomifKejelcha #Sports #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
የማይክል ካሪክ ማንችስተር ዩናይትድ አዲሱን የውድድር ዘመን በቅሌት ጀምሮታል!
ሀል ሲቲ 2-0 ማንችስተር ዩናይትድ
#PremierLeague #EPL #ManUtd #ManchesterUnited #Football
8 085
አዲሱ የውድድር ዘመን በሻምፒዮኖቹ ድል ተጀመረ!
አርሰናል 3-0 ኮቨንተሪ
#PremierLeague #EPL #Arsenal #Coventry #Football
8 085
በአሜሪካ ሜሪላንድ አውሮፕላን ማረፊያ 847 ፓውንድ (384 ኪ.ግ) ጫት በቁጥጥር ስር ዋለ
በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት በሚገኘው የባልቲሞር/ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ (BWI)፣ ከለንደን በመጡ ሁለት አሜሪካውያን መንገደኞች ሻንጣ ውስጥ በድምሩ 847 ፓውንድ (ወደ 384 ኪሎ ግራም) የሚመዝን ሕገ-ወጥ ጫት ተይዟል።
ዋና ዋና ነጥቦች፦
ክስተቱ፦ ተጠርጣሪዎቹ ጫቱን በ12 ሻንጣዎች ውስጥ የሻይ ቅጠል አስመስለው ይዘው ሲጓዙ በጉምሩክና ድንበር ጥበቃ (CBP) ባለስልጣናት ፍተሻ ወቅት ተይዟል። የተያዘው ጫት የገበያ ዋጋ ወደ 100,000 ዶላር እንደሚገመት ተገልጿል።
ጫት በአሜሪካ ሕግ፦ ጫት በምስራቅ አፍሪካ እና በአረብ ባሕረ-ሰላጤ ባህላዊ ልማድ ቢሆንም፣ በአሜሪካ የፌዴራል ሕግ መሠረት ሕገ-ወጥ ዕፅ (Schedule I / IV Controlled Substance) ተብሎ የተፈረጀ ነው።
የጤና ተፅዕኖ፦ ጫት ውስጥ የሚገኙት ካቲኖን (Cathinone) እና ካቲን (Cathine) የተባሉ አነቃቂ ኬሚካሎች የልብ ምትንና የደም ግፊትን እንደሚጨምሩ፣ ለእንቅልፍ ማጣት፣ ለጭንቀትና ለከፋ የጤና ችግር ሊዳርጉ እንደሚችሉ የጤና ባለሙያዎች ያስረዳሉ።
#ዜና #ጫት #አሜሪካ #CBP #BWI #Maryland #News #Khat
8 085
ትናንት ረፋድ ላይ በመቀለ ከተማ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 13 ሰዎች ቆሰሉ
ትናንት ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም. በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀለ የተለያዩ ቦታዎች ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 13 ሰዎች ከባድ እና ቀላል የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው የክልሉ ኮምንኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።
የድሮን ጥቃቱ “የመኖሪያ አካባቢን ዒላማ ያደረ” መሆኑን የክልሉ እና የህወሓት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አማኑኤል አሰፋ ተናግረዋል። በትናንቱ ጥቃት የቆሰሉ ዜጎች አይደር ሆስፒታል መግባታቸውም ተሰምቷል።
የክልሉ ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በትናንቱ መግለጫ የድሮን ጥቃቱ በሐውልቲ ክፍለከተማ፣ ሞሞና ጣቢያ፣ ቀጠና 27፣ እዳማርያም እና ኩሓ በተሰኙ አካባቢዎች በሚገኙ መኖሪያ ቤቶች ላይ ያረፈ መሆኑን አሳውቋል። ተጨማሪ ጥቃቶች ከፌደራል መንግሥቱ ሊሰነዘር ስለሚችል የክልሉ ነዋሪ ጥንቃቄ እንዲያደርግም በመግለጫው አሳስቧል።
#Ethiopia #Tigray #Mekelle #DroneStrike #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 085
+1
አንድ ሴት ታዳጊን በጋራ ሆነው ሲደበድቡ የነበሩ ተማሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ
ከሰሞኑ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር የነበረ አንዲት ታዳጊ ስትደበደብ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። በርካታ ሰዎች ቪዲዮን እየተቀባበሉ ደብዳቢዎቹ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንዲውሉ በማሳሰብ ቁጣቸውን ሲገልጹ ተስተውሏል።
ይህን ተከትሎ ነሐሴ 11/ 2018 የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ባወጣው መግለጫ ድርጊቱ የተፈጸመው በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ዓለም ባንክ አካባቢ በጥቅምት ወር መሆኑን ገልጿል።
ታዳጊዋን የደበደቡት ተማሪዎች ኤደን ዳዊት እና ሃኒ ሁሴን እንደሚባሉም አስታውቋል።ይህ ቪዲዮው በማኀበራዊ ሚዲያ ከመሰራጨቱ ከወራት በፊት ወንጀሉን የፈፀሙትን ሦስት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ ማጣራቱን ፖሊስ ገልጿል፡፡
በወንጀሉ የተጠረጠሩት ሦስት ተማሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበው በጊዜ ቀጠሮ ታስረው ፖሊስ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የፍትሕ አካል መላኩን አመልክቷል።
ልጅቷ ስትደበደብ የሚያሳየው ቪዲዩ መለቀቁ በልጅቷም ሆነ በቤተሰቧ ላይ አሉታዊ ጫና የሚያሳድር በመሆኑ ቪዲዮውን የለቀቀውን አካል ለማረጋገጥ ፖሊስ ሦስቱን ተጠርጣሪዎች በድጋሚ በቁጥጥር ስር አውሎ ተጨማሪ ምርመራ እያጣራ መሆኑንም ገልጿል፡፡
#Ethiopia #AddisAbaba #AddisAbabaPolice #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
