Benishangul Gumuz Education Bureau
رفتن به کانال در Telegram
ይህ ቻናል የቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን ከክልል እስከ ትምህርት ቤቶች ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡
نمایش بیشتر5 451
مشترکین
-224 ساعت
+177 روز
-5830 روز
آرشیو پست ها
Dear Mitiku, these are model exams for grades 6 & 8. Please share for all woredas.
Geneva Global ከግልገል በለስ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ እና ከአሶሳ ዩኒቨርስቲ ጋር በጋራ በሚተገበሩ ፕሮግራሞች ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረም::
Geneva Global በኢትዮጵያ የመምህራን ትምህርት ሥርዓትን ማጠናከር እና የማስተማርና መማር ሂደቱን ጥራት የሚያሻሽሉ ዘላቂ ተሃድሶዎችን ተቋማዊ ማድረግ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ የሚገኝ ጠቋም ሲሆን የ«ኢትዮጵያ የማስተማር መሪዎች» (Leaders in Teaching Ethiopia) ፕሮግራም የአስፈጻሚ ስትራቴጂው አካል በመሆን፣ 15 ዩኒቨርሲቲዎችን እና 14 የመምህራን ትምህርት ኮሌጆችን ያካተተ ሰፊ የመምህራን ትምህርት ተቋማት መረብ ጋር አጋርነት መስርቷል። በቀጣይ አምስት አመታት በግልገል በለስ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ እና አሶሳ ዩኒቨርስቲ በጋራ ከሚሰሩ ስራዎች ውስጥ :-
* አዲስ የCTE አሰልጣኞችን ማዘጋጀት (Preparing new CTE instructors)
*በስራ ላይ ያሉ የኮሌጅ :የ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ መምህራንን ክህሎት ማሳደግ (Enhancing skills of current teachers)
*የትምህርት አመራርነትን ማጠናከር (Strengthening instructional leadership)
*የተማሪዎችን የሽግግር ሂደት መደገፍ (Supporting students transition)
* ሁሉን አቀፍነትን እና የሥርዓተ-ጾታ እኩልነትን ማሻሻል (Advancing inclusion and gender equity)
*አስተማሪዎችን ማበረታታት/ማነቃቃት (Motivating educators)
ቀጣይነት ያለው የትምህርት ሥርዓት መገንባት (Building a sustainable educational system) ወዘተ ይገኙበታል::
አሶሳ ዩኒቨርስቲን እና ኮሌጁን በመወከል የአሶሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ያሬድ ሙሉ የመግባቢያ ስምምነቱን የተፈራረሙ ሲሆን የኮሌጁ ዲን አቶ ብዙአየሁ ሳንቢት የፊርማ ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል:: ፕሮግራሙ በተለያዩ ክልሎች እንደሚተገበር ተገልፅዋል::
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ለትምህርት ለወጥ ትግበራ የሚውል የኢቶል (ETOL) ፕሮግራም አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ።
(አሶሳ ሰኔ 5/2018 ዓ.ም) የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ለትምህርት ለውጥ ትግበራ የተማሪዎች ውጤት ማሻሻል የሚውል የኢቶል(Ethiopa Education Tiransformation Opration For Learning ) ፕሮግራም አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር ገምግሟል ።
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ የኢቶል ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ኩመራ አየለ እንደገለጹት በ2018 በጀት ዓመት ለትምህርት ለውጥ ትግበራ የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻልና ከፍ ለማድረግ ያታለመ ፕሮጀክት መሆኑን አስረድተዋል ።
በተለይም ለችግር የተጋለጡ ተማሪዎችን የትምህርት ተደራሽነትንና ተከታታይነት ከማረጋገጥ ባሻገር የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዝ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።
የድጎማ በጀቱ የፋይናንሻል የሥራ አፈጻጸም ወጤታማ ቢሆንም የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ተገቢውን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ገንዘቡ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጥብቅ ጥብቅ የሙስና መከላከል እና የኦዲት ቁጥጥር ሥርዓቶች ተዘርግቷል ብለዋል።
የትምህርት ቢሮ የኢቶል ፕሮግራም ክትትልና ግምገማ ባለሙያ አቶ ጠብቆው ወርቁ በበኩላቸው ኢቶል ፕሮግራም የመማር ማስተማር ሂደቱን በትምህርት ቤቶች ላይ በተጠናክረ መልኩ ለማስቀጠል የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል ።
ፕሮግራሙ በክልል ደረጃ የትምህርት ዘርፉን ለመደገፍ ትልቁ እና ወሳኝ አካል ሲሆን በትምህርት ቤቶች ደረጃ ትልቅ ለውጥን ለማምጣት ያለመ ፕሮግራም መሆኑን ባቀረቡት ጹሑፍ አመላክቷል ።
በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የኢቶል ፕሮግራም በክልል ደረጃ የትምህርት ጥራት ለማሻሻል የሚያግዝ በመሆኑ ፕሮግራሙ በበለጠ ውጤታማ እንዲሆን ተገቢውን ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ብሏል።
የኢቶል ፕሮግራም በበለጠ ውጤታማ እንዲሆን በዘርፉ ላይ የተሰማሩት አካላት የተጠናከረ ክትትልና ግምገማ ልደረግ ይገባል ብሏል።
በውይይት መድረኩ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ እና ትምህርት ቢሮ ፣የአሶሳ ከተማ አስተዳደርና ማኦኮሞ ልዩ ወሰዳዎች እና በአሶሳ እና ከማሺ ዞን ስር የሚገኙ ፕሮግራሙ የሚተገበርባቸው ወረዳዎች ተገኝተዋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2018 ዓ.ም ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለክልላዊ እና ብሔራዊ ፈተና ይቀመጣሉ
*
(አሶሳ፤ ሰኔ 5/2018 ዓ/ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን 53 ሺህ 462 ተማሪዎች ለክልላዊ እና ብሔራዊ ፈተና እንደሚቀመጡ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ።
የክልሉ የፈተና ኮማንድ ፖስት በ2018 ዓ.ም የሚሰጡ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ እና የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ውጤታማ ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ የዝግጅት ሥራዎች ዙሪያ ውይይት አካሂዷል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር)፣ ክልላዊ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል እንዲሁም እና የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤታማ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኙ ባለድረሻ የተቀናጀ ሥራ ይጠበቃል ብለዋል።
በ2018 የትምህርት ዘመን 7 ሺህ 679 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና፣ 21 ሺህ 541 ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል እንዲሁም 24 ሺህ 242 ተማሪዎች ደግሞ 6ኛ ክልላዊ ፈተናን እንደሚወስዱ ተናግረዋል።
በክልሉ ብሔራዊ ፈተናን የሚወስዱ ተማሪዎች ቀደም ሲል በአሶሳ እና እንጂባራ ዩኒቨርሲቲዎች ሲወስዱ እንደነበር ጠቁመው፣ በተያዘው በጀት ዓመት የፈተና መስጫ ማዕከላት ከ2 ወደ 18 ማዕከል ከፍ ማለቱን ተናግረዋል።
ከሰኔ 24/2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን ብሔራዊ ፈተና ከሚወስዱ 7 ሺህ 679 ተማሪዎች ውስጥ 4 ሺህ 999 ወይም 65 በመቶ የሚሆኑት በኦንላይን እንደሚፈተኑ አስረድተዋል፡፡
ፈተናውን በኦንላይን ለሚውስዱ ተማሪዎች የሚውሉ 245 ታብሌቶች ተገዝተው ለፈተና ማዕከላት መሠራጨታቸውንም ገልጸዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር፣ ክልላዊ እና ብሔራዊ ፈተናዎችን በሠላምና በውጤታማነት ለማጠናቀቅ የሚመለከታቸው ተቋማትና የጸጥታ አካላት ቅንጅታቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል፡፡
ተማሪዎች የፈተና ህግጋትን በማክበር በተረጋጋ፣ በሰላማዊና በራስ መተማመን ፈተናቸውን እንደወስዱ ማድረግ የሁሉም ድርሻ ሊሆን እንደሚገባም ጠቅሰዋል፡፡
ሲል የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን በዘገባው አመላክቷል
ስርዓተ-ጾታ አካቶ የማስተማር ስነ-ዘዴን በተሻለ ደረጃ ተግባራዊ እንዲደረግ ለትምህርት ቤት አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው
---------------- ------------ ------------- --------------- ----------------
(ሰኔ 3/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) የቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ከዩኒሴፍ ኢትዮጲያ ጋር በመተባበር - በSTEP ፕሮግራም ስርዓተ-ጾታ አካቶ የማስተማር ስነ-ዘዴን በተሻለ ደረጃ ተግባራዊ እንዲደረግ ለትምህርት ቤት አመራሮችና ለወረዳ የሴቶች ጉዳይ ተጠሪዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
ከስርዓተ-ጾታ ጋር በተያያዘ ቢሮው ቀላል የማይባሉ ስልጠናዎችንና ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ያወሱትና ስልጠናውን በይፋ ይስጀመሩት በክልሉ ትምህርት ቢሮ የትምህርት ፕሮግራሞች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ በሺር አብዱረሂም የዚህን ስልጠና አተገባበሩን በልዩ ሁኔታ ክትትል እንደሚደረግና ርዕሳነ-መምህራን ለዚሁ እንዲዘጋጁ አሳስበዋል፡፡
የሴት ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎና ውጤታማነት ለማሻሻል በእያንዳንዱ የክፍል ውስጥ የማስተማር ስነ-ዘዴ መምህራን ተግራዊ እንዲያደርጉ የትምህርት ቤት አመራሮች ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንዲያደርጉ የሚያስችል ስልጠና ነው ያሉት በቢሮው የመምህራንና የት/ቤት አመራሮች ልማት ዳሬክተሩ አቶ ናሽናል ድሪርሳ ለስልጠናው ትኩረት እንዲሰጡ አሳስበዋል፡፡
ስልጠናው በስርዓተ-ጾታ ምንነት ፣ አስፈላጊነት ፣ የህግ-አግባብና በትምህርት ቤት በተለይም በክፍል ውስጥ በመማር ማስተማር መካተት በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ሰልጠናው በመተከል ዞን በተመሳሳይ እየተሰጠ ይገኛል ተብሏል፡፡ የሳይንስና የሒሳብ መምህራንም በሳይንስ ኪት ምንነት አስፈላጊነትና በተግባር የታገዘ ስልጠናም እየተሰጠ መሆኑን ለማዎቅ ተችሏል፡፡ ዘገባው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡
የትምህርት ቤቶችን የመረጃ ስርዓት በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማዘመን ጊዜ የምንስጠው ጉዳይ አይደለም ፤ አቶ በሽር አብዱረሂም
----------- ------------- -------------- ----------------
(ሰኔ 1/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) የትምህርት ቤቶችን መረጃ ስርዓት በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማዘመን ጊዜ የሚስጠው ጉዳይ አለመሆኑን በክልሉ ትምህርት ቢሮ የትምህርት ፕሮግራሞች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ በሽር አብዱረሂም ገልጸዋል።
ትምህርት ቤቶችን በግብዓት ለማሟላትና ተገቢውን ድጋፍ ለማድረግ የትምህርት መረጃን ተደራሽነትና ማዘመን አስፈላጊ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ከጊዜው ጋር መራመድም እንድትምህርት ተቋም አስገዳጅ ይሆናል ሲሉ አቶ በሺር አክለዋል፡፡
የክልሉ ትምህርት ቢሮ አብዛኞቹን ትምህርት ቤቶች የትምህርት መረጃ ስርዓታቸውን ወደ ዲጂታል ስርዓት እያስገባ መሆኑን የጠቀሱት አቶ በሺር በጄኔቫ ግሎባል ፕሮጄክት የሚታገዙ 21 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እያንዳንዱን የትምህርት መረጀ በትክክለኛው መሙላት ለቀጣይ ለሚደረገው ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማ የተማሪዎችን የማሳለፍ ምጣኔን ከፍ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑና ሰልጣኝ የአይሲቲ መምህራንም ይህን ሃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
በድርጅቱ የታቀፉ ትምህርት ቤቶች ከሶስት ዓመታት በፊት ምንም ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያላሳለፉና ከዚህ በኃላ ተገቢውን ትምህርት ለተማሪዎች በመስጠትና ተማሪዎችን በማገዝ ማሳለፍ አስጋዳጅ መሆኑን በስልጠና ማስጀመሪያ የተመላከተ ሲሆን ፤ በዚሁ ልክ ትምህርት ቤቶች መስራት አለባቸው ተብሏል፡፡
በክልሉ የድርጅቱ አስተባባሪ አቶ ሸምሰዲን መሀመድ በበኩላቸው እንደገለጹት በቀጣይ ድጋፍ በሚደረግላቸው 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በቀጥታ ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ድርሻ ያላቸው ተግባራት ለመደገፍና ለመከታተል የሚመሉት መረጃዎች በጥንቃቄና በትኩረት እንዲሆን አሳስበዋል፡፡
በትምህርት መረጃ የሚሰጠው ስልጠና ለሁለት ቀናት ቆይታ ያለው ሲሆን ሰልጠናውን በቢሮው የዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳሬክተሩ አቶ ቴዎድሮስ አበራ በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ በመተከልና በካማሺ ዞን ተመሳሳይ ስልጠናዎችን በድርጅቱ ለታቀፉ ትምህርት ቤቶች ይሰጣል ተብሏል፡፡ ዘገባው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡
የ6ኛና የ8ኛ ክፍል ፈተና እርማት የሚያገለግለው ሶፍት ዌር በተመለከተ ለርዕሳነ መምህራንና ለስርዓተ-ትምህርት ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው
--------- ----------- ------------- ---------------
(ግንቦት 28/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) የቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ከፕላን ኢንተርናሽናል ድርጅት ጋር በመተባበር የ6ኛና የ8ኛ ክፍል ፈተና እርማት የሚያገለግለው ሶፍት ዌር በተመለከተ ለርዕሳነ መምህራንና ለወረዳ ስርዓተ-ትምህርት ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በቢሮው የስርዓተ-ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ዳሬክተር አቶ አህመድ ኡስማን እንደገለጹት ስልጠናው ያስፈለገበት ዋነኛ ዓላማ የ2018 ዓ.ም የ6ኛና የ8ኛ ክፍል ፈተናን በማሽን ከመታረሙ ጋር በተያያዘ ከትምህርት ቤት የሚመጡ የተማሪዎች መረጃ በጥንቃቄ በሶፍትዌሩ ላይ ባለው መጠይቅ ተሞልቶ በመላክ የፈተና አስተዳደር ስርዓቱን ማስጠበቅ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
አቶ አህመድ አክለው እንደገለፁት የሶፍትዌር ስልጠናው
ከዚህ በፊት የ6ኛና የ8ኛ ክፍል ፈተና እርማት ሲወድስ የነበረው ጊዜ በእጅጉ በማሳጠር ፣ የሰው ሃይል ፣ የፈተና ድንነት ፣ የፈተና ስርቆትና ኩረጃ ብሎም በእርማት ጊዜ የሚገጥሙትን ችግሮች መፍታት ያስችላል ብለዋል፡፡
ስልጠናውን ከቀለም ሜዳ ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኪሩቤል እየተሰጠ ሲሆን ተፈታኝ ተማሪዎችን ከመመዝገብ እስከ መፈተን ድረስ ያለው አሰራርና አካሄዶችን ለፈተና እርማት ተብሎ በተዘጋጀው ሶፍትዌር ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል ብለውናል፡፡
ሙሉ የተማሪው መረጃ በጥንቃቄ መሙላት ከፈተና በኃላ በእርማት ጊዜ የሚፈጠረው ችግር በእጅጉ እንደሚቀንስ በስልጠናው ላይ የተመላከተ ሲሆን የተማሪዎች የፈተና መመዝገቢያ ቁጥር ፣ ተማሪዎች ሲፈተኑ ሕጻናት እንደመሆናቸው መጠን የመልስ መስጫ ወርቀታቸው በጥንቃቄ እንዲይዙ ፣ መሞላት የሚገባቸው መረጃዎች በጥንቃቄ እንዱመሉ ወረዳዎች ትልቅ ሃላፊነት አለባቸው ተብሏል፡፡ ዘገባው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ልጆቻችሁን ይመለከታል
ልጆች ከስልክ፣ ከታብሌት ወይም ከኮምፒውተር ስክሪን ፊት ረጅም ጊዜ ማሳለፋቸው (Screen Time) በአጠቃላይ እድገታቸው ላይ የሚፈጥረው ተፅዕኖ በአሁኑ ጊዜ የብዙ ወላጆች አሳሳቢ ጉዳይ ሆኗል። ይህ ልምድ በጤናቸው፣ በአዕምሯቸው እና በስነ-ልቦናቸው ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖን ይፈጥራል፡፡
#በጤና ላይ የሚያደርሰው ተጽዕኖ፡- ከስክሪን የሚወጣው ሰማያዊ ብርሃን (Blue Light) ሰውነት እንቅልፍ የሚያመጣውን Melatonin የተባለ ሆርሞን እንዳያመርት ያግዳል፦ ይህም ልጆች እንቅልፍ እንዲያጡ ወይም ጥልቅ እንቅልፍ እንዳይተኙ ያደርጋል።
ልጆች በአንድ ቦታ ተቀምጠው ረጅም ሰዓት ሲያሳልፉ መንቀሳቀስ፣ መሮጥና መጫወት ያቆማሉ። ይህ ደግሞ ለአላስፈላጊ የሰውነት ውፍረት እና ለጡንቻዎች አለመንቀሳቀስ ይዳርጋል። አካላዊ እድገት እና ጥንክሪያቸውንም ያላላል፡፡
የአይን እይታ መዳከም፦ ለረጅም ሰዓት በቅርብ ርቀት ስክሪን ማየት የአይን መድረቅ፣ እይታ ብዥ ማለት እና የአይን ጡንቻዎች መድከም (Digital Eye Strain) ያስከትላል።
#የትኩረት ማጣት (Attention Span)፦ በስልኮች ላይ የሚለቀቁ ቪዲዮዎች እና ጌሞች በጣም ፈጣን በመሆናቸው፣ የልጆችን አዕምሮ በአንድ ነገር ላይ ረጅም ጊዜ የማተኮር ብቃት ያሳጡታል። ይህ በትምህርታቸው ላይ ትኩረት እንዳያደርጉ እና ስልቹ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡
የቋንቋ እና የንግግር እድገት መዘግየት፦ በተለይ ከ3 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ቋንቋ የሚማሩት ከሰዎች ጋር በሚያደርጉት ቀጥተኛ ግንኙነት (interaction) ነው። ስክሪን ላይ ብቻ የሚያሳልፉ ህፃናት የመናገር እና ሃሳብን የመግለጽ ብቃታቸው ሊዘገይ ይችላል።
#የፈጠራ ችሎታ መከተፍ፦ ዝግጁ የሆኑ ምስሎችን እና ጌሞችን ብቻ ማየት የልጆችን የራሳቸውን ጨዋታ የመፍጠር እና የማሰብ (Creative thinking) ችሎታ ያጠፋባቸዋል።
የስነልቦና ተጽዕኖ
የባህሪ መለወጥና ብስጭት፦ ስልክ ሲከለከሉ ከልክ በላይ መቆጣት፣ መጮህ ወይም ግትር መሆን (Temper tantrums)። በስልኩ ሱስ የመያዝ ምልክቶች ሊታዩባቸው ይችላል።
#የማህበራዊ ክህሎት ማጣት፦ ልጆች ከሰዎች ጋር እንዴት እንደሚግባቡ፣ ስሜታቸውን እንዴት እንደሚቆጣጠሩ እና ከሌሎች ጋር እንዴት እንደሚጋሩ የሚማሩት በአካል ሲገናኙ ነው። ስልክ ላይ የሚያሳልፉ ልጆች ግን ብቸኝነትን ሊመርጡና ከሰዎች ጋር መግባባት ሊከብዳቸው ይችላል።
ጭንቀትና ድብርት፦ በተለይ ትልልቅ ልጆች (አራሶች/ቲንኤጀርስ) በማህበራዊ ሚዲያ በሚያዩዋቸው ነገሮች ምክንያት ራሳቸውን ከሌሎች ጋር በማወዳደር ለጭንቀት እና ለደህንነት ማጣት ስሜት ሊጋለጡ ይችላሉ።
#ምን መደረግ አለበት?
የእድሜ ገደብ መጠቀም፦ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እንደሚመክረው ከ2 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ጨርሶ ስክሪን ባያዩ ይመረጣል። ከ2-5 ዓመት ላሉ ደግሞ በቀን ከአንድ ሰዓት ማነስ አለበት።
አርአያ መሆን፦ ልጆች ከእኛ ስለሚማሩ፣ ወላጆች ራሳቸው በልጆቻቸው ፊት ስልክ የሚጠቀሙበትን ሰዓት መቀነስ አለባቸው።
አማራጭ ጨዋታዎች፦ መጽሃፍትን ማንበብ፣ በአካል የሚጫወቱትን ጨዋታዎች ማቅረብ እና ከቤት ውጪ እንዲንቀሳቀሱ ማበረታታት
በመጪው የትምህርት ዘመን 1452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ሥራ ለማስጀመር የግንባታ ማስጀመር ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው።
(ግንቦት 28/2018 ዓ.ም )በትምህርት ሚኒስቴር እና በክልል ትምህርት ቢሮዎች ትብብር እየተገነቡ የሚገኙ 1,452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እስከ መጪው ነሐሴ መጨረሻ ድረስ በማጠናቀቅ በአዲሱ የትምህርት ዘመን ለአገልግሎት ለማብቃት የግንባታ ማስጀመር ሥራዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውን የትምህርት ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ከተማ መስቀላ ገልጸዋል።
ዶ/ር ከተማ እንዳስታወቁት፣ ከአጠቃላይ 1,452 ትምህርት ቤቶች መካከል 726 በትምህርት ሚኒስቴር እና 726 በክልል ትምህርት ቢሮዎች አማካኝነት ይገነባሉ ብለዋል።
የግንባታ ሂደቱንም ለማፋጠን እስካሁን በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነቡ 341 ትምህርት ቤቶች እና በክልሎች የሚገነቡ 64 ትምህርት ቤቶች የኮንትራት ስምምነት ከተቋራጮች ጋር ተፈርሞ ወደ ሥራ የተገባ ሲሆን፣ 25 ትምህርት ቤቶች ደግሞ የግንባታ ሥራቸውን በይፋ መጀመራቸውን አብራርተዋል።
እነዚህ ትምህርት ቤቶች በመጪው የትምህርት ዘመን ለአገልግሎት ሲበቁ ከ87,000 በላይ ሕፃናትን ተቀብለው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽነትን በ15 በመቶ እንደሚያሳድጉ ተገልጿል።
ሥራ አስኪያጁ አክለውም በተለያዩ ምክንያቶች የግንባታ ሂደታቸው የዘገየባቸው ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ቀሪውን ጊዜ በተጠናከረ ቁርጠኝነት በመጠቀም ትምህርት ቤቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ አስፈላጊውን ትኩረትና ክትትል እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
