es
Feedback
EthioTube

EthioTube

Ir al canal en Telegram

ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ። Follow us on other our social media networks: Facebook.com/EthioTube Twitter.com/EthioTube Youtube.com/EthioTube Instagram.com/EthioTube

Mostrar más
8 353
Suscriptores
Sin datos24 horas
-177 días
-12130 días
Archivo de publicaciones
አርጀንቲናን 2ለ0 ስትመራ የቆየችው ግብጽ ተሰናበተች ሜሲ ዳግም ዋንጫ ያነሳ ይሆን? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #Egypt #Argentina #Football #Mess
አርጀንቲናን 2ለ0 ስትመራ የቆየችው ግብጽ ተሰናበተች ሜሲ ዳግም ዋንጫ ያነሳ ይሆን? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #Egypt #Argentina #Football #Messi

ብልጽግና ፓርቲ በሥልጣን ላይ ያለ መንግሥት ለሁለት የሥልጣን ዘመን ብቻ እንዲገደብ የሚያስችል አጀንዳ ለምክክር ኮሚሽን አስገብቷል ተባለ በዘንድሮ ምርጫ በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ ሥልጣን የያዘው የብል
ብልጽግና ፓርቲ በሥልጣን ላይ ያለ መንግሥት ለሁለት የሥልጣን ዘመን ብቻ እንዲገደብ የሚያስችል አጀንዳ ለምክክር ኮሚሽን አስገብቷል ተባለ በዘንድሮ ምርጫ በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ ሥልጣን የያዘው የብልጽግና ፓርቲ፤ ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ካስገባቸው አጀንዳዎች ውስጥ በሥልጣን ላይ ያለ መንግሥት ለሁለት የሥልጣን ዘመን ብቻ እንዲቆይ የሚል እንደሚገኝበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናግረዋል። ዐቢይ ይህን የተናገሩት ዛሬ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም. በፓርላማ ተገኝተው ከምክር ቤት አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ ነው። ከአንድ ሳምንት በኋላ በሚጀመረው አገር አቀፍ የምክክር ጉባዔ ላይ ምክክር ከሚደረግባቸው ጉዳዮች ውስጥ የሥልጣን ዘመን መገደብ መሆኑን አንስተዋል። ዐቢይ የሚመሩት የብልጽግና ፓርቲ “በሥልጣን ላይ ያለ መንግሥት ቢበዛ ለሁለት የሥልጣን ዘመን ብቻ መቆየት አለበት” የሚል አጀንዳ ለኮሚሽኑ ማቅረቡን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በአጀንዳነት የቀረበው ሃሳብ በአፍሪካ ደረጃ ያልተለመደ ነው ሲሉ አወድሰውታል። እንደሳቸው ማብራሪያ በአፍሪካ የተለመደው ሕገ መንግሥት በማሻሻል የሥልጣን ዘመንን ማራዘም መሆኑን አብራርተዋል። #Ethiopia #EthiopianPolitics #ProsperityParty #AbiyAhmed #PMAbiy #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa

ሮናልዶ እና ፖርቱጋል ተሰበቱ ስፔን ዋንጫ ያነሳ ይሆን? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #Spain #Portugal #Football #Ronaldo
ሮናልዶ እና ፖርቱጋል ተሰበቱ ስፔን ዋንጫ ያነሳ ይሆን? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #Spain #Portugal #Football #Ronaldo

ሀላንድ ብራዚልን አሰናበተ ዋንጫው የማን ነው ዘንድሮ? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #Football #Brazil #Norway
ሀላንድ ብራዚልን አሰናበተ ዋንጫው የማን ነው ዘንድሮ? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #Football #Brazil #Norway

ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ በሕክምና ስትረዳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየችከዚህ ዓለም በሞት ተለየች ራሔል፤ “አራዳ”፣ “ትዝታ”፣ “ምኒልክ” እና “ሀገሬ
ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ በሕክምና ስትረዳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየችከዚህ ዓለም በሞት ተለየች ራሔል፤ “አራዳ”፣ “ትዝታ”፣ “ምኒልክ” እና “ሀገሬ ኢትዮጵያ” እና ሌሎች በርካታ ድንቅ ሙዚቃዎችን ያበረከተች አንጋፋ አርቲስት ነበረች። 13 አልበሞችን ያሳተመችው ራሔል የሙዚቃ ጉዞዋን በ1973 ዓ.ም “አንቺ ባለድሪ” በተሰኘ አልበሟ እንደጀመረች ተነግሯል። ከኪነ-ጥበብ ስራዎቿ ባሻገር፣ ራሔል በሆቴልና መስተንግዶ ዘርፍም የረጅም ጊዜ ልምድ ነበራት። በጊዮን ሆቴል በዲፕሎማ የተመረቀችው አርቲስቷ፣ በተለያዩ የሀገር ውስጥ ሆቴሎች በጀነራል ማናጀርነት ጭምር አገልግላለች። ራሔል የሁለት ወንድና የአራት ሴት ልጆች እናት እንዲሁም የልጅ ልጆችንም አይታለች። ኢትዮ ቲዩብ ለድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ቤተሰቦች፣ አድናቂዎች መጽናናትን ይመኛል። #Ethiopia #RahelYohannis #EthiopianMusic #AmharicMusic #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa

ለአለም ዋንጫ ቀጣይ ጥሎ ማለፍ ዙር ያለፉ ምርጥ 16 ቡድኖች እነዚህ ናቸው። 2ቱ አፍሪካዊ ቡድኖች ናቸው። አፍሪካውያኑ የት ይደርሱ ይሆን? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup202
ለአለም ዋንጫ ቀጣይ ጥሎ ማለፍ ዙር ያለፉ ምርጥ 16 ቡድኖች እነዚህ ናቸው። 2ቱ አፍሪካዊ ቡድኖች ናቸው። አፍሪካውያኑ የት ይደርሱ ይሆን? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #AfricansAtWorldCup #Football

አፍሪካን ያኮሩት ኬብ ቨርዲዋች - ቢሸነፋም የብዙዎችን ልብ አሸንፈዋል! #Messi #Argentina #CapeVerde #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026
አፍሪካን ያኮሩት ኬብ ቨርዲዋች - ቢሸነፋም የብዙዎችን ልብ አሸንፈዋል! #Messi #Argentina #CapeVerde #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026

ማን ወደ ሀገሩ ይገባ ይሆን ዛሬ? #Ronaldo #Modric #Portugal #Croatia #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #TheLastDance
ማን ወደ ሀገሩ ይገባ ይሆን ዛሬ? #Ronaldo #Modric #Portugal #Croatia #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #TheLastDance

በሀብሩ ወረዳ ሕፃናት በእሳት ሲጫወቱ በተቀሰቀሰ አደጋ ከ 53 በላይ መኖሪያ ቤቶች እና 1 መስጅድ ወደመ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ አስተዳደር 023 ቀጅማ ቀበሌ ቀሰማ ተብላ በምትጠ
+2
በሀብሩ ወረዳ ሕፃናት በእሳት ሲጫወቱ በተቀሰቀሰ አደጋ ከ 53 በላይ መኖሪያ ቤቶች እና 1 መስጅድ ወደመ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ አስተዳደር 023 ቀጅማ ቀበሌ ቀሰማ ተብላ በምትጠራ ጎጥ ሁለትህፃናት ከአገዳ ክምር አጠገብ እሳት በማያያዝ ሲጫወቱ በተፈጠረ አደጋ ከ53 በላይ መኖሪያ ቤት እና በ1 መስጅድ የቃጠሎ አደጋ ደርሶባቸዋል። በዚህ አደጋ ከ 163 በላይ ሰዎች ድጋፍ የሚሹ መሆናቸው ተሰምቷል። የወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የእሳት አደጋ ከቦታው ድረስ በመሄድ ተመልክቷል። ተጎጂዎችን ከዕለት ድጋፍ ጀምሮ በዘላቂነት ለማቋቋም እንዲቻል የጉዳቱን መጠን በትክክል ሊያጠና የሚችል የቴክኒክ ቡድን በማዋቀር በዛሬው ዕለት አደጋ ወደ ደረሰበት ስፍራ እንዲሄዱ ተደርጓል። በዜጎች ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመታደግ በመንግስት በኩል ስራዎች እየተሰሩ ነው ተብሏል። #Ethiopia #EthiopianNews #AmharicNews #Amhara #Mesjid #EthioTube #Africa

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ "እኔ በዲሞክራሲ የምታማ ሰው አይደለሁም ብለውኝ ነበር" ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ 👉"ኦሄዴዶች በዚህ ደረጃ ይወርዳሉ፤ከመውረድም እንዲህ ያንሳሉ ብዬ አስቤ አላውቅም"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ "እኔ በዲሞክራሲ የምታማ ሰው አይደለሁም ብለውኝ ነበር" ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ 👉"ኦሄዴዶች በዚህ ደረጃ ይወርዳሉ፤ከመውረድም እንዲህ ያንሳሉ ብዬ አስቤ አላውቅም" ዕውቁ ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ ተበድለናል፣ ተጨቁነናል፣ ይሉ የነበሩ ኦሄዴዶች በዚህ ደረጃ ይወርዳሉ ብዬ አስቤ አላውቅም ብለዋል። ፓለቲከኛው ረጅም ጊዜ ከሚዲያ እና የፓለቲካ ተሳትፎ ርቀው የቆዩ ሲሆን በዚህ ሳምንት በተላለፈውና ሪፖርተር ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቃለመጠይቅ ወቅታዊ ጉዳዮችን የተመለከተ አስተያታቸውን አጋርተዋል። በኢዜማ ፓርቲ ውስጥ አመራር የነበሩት አቶ አንዷለም ፓርቲያቸውን ለቅቀው የወጡት ኢዜማ "ከብልፅግና ጋር ያለው መስመር ፈፅሞ እስኪጠፋ ድረስ" መቀጠሉን በመቃወም መሆኑን ተናግረዋል። ፓለቲከኛ አንዷለም በነበራቸው ቆይታ ያነሷቸው ሀሳቦች:- ⭕️ለውጡ የመጣ ሰሞን "ብዙዎቻችን የነጋ መስሎን ነበር፤ የፓለቲካ ትግል ውስጥ ምን አደርጋለሁ ብዬ አስቤ ነበር" ብለዋል። ከለውጡ "አንድ፣ሁለት ወር በኋላ ግን ነገሮች ከሐዲድ እየወጡ እንደሆነ ገባኝ" ሲሉ ተናግረዋል። ⭕️አንዷለም ኦሆዴዶች/ኦፒዲኦ "በዚህ ደረጃ ይወርዳሉ ብዬ አስቤ አላውቅም" በማለት ተናግረዋል። "ተበድለናል፣ተጨቁነናል" ሲሉ የነበሩት ኦሕዴዶች፤ ኢህአዴግ ውስጥ እንደበታች ይታዩ እንደነበር በመጥቀስ በነሱ ላይ የደረሰውን በደል ሥልጣን ከያዙ በኋላ በሌላ ላይ ለመጫን መሞከራቸውን ተችተዋል። ⭕️ "በዚህ ደረጃ ይወርዳሉ ከመውረድም በጣም ያንሳሉ ብዬ አስቤ አላውቅም። ከሰብአዊነት ጎዳና ወጥተው እንደዚህ ትከሻችን ላይ ቆመው እስክስታ ይወርዳሉ ብዬ አስቤ አላውቅም" ሲሉ በሥልጣን ላይ ያሉትን የቀድሞ የኦሕዴድ አባላትን በጠንካራ ቃላት ተችተዋል። #Ethiopia

የሴት አልባሳትን በመጠቀም ሲያጭበረብር የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ ከማኀበረሰቡ እሴትና ባሕል ባፈነገጠ መልኩ የሴት ሂውማን ሄር፣ የጆሮ ጌጣ ጌጥ እና የመሳሰሉትን አለባበሶች በመጠቀም ሲንቀ
+2
የሴት አልባሳትን በመጠቀም ሲያጭበረብር የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ ከማኀበረሰቡ እሴትና ባሕል ባፈነገጠ መልኩ የሴት ሂውማን ሄር፣ የጆሮ ጌጣ ጌጥ እና የመሳሰሉትን አለባበሶች በመጠቀም ሲንቀሳቀስ የነበረው ተጠርጣሪ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋለ። ጀማል አነስ የተባለው ተጠርጣሪ በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው አስኮ መናህሪያ አካባቢ ሊያዝ ችሏል። ሴት መስሎ ከግለሰቦች ጋር ንግግር በሚያደርግበት ወቅት በመጠራጠር ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውልም ችሏል፡፡ በግለሰቡ ላይ በተደረገበት አካላዊ ፍተሻም ሴት ሳይሆን ወንድ ሆኖ መገኘቱን ከጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ተጠርጣሪ ጀማል አነስ ከዚህ ቀደምም ሴት መስሎ ሲያጭበረብር እንደነበር ከምስክሮች ቃል መረዳት የተቻለ ሲሆን ከተንቀሳቃሽ ስልኩ ላይም በተለያየ ጊዜ የተለያዩ የሴት አልባሳትንና ጌጣጌጦችን ለብሶ የተነሳቸው ፎቶ ግራፎች መገኘታቸውን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል፡፡ ከህብረተሰቡ እሴትና ባህል ባፈነገጠ መልኩ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች አንድም ለወንጀል ተግባር የሚደረጉ የማታለያ መንገዶች መሆናቸውን የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ኀብረተሰቡ መሰል እንቅስቃሴዎችን ሲመለከት ለፖሊስ መረጃ መስጠት እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡ #Ethiopia #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa

ሞሮኮ በሆላንድ ላይ የበላይ በመሆን ወደ ምርጥ 16 #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #AfricansAtWorldCup #Football #Morocco #Netherlands
ሞሮኮ በሆላንድ ላይ የበላይ በመሆን ወደ ምርጥ 16 #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #AfricansAtWorldCup #Football #Morocco #Netherlands

ለአለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ያለፉት ምርጥ 32 ቡድኖች እነዚህ ናቸው። 9ኙ አፍሪካዊ ቡድኖች ናቸው። አፍሪካውያኑ የት ይደርሱ ይሆን? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #Afr
ለአለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ያለፉት ምርጥ 32 ቡድኖች እነዚህ ናቸው። 9ኙ አፍሪካዊ ቡድኖች ናቸው። አፍሪካውያኑ የት ይደርሱ ይሆን? #WorldCup #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #AfricansAtWorldCup #Football

"በጠቅላይ ሚኒስት ዐቢይ ካቢኔ ውስጥ ሁለት ሚኒስትሮች ሃይማኖት የላቸውም" ዮናስ ዘውዴ (ዶ/ር) የቀድሞ የብልፅግና ፓርቲ ሹም የነበሩት ዮናስ ዘውዴ (ዶ/ር) ከሰመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅ የተለያዩ
"በጠቅላይ ሚኒስት ዐቢይ ካቢኔ ውስጥ ሁለት ሚኒስትሮች ሃይማኖት የላቸውም" ዮናስ ዘውዴ (ዶ/ር) የቀድሞ የብልፅግና ፓርቲ ሹም የነበሩት ዮናስ ዘውዴ (ዶ/ር) ከሰመኑ በሰጡት ቃለ መጠይቅ የተለያዩ ጉዳዮችን አንስተዋል። የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ በመሆን ያገለገሉት ዮናስ ዘውዴ (ዶ/ር) ከኃላፊነት በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን ከገለፁ በኋላ ረዘም ላለ ጊዜ ከዕይታ ጠፍተው ነበር። ይሁን እንጂ በፌስ ቡክ ገፃቸው መንግሥትን ጠንከር ባሉ ቃላት በመተቸት እና በመውቀስ ሃሳቦቻቸውን ማጋራታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋ ሆድ እና ጀርባ እንደሆኑ ማሳያ ተደርጎ ሲነገር መቆየቱ ይታወሳል። ዮናስ ዘውዴ(ዶ/ር) በአሁን ወቅት ከኢትዮጵያ መውጣታቸውን አስታውቀዋል። በአሜሪካ አትላንታ "ስመጥር በሆነ ዩኒቨርስቲ ውስጥ" ትምሕርታቸውን እየተከታተሉ መሆኑንም ተናግረዋል። ዮናስ በሰጡት ቃለመጠይቅ ምን ተናገሩ? 👉 የብልፅግና ፓርቲን ስያሜ ያወጡት የቀድሞ ም/ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ብናልፍ አንዷለም መሆናቸውን ገልፀዋል። ለፓርቲው ስም ለማውጣት በአዳማ በተካሔደ ውይይት ለፓርቲው "ጤፍእና ቡና"የተሰኘ አማራጭ ስያሜ ቀርቦ እንደነበርም አስታውሰዋል። 👉በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ካቢኔ ውስጥ ሁለት ሚኒስትሮች ሃይማኖት የላቸውም ብለዋል። በስም ያልጠቀሷቸው እነዚህ ሁለት ሚኒስትሮች ሚኒስትር ከመሆናቸው በፊት እንደሚያውቋቸው ገልፀው፤ "ራሳቸውን ከኦርቶዶክስ ጋ ሊያመሳስሉ ይችላሉ [እንጂ] ጴንጤ ወይ ሙስሊም እንዳልሆኑ አውቃለሁ" ብለዋል። 👉በካቢኔው ውስጥ "የኦርቶዶክስ ቁጥር በጣም አናሳ መሆኑን አውቃለሁ" ብለዋል። አክለውም "ለምን እንደዚህ እንዲደረግ ተፈለገ?" የሚለውን ግን እንደማያውቁ ነው ያስረዱት። #Ethiopia

ኢዜማ በትግራይ ክልል ምርጫ አለመካሄዱን “የውጭ ሚዲያዎች አጋንነው አቅረበውታል” አለ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) መሪ አቶ እዮብ መሳፍንት፤ የትግራይ ክልል በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ
ኢዜማ በትግራይ ክልል ምርጫ አለመካሄዱን “የውጭ ሚዲያዎች አጋንነው አቅረበውታል” አለ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) መሪ አቶ እዮብ መሳፍንት፤ የትግራይ ክልል በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ አለመሳተፏ በውጭ ሚዲያዎች በተጋነነ መንገድ መቅረቡን ተችተዋል። የፓርቲው መሪ ይህንን የተናገሩት “ቻናል አፍሪካ” (Channel Africa) ከተሰኘው የሬዲዮ ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ነው። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ከ አምስት ዓመታት በፊት ከተደረገው ምርጫ የተሻለ ሆኖ መካሔዱን አቶ እዮብ ጠቁመዋል። የኢዜማው መሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአጠቃላይ 547 መቀመጫዎች እንዳሉት አስታውሰው፣ ከእነዚህ ውስጥ በትግራይ ክልል የሚገኙት 38 ወንበሮች ብቻ መሆናቸውን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በትግራይ ክልል ምርጫ አለመካሄዱ፣ ቃለ መጠይቁን በሰጡበት “ቻናል አፍሪካ” ጨምሮ በሌሎች የውጭ መገናኛ ብዙኃን ከመጠን በላይ ተጋኖ መዘገቡን ተችተዋል። አቶ እዮብ ሲያስረዱም “ከ 547 መቀመጫዎች መካከል [ትግራይ ክልል] ያላት 38 መቀመጫዎችን ብቻ ነው። ነገር ግን የእነዚህ ወንበሮች አስፈላጊነት [አለመምረጣቸው]፣ የእናንተን ሚዲያ ጨምሮ በውጭ መገናኛ ብዙኃን በጣም በተጋነነ መንገድ ነው የቀረበው” ሲሉ ተደምጠዋል። #Ethiopia #Tigray #Ezema #EyobMesafint #EthiopianElection #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa

በተፈረደባቸው የሞት ፍርድ ሊገደሉ ከነበሩ ኢትዮጵያውያን መካከል ከ300 በላይ የሚሆኑት ወደ ሀገር ቤት ተመለሱ በሳዑዲ ዐረቢያ የተፈረደባቸውን ሞት ፍርድ ሲጠባበቁ ከነበሩ እና የፍርድ ሂደታቸው ተቋ
+2
በተፈረደባቸው የሞት ፍርድ ሊገደሉ ከነበሩ ኢትዮጵያውያን መካከል ከ300 በላይ የሚሆኑት ወደ ሀገር ቤት ተመለሱ በሳዑዲ ዐረቢያ የተፈረደባቸውን ሞት ፍርድ ሲጠባበቁ ከነበሩ እና የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው ኢትዮጵያውያን መካከል 320 የሚሆኑት በዛሬው ዕለት ወደ ሀገር ገብተዋል። ተመላሾች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ አቀባበል አድርገውላቸዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሪያድ የሚገኘውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሚሲዮን እና ጂዳ የሚገኘውን ቆንስላ ጽሕፈት ቤት በማስተባበር ባደረገው የዲፕሎማሲ ጥረት የሞት ፍርዱ ሊቋረጥ ችሏል። በሳዑዲ አረቢያ ለእስር ተዳርገው የነበሩ 1655 ዜጎቻች ሲሆኑ ሁሉም የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምሕረት አዋጅ እንዲሰጣቸው ተደርጓል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሕብረተሰቡ ከሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች በማኅበራዊ ሚዲያ የታጀበ ሀሰተኛ ማታለያ ድርጊት የውጭ አገር ጉዞ ራሱን እንዲጠብቅ መንግሥት አሳስቧል። #Ethiopia #EthiopiansInSaudi #SaudiArabia #Migrants #Immigrants #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa #MiddleEast

"መርጌታ ነኝ እቁብ እንዲደርስህ አደርጋለሁ" በማለት 625 ሺህ ብር ያጭበረበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ 👉 ገንዘቡን የተጭበረበረው ግለሰብ በደረሰበት የሥነ ልቡና ቀውስ ፀበል ገብቶ ነበር። አ
+1
"መርጌታ ነኝ እቁብ እንዲደርስህ አደርጋለሁ" በማለት 625 ሺህ ብር ያጭበረበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ 👉 ገንዘቡን የተጭበረበረው ግለሰብ በደረሰበት የሥነ ልቡና ቀውስ ፀበል ገብቶ ነበር። አብርሀም ሰርኬ የሚባለው ግለሰብ በሐሰት መሪ ጌታ ነኝ በማለት አቶ ደነቀው ሙሉቀን ከተባለና በዳንሻ ከተማ በሆቴል ስራ ላይ ከተሰማራ ግለሰብ 625ሺህ ብር አታሎ መውሰዱን የሉማሜ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር በድሉ መልሰው ተናግረዋል። ወንጀሉን የፈፀመው ግለሰብ "እቁብ እንዲደርስህ አደርጋለው" በማለት ታህሳስ 2018ዓ.ም ብሩን አታሎ መስዷል። ይህን ብር ከወሰደ በኋላ በተጨማሪ ሦስት መቶ ሺህ ብር ካልጨመረክ "ቤተሰብህን በሙሉ በመተት አጠፋብሃለው" በማለት በተበዳይ ላይ አደገኛ የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም መቆየቱ ተመላክቷል። የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት የፍ/ቤት መያዥያ ትዕዛዝ በማውጣት ተጠርጣሪው በተገኘበት በቁጥጥር ስር እንዲውል በፃፈው የትብብር ደብዳቤ ከምስራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ የመረጃ ክትትል ቡድን ጋር በመተባበር ግለሰቡ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም በሉማሜ ከተማ አስተዳደር በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጎል። አቶ ደነቀው ሙሉቀን በደረሰበት የማታለል ወንጀል ምክንያት ለከፍተኛ ሥነልቦናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተጋልጦ በፀበል ቦታ እንደቆየ ተሰምቷል። #Ethiopia #Dansha #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa

ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ብልፅግና ፓርቲ ማሸነፉ ታወጀ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጨረሻ የውጤት አሳውቋል። ገዥው ብልፅግና ፓርቲ ለሚ
ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ብልፅግና ፓርቲ ማሸነፉ ታወጀ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጨረሻ የውጤት አሳውቋል። ገዥው ብልፅግና ፓርቲ ለሚቀጥሉት 5 ዓመታት ሀገሪቱን የሚመራበትን ድምፅ በማግኘት ማሸነፉ ተገልጿል። ብልፅግና ፓርቲ ምርጫ በተካሄደባቸው የሁሉም ክልል እና የፌዴራል ከተማ ምክር ቤቶች እንዲሁም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አብላጫ ወንበሮችን በማግኘት አጠቃላይ አሸናፊነቱን በይፋ አረጋግጧል። ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ምርጫ ከተካሄደባቸው 501 ወንበሮች መካከል ብልፅግና ፓርቲ 438 መቀመጫዎችን አሸንፏል። ተቃዋሚ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች 41 ወንበሮች ተከፋፍለዋል። በተወሰኑት ላይ የድጋሚ ማጣራት ወይም ድጋሚ ምርጫ ይካኼድባቸዋል ተብሏል። ቦርዱ ይፋ ባደረገው የክልል ምክር ቤቶች የመጨረሻ የውጤት መሠረት፣ ብልፅግና ፓርቲ በሁሉም አካባቢዎች በበላይነት ወንበር አግኝቷል። #Ethiopia #EthiopianElection #ProsperityParty #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa

ከኢትዮጵያ የተላከ ነው የተባለ ጫት በዋሽንግተን ደለስ ኤርፖርት ውስጥ ተያዘ በአሜሪካ ዋና ከተማ ዋሽንግተን በሚገኘው ደለስ ኤርፖርት፤ ከኢትዮጵያ የተላከ ነው የተባለ 139 ፖውንድ የሚመዝን ጫት እ
ከኢትዮጵያ የተላከ ነው የተባለ ጫት በዋሽንግተን ደለስ ኤርፖርት ውስጥ ተያዘ በአሜሪካ ዋና ከተማ ዋሽንግተን በሚገኘው ደለስ ኤርፖርት፤ ከኢትዮጵያ የተላከ ነው የተባለ 139 ፖውንድ የሚመዝን ጫት እንደተያዘ ተሰምቷል። የአሜሪካ የጉምሩክ እና ድንበር ጥበቃ ባለሥልጣናት እንደተናገሩት፤ ወደ ካሊፎርኒያ ሊተላለፍ ነበር የተባለው ጫት 17 ሺህ ዶላር ወይም ከ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያለው ነው ብለዋል። ጫቱ ሊገኝ የቻለው የለተያዩ ቅመማ ቅመሞች እንደያዘ ተደርጎ የተመዘገበን ጭነት በሚፈትሹበት ወቅት መሆኑን የጉምሩክ እና ድንበር ጥበቃ ባለሙያዎች ተናግረዋል። ጭነቱ በአጠቃላይ 102 ሳጥኖችን ይዟል። ከእነዚህም መካከል አስሩ ሳጥኖች ቅጠላቅጠል ያላቸው የእፅዋትን የያዙ ሲሆን ለአሜሪካ የግብርና መሥሪያ ቤት የዕፅዋት ተመራማሪዎች ተልከው በተደረገው ማጣራት የጫት ቅጠል መሆናቸው ተረጋግጧል። ጫት፤ የምግብ ፍላጎት ማጣትን፣ የመተንፈስ ችግርን፣ እንዲሁም የደም ግፊት እና የልብ ምት የሚጨምር በመሆኑ የዓለም ጤና ድርጅት በአውሮፓውያኑ የዘመን አቆጣጠር በ1980 ጫትን “አላግባብ ጥቅም ላይ የሚውል ለሱስ የሚደርግ ዕፅ” በሚል ፈርጆታል። የአሜሪካ የጉምሩክ እና ድንበር ጥበቃ በመካነድሩ ላይ ባወጣው መግለጫ፤ በኤርፖርት የተያዘውን ጫት በማስተላለፉ የተያዙ ሰዎች ስለመኖራቸው ያለው ነገር የለም። #Ethiopia #UnitedStates #Khat #Chat #USA #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa

🎟️ TICKETS ARE LIVE! 🎟️ Join us for the Birara Genet Charitable Organization Annual Fundraising Event! Your presence and su
+1
🎟️ TICKETS ARE LIVE! 🎟️ Join us for the Birara Genet Charitable Organization Annual Fundraising Event! Your presence and support help us continue our mission to Educate. Empower. Elevate. 🌟 🗓️ Date: Thursday, June 25, 2026 🕠 Time: 5:30 PM 📍 Location: Sheraton Hotel, Addis Ababa 💵 Ticket Price: 2,500 ETB How to Secure Your Seat: Transfer your ticket payment to the account name Birara Genet Charitable Organization via either of these bank options: • CBE Bank: 1000434925766 • Enat Bank: 1041137703037001 ✨ Reserve your seat today! For more information or to confirm your booking, send us a DM or call us directly at 📞 +251 97 571 4310. See you there! 🙌✨ #BiraraGenet #FundraisingEvent #AddisAbaba #CharityEvent #TicketsLive