Benishangul Gumuz Education Bureau
Відкрити в Telegram
ይህ ቻናል የቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን ከክልል እስከ ትምህርት ቤቶች ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡
Показати більше5 482
Підписники
+224 години
+137 днів
+4630 день
Архів дописів
በማኦ እና ኮሞ ልዩ ወረዳ በዌጼ ወዴሳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በማህበረሰብ ውይይት ፌስቲቫል ተካሄደ ።
------------=------------= -------------=------------
(ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ፤ ቶንጎ) የማኦ እና ኮሞ ልዩ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ከዩኒሴፍ -STEP ፕሮግራም ጋር በመተባበር በ4 ትምህርት ቤቶች የሴቶች የትምህርት ተሳትፎና ተጠቃማነት ማሻሻል ፣ የልዩ ፍላጎት ትምህርትና የህብረተሰብ ተሳትፎ ስራዎችን በማሳደግ የተማሪዎች ትምህርት ዉጤታማነትን ማሻሻል ላይ የማህበረሰብ ውይይት መድረኮችን በት/ቤቶች ደረጃ ስካሄድ መቆየቱና ተጨባጭ ለዉጦች መመዝገባቸዉ አቶ ዳዊት ሽፈራዉ የትምህርት ጽ/ቤት የስርዓተ ትምህርት ዝግጅት ቡድን መሪ ተናግሯል።
በዌጼ ወዴሳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በማህበረሰብ ዉይይት ህብረተሰቡ በት/ቤቱ ችግሮች ላይ በማወያየት የሴት ተማሪዎች፣ ልዩ ፍላጎት ተማሪዎች እና የህብረተሰብ ተሳትፎ ስራዎች ላይ ተጨባጭ ውጤቶች የተገኙ ሲሆን ፤ ህብረተሰቡ በውይይቱ የትምህርት ቤቱን ችግሮች ለመፍታት 50 የዶሮ እርባታ በት/ቤቱ ማስጀመር፣ የተማሪዎች ምገባ አጠናክሮ ማስቀጠል እና ዉስጥ ገቢዉ ለማሳደግ ዘርፍ ብዙ ተግባራት ተከናዉኗል።
ትምህርት ቤቱ ባካሄደው በማህበረሰብ ውይይት ፌስቲቫል ላይ ጉልህ ድርሻ ላደረጉ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ዕውቅናና ምስጋና ሰጥቷል በተጨማር ድጋፊ ለሚሹ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስና ንጽህና መጠቂያ ቁሳቁስ ድጋፊ ተደርጓል።
በማህበረሰብ ዉይይት ፌስቲቫል ላይ የማኦ እና ኮሞ ልዩ ወረዳ ሰላም ግንባታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀሽም አልማም፣የልዩ ወረደዉ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ረ/ኮማሽኔር አልኪድር አሻርፍ፣ የቀበሌዉ አመራሮች፣የተማሪ ወላጆች እና በለድርሻ አካላት ተገኝቷል።
ወጣት ተማሪዎች በአሉታዊ መንገድ ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ የሚመለከታቸው ሁሉ ከወዲሁ ጥብቅ ክትትል ሊያደርጉ ይገባል ተባለ
----------- ---------------- --------------- -----------
(ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ወጣት ተማሪዎች በአሉታዊ መንገድ ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ የሚመለከታቸው ሁሉ ከወዲሁ ጥብቅ ክትትል ሊያደርጉ ይገባል ሲል ገለጸ።
ቢሮው ከዩኒሴፍ - STEP ፕሮግራም ጋር በመተባበር የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የስነ- ምግባር መመሪያን ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ስልጠና ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በቢሮው የስርዓተ-ትምህርትና የትምህርት ተቋማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ ኡስማን ወጣት ተማሪዎች በአሉታዊ መንገድ ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ የሚመለከታቸው ሁሉ ከወዲሁ ጥብቅ ክትትል ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።
አቶ መሀመድ አክለውም ያላቻ ጋብቻ በትምህርት ቤቶች እየታየ ያለውን የሴት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ እንዲለዩ ምክንያት በመሆኑ የየትምህርት ቤት አመራሮች ይህን ጉዳይ ትኩረት ሰጥተው ሊከታተሉት ይገባል ብለው የሚቀርበውን መመሪያ በሚገባ ተከታትለው እና በትምህርት ቤቶች ተግባራዊ በማድረግ ትውልድን በስነ ምግባር በማነፅ ለውጤት ማብቃት ከሁሉም መምህራን ይጠበቃል ብለዋል።
በቢሮው የስርዓተ ፆታና ፀረ ኤች አይ ሺ ኤድስ ዩኒት አስተባባሪ ወ/ሮ ከሪማ ሳሌህ በበኩላቸው በትምህርት ቤቶች በጀንደር ክበብ አማካኝነት ለተማሪዎች የህይወት ክህሎትና የስነ ምግባር መመሪያን በትምህርት ቤት ደረጃ በመተግበር በተማሪዎች ላይ የባህሪ ለውጥ እንዲታይ መስራት ይገባል ብለዋል።
ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚሠጠውን ይህንን ስልጠና በቢሮው መምህራን ልማት ባለሙያ አቶ ካሳሁን በላይነው የተማሪዎችን ስነ ምግባር መመሪያን ጥልቅ ግንዛቤ እየሠጡ ይገኛል። ዘገባው የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
Follow this link to join my WhatsApp community: https://chat.whatsapp.com/IrRJLbE25t3Bggb3cYaVXd
124 ሚሊዮን ብር ገዳም ህብረተሰቡ ለትምህርት ዘርፍ ስራ አስተዋጽኦ አድርጓል
------- ------------ ------------ --------------- ----
(ሰኔ 28/2018 ዓ.ም-አሶሳ)የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ላለፉት አስራ ሁለት ወራት ያከናወናቸውን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ለቢሮው ሰራተኞች በቀረበበት መድረክ ላይ በቢሮው የዕቅድና ትምህርት ፕሮግራሞች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ በሺር አብዱረሂም 124 ሚሊዮን ብር ገዳም ህብረተሰቡ ለትምህርት ዘርፍ ስራ አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የዕቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ አበራ ሲሆኑ የተከናወኑ ዓበይት ስራዎች ፣ የተገኙ ውጤቶች ፣ ያጋጠሙ ችግሮች ፣ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎችን በዝርዝር አቅርበዋል። በተመሳሳይ የክረምት የበጎ አድራጎት ስራዎች ዕቅድ በቢሮው ዕቅድ ባለሙያ በአቶ መንግሥቱ ማሩ ቀርቧል።
በትምህርት ዘርፍ ከተሰማሩ አምስት አዳዲስ የትምህርት አጋር ፕሮጀክቶች በተያዘው ዓመት በርካታ ስራዎችን ማከናወናቸው በቀረበው ሪፓርት ተጠቁሟል፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰሩ ከነበሩ ስራዎች መካከል ሁሉም የትምህርት ባለሙያዎችና የትምህርት ቢሮ ሰራተኞች ዲጂታል የፋይዳ መታወቂያ መያዝና አምስት ሚሊዮን ኮደርስ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን አቶ ቴዎድሮስ በሪፖርታቸው አመላክተዋል፡፡
የትምህርት ስራ አመራር (EMIS) ሙሉ በሙሉ ከወረቀት ነፃ ለማድረግና የፈተና ስርዓትን ለማዘመን ቢሮው ያከናወናቸው ተግባራት በስኬት ይወሰዳሉ ሲሉ አቶ በሺር አንስተዋል።
ህብረተሰብ ተኮር የተማሪዎች የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም መደረጉ ፤ የትምህርት አጋር ድርጅቶች ለትምህርት ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መሰጠት እንዲሁም በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ከ13 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሴት ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት መሰጠቱ ከቀረበው ሪፖርት በዋናነት ተገልፀዋል፡፡
ሰራተኞችም ገንቢ አስተያየቶችንና በቀጣይ ቢሰራባቸው ያሏቸውን ጉዳዮች በሰፊው አንስተዋል።
የዕቅድና ትምህርት ፕሮግራሞች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ በሽር አብዱረሂም በማጠቃለያው እንዳሉት ቢሮው በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ያከናወናቸውን አበረታች ስራዎችን ማስቀጠል በክፍተትነት የተነሱትን ደግሞ የማረም ስራዎች ተሰርተው ቀጣዩን የዝግጅት ምዕራፍ በተጠናከረ መልኩ መስራት እንደሚገባ አሳስው፤ በተለይ በዚህ የክረምት ወራት የበጎ አገልግሎት ዕቅዱን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ሁሉም ሰራተኞች ሀላፊነት እንዳለባቸው አፅንዖት ሰጥተዋል፡፡
ዘገባው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
የትምህርት ጥራትና ብቃትን በማስጠበቅ የግል ትምህርት ተቋማት ተወዳዳሪነታቸው ማሳደግ ይኖርባቸዋል ተባለ
-------------- ----------------- --------------- -------
(ሰኔ 28/ 2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) በቤኒሻንጉል -ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የስርዓተ-ትምህርትና የትምህርት ተቋማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ ኡስማን የሮሜድ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ባዘጋጀው የተማሪ ወላጆች ፕሮግራም ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት የትምህርት ጥራትና ብቃትን በማስጠበቅ የግል ትምህርት ተቋማት ተወዳዳሪነታቸው ማሳደግ ይኖርባቸዋል ብለዋል።
ሮሜድ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአሶሳ ከተማ ሻል ካሉ ትምህርት ቤቶች ጋር ተወደዳዳሪ ለመሆነ የሚያደረገውን ጥረት እናደንቃለን ፤ እንደቢሮ ማድረግ የሚገባንን ድጋፍ እናደርጋለን ያሉት አቶ መሀመድ ትምህርት ቤቱ በክላስተር ስር ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች ያስተላለፉቸውን መልካም አሰራሮች በቀጣይም ተጠናክረው መቀጠልና በመዲናዋ ተወዳዳሪ ትምህርት ቤት መሆን አለበት ብለዋል፡፡
ከትምህርት ቤቱ ስኬት ጀርባ ያሉትን የትምህርት ቤቱ ርዕሳነ መምህራን ፣ መምህራንና ትምህርት ቤቱ እንደሌሎቸ ትምህርት ቤቶች ተወዳዳሪ እንዲሆን ጥረት ለሚያደርጉ የት/ቤቱ ባለቤቶቸ ምስጋና ያቀረቡት አቶ መሀመድ ፤ ተሸላሚ ተማሪዎችና ወላጆችንም እንኳን ደስ ያላቸሁ ብለዋል፡፡
ትምህርት ቤቱ ትውልድ የመቅረጽ ሃላፊነቱን ይበልጥ እንዲወጣ ያሳሰቡት የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ጎጃም አያና ናቸው።
የትምህርት ቤቱ ባለቤት አቶ ምትኩ በበኩላቸው ለወላጆች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
የትምህርት ቤቱ ዋና ርዕሰ መምህር አቶ አዲሱ ትምህርት ቤቱ በመማር ማስተማር በዓመቱ ያከናወናቸው ስራዎች በሪፖርት ለወላጆች አቅርበዋል ፤ ለመጡ እንግዶችም ምስጋና አቅርበዋል።
ተማሪችም አስተማሪ መልዕክቶቾን በመዝሙር አስተላልፈዋል ፤ በውጤታቸው በደረጃ ለወጡ ተማሪዎችም የማበረታቻ ሽልማት በክብር እንግዶች ተበርክቶቸዋል። ዘገባው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው።
Education Transformation Operation fo rLearning-ETOL አፈጻምን በተመለከተ የግንዛቤ ምክክር እየተደረገ ይገኛል
---------- --------------- -------------- ----------- ---
በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የ” Education Transformation Operation for Learning-ETOL“ አፈጻጸምን በተመለከተ፤ ከአሶሳ ዞን ወረዳዎች፣ከማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳና ከአሶሳ ከተማ የትምህርት መምሪያ ለተወጣጡ የትምህርት ጽኅፈት ቤት ኃላፊዎች፣የሥርዓተ ትምህርት ቡድን መሪዎች፣የአካባቢ ጥበቃ ባለሞያዎችና የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ባለሞያዎች ግንዛቤ የሚያሰፋ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡
ከፍ ሲል የተጠቀሰውን ጉዳይ በተመለከተ የምክክሩን ዋና ዓላማ ተመርኩዘው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በትምህርት ቢሮ ትምህርት እቅድና የትምህርት ፕሮግራሞች ዘርፍ ምክትል ኃላፊው አቶ በሺር አብደልራሒም ናቸው፡፡
አቶ በሺር እንደተናገሩት፤ ቀደም ሲል በጥቅል ለትምህርት ቤቶች ድጋፍ ያደርግ የነበረው የአጠቃላይ የትምህርት ጥራት መሻሻል መርኃ-ግብር-ለፍትሐዊነት ፕሮግራም ፤ባዲስ መልክ በ “ETOL” ተተክቶ እየተፈጸመ ስለሚገኝ፤ ትምህርት ቤቶችና ወረዳዎች ምን ምን ተግባራትን እንዴት እንደሚፈጽሙና፤ በሀገር-ዓቀፍ ደረጃ ከሚናወነው የአጠቃላይ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም አፈጻጸም ጋር በሰናሰለ መንገድ የሚያከናውኗቸውን ተግባራት ለማሳለጥ፤ይኽ የግንዛቤ ምክክር ትልቅ አስተዋጽዖ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
አያይዘውም፤ከቅድመ መደበኛ ትምህርት ጀምሮ እስከ ስድስተኛ ክፍል ድረስ አጠቃላይ ድጋፍ በማድረግ የሚፈጸመው የ“ETOL” አካሄድ፤ ሀገራችን ካስቀመጠችውና ወደፊት ለመፈጸም እቅድና ዝግጅት እያደረገችባቸው ከሚገኙት ዘርፈ ብዙ ተግባራት አንጻር፤ ራስን መቻልመና ከማናቸውም ረጅ ድርጅቶች ነጻ ኾኖ፤ ተግባራትንና ፍላጎቶችን ለሟሟላት በራስ የመፈጸም አቅም የማጎልበት ኣካሄድን ያማከለ ሊኆን ይገባል ብለዋል፡፡
በመቀጠልም፤በትምህርት ዘርፉ የሚታዩብንን ክፍተቶች ደረጃ በደረጃ ለመድፈን የምናደርጋቸውን ጥረቶችን በበለጠ መጠን አውቆ ፤ለወደፊቱ ትምህርት ቤቶች ከየአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር በመተባባር በራሳቸው አቅም የሚያናከናውኗቸውን ተግባራት የማስፋት ኃለፊነትንም ያጠቃለለ ምክክር ሊያደርጉ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
በማከልም፤በትምህርት ቤቶች የተማሪዎች የምገባ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ትምህርት ቤቶችን በመጠገን በአዲስ የመገንባትና ቁሳቁሳቸውን የማሟላት ሂደትና ሊኖራቸው ስለሚገባው የውስጥ ገቢን የሚያሰፉ የተለያዩ የእንስሳት ርባታና የርሻ ተግባራት መፈጸሚያ ሥፍራዎችን ስለማስፋፋት ወዘተ. በዚኽ ስብሰባ የተገኛችሁ ባለሞያዎች በሚገባ መመካከር ይገባችኋል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም በትምህርት ቤት ጊቢዎችንና አካባቢዎችን አረንጓዴ ማልበስና ለመማር ማስተማር የተመቹና የሚመረጡ በማድረግ ማኅበረሰቡን ያሳተፈ ልማት ማከናወንን፤ በትምህርት ቤቶች በሚከናወኑ አጠቃላይ የልማት ሥራዎች ገንዘብ ወጪ ኾኖላቸው ሲከናወኑ አስፈላጊውን ደንብ ባልጣሰ መልኩ ሊፈጸሙ እንደሚገባ በማሳሰብ፤ ይኸንን ደንብ በጣሰ መልኩ የሚፈጸሙ አሠራሮችን ለመታገልና ለማስወገድ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ተጠሪዎች ስለሚያከናውኗቸው ተግባራት የሚያስረዱ አንኳር ነጥቦች በባለሙያዎች የሚቀርቡ በመኾናቸው ተሰብሳቢዎች በትኩረት እንዲሳተፉ አደራ ብለዋል፡፡
ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚቀጥለው በዚኽ ምክክር፤ በ “ETOL” ጥቅል አፈጻጸምና የትኩረት ነጥቦች የዘርፉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ተጠሪ አቶ ንጉሤ ዲቢሳ፤እንዲኹም በአካባቢና ማኅበራዊ ጥበቃ ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራትን አስመልክቶ ባለሞያው አቶ ታምሩ ማሞ፤ እንዲኹም በትምህርት ቢሮ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ባለሞያው አቶ ሲራጅ ኢብራሒም ለምክክሩ ተሳታፊዎች ያዘጋጇቸውን ሃሳቦች የሚያቀርቡ ሲኾን፤ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መመሪያን ጨምሮ በየወረዳዎቹ በየዘርፉ የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ሪፖርቶችን ተሳታፊዎቹ የሚያቀርቡ ይኾናል፡፡
ዘገባው ትምህርት ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
+7
በማህበረሰብ ውይይት ተጨባጭ ውጤቶችን አግኝተናል ፤ በቢልዲጊሉ ወረዳ የዙምባ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
------------ ------------ ------------- -------------
(ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ከዩኒሴፍ -STEP ፕሮግራም ጋር በመተባበር በሰባት ወረዳዎች ፤ በ25 ትምህርት ቤቶች በሴቶች የትምህርት ተሳትፎ ፣ በልዩ ፍላጎት ትምህርትና በህብረተሰብ ተሳትፎ በሚሉ አጀንዳዎች የማህበረሰብ ውይይቶች ሲያደረግ ቆይቷል።
በማህበረሰብ ውይይት ውጤቶችን አግኝተናል የሚለን በቢልዲጊሉ ወረዳ የዙምባ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከላይ በተጠቀሱ አጀንዳዎች መሻሻሎችና ተጨባጭ ውጤቶች የተገኙ ሲሆን ፤ ህብረተሰቡ በውይይቱ የትምህርት ቤቱን ችግሮች ለመፍታት ሰባት የእርባታ ፍየሎች ፤በበቆሎ ሰብል የተሸፈነ የእርሻ ቦታ ድጋፍ አድርጓል።
ትምህርት ቤቱ ባካሄደው በማህበረሰብ ውይይት ፌስቲቫል ላይ ጉልህ ድርሻ ላደረጉ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ዕውቅናና ምስጋና ሰጥቷል። የክልሉ ትምህርት ቢሮንና ዩኒሴፍ -STEP ፕሮግራም አመስግኗል። በሌሎችም ትምህርት ቤቶች ተመሳሳይ ውጤቶች ተገኝተዋል። የዘገባው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ የዘርፉን ሪፎርም ስራ መነሻ በማድረግ ቢሮውን ለተገልጋዮችና ለሰራተኞች ምቹ የስራ አካባቢ ለማድረግ እየሰራ ነው። ጥቂቶቹን በምስል. . . .
+9
ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ቀን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በኦን ላይን እየተሰጠ ነው
------ ---------- -----
(ሰኔ 25/2018 ፤ አሶሳ) ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ቀን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በኦን ላይን እየተሰጠ ነው።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ፤ የቢሮው ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ ኡስማን ፣ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ጎጃም አያናና የቢሮ ዳሬክተሮች በገመ ሃሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማዕከል በኦን-ላይን እየተሰጠ ያለውን ፈተና ተመልክተዋል።
ፈተናው ደህንነቱን በጠበቀና ሰላማዊ ሆኖ እየተሰጠ መሆኑንም የስራ ሃላፊዎች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በክልል በ16 የመፈተኛ ጣቢያዎቾ ፈተናውን በበይነ-መረብ ይሰጣል እየተሰጠ ይገኛል። 5,017 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በበይን መረብ ፈተናውን ይወስዳል ፤ በጥቅሉ 7,705 ተማሪዎች ፈተናውን የሚወስዱ ሲሆን 4,336 የተፈጥሮ ሳይንስ 3369 የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ መሆናቸው ታውቋል። የዘገባው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው።
