uk
Feedback
ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

Відкрити в Telegram

በብ/ዓ/ቅ/ጴጥሮስ ወጳውሎስ እና ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ የፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ገጽ ነው

Показати більше
3 151
Підписники
+124 години
+127 днів
+7230 день
Архів дописів
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን  
ለሰንበት /ት/ቤታችን አባላት በሙሉ
  የሰንበት /ት/ቤቱ ንብረት የሆኑ መገልገያ ዕቃዎች በተለያየ ምክንያት በእጃችሁ ላይ የሚገኙ የሰ/ት/ቤታችን አባላቶች ከዛሬ ከሰኔ 30 ቀን እስከ ሐምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሰንበት /ት/ቤቱ ሒሳብና ንብረት ክፍል እንድታስረክቡ እየጠየቅን ይህ ሳይሆን ቢቀር ግን ሰንበት ት/ቤቱ ባስቀመጠው መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 15 ንዑስ አንቀጽ 15.2 መሠረት የሰ/ት/ቤቱን ንብረት ለግል ጥቅም ማዋል የሚያስከትለው ቅጣት እንደሚከተል በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ ንብረቶች የት እና ማን ጋር እንደሚገኙ ሙሉ መረጃዎች ስላሉን ስማችሁን ከፎቶ ጋር ማስታወቂያ ቦርድ ላይ ከመለጠፉ በፊት እና ከላይ በተገለጸው አንቀጽ መሠረት እርምጃ ሳይወሰድ በፊት በእጃችሁ ያለውን ንብረት እንድትመልሱ እናሳስባለን።
የሰንበት /ት/ቤቱ ጽ/ቤት

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ለሰንበት /ት/ቤታችን አባላት በሙሉ / በድጋሚ ለማስታወስ   እንኳን ለቅዱሳን ሐዋርያቱ ዓመታዊ በዓል በሠላም አደረሳችሁ
ከሰጠኸኝም ሁሉ ለአንተ ከዐሥር እጅ አንዱን እሰጥሃለሁ ዘፍ 28:22
  💰 ወርሃዊ መዋጮ መክፈል መንፈሳዊ ኃላፊነትዎ እንዲሁም የአባልነት ግዴታዎስ መሆኑን ያውቃሉ? 💰 በእርስዎ የወርኃዊ መዋጮ አስተዋጽኦ የሰንበት ት/ቤታችን ... 🔹 የወንጌል አገልግሎት ይፋጠናል 🔸 ለአገልግሎት የሚሆኑ ንዋያት እና ንብረቶች ይገዙበታል። 🔹 ጥገናና እድሳት የሚያስፈልጋቸው ንብረቶች ይጠገኑበታል። 🔸 እንዲሁም ለእርስዎ የወንጌልን ቃል በመተግበር ሰማያዊ ዋጋን ያገኙበታል  በመሆኑም ውድ አባላቶቻችን መንፈሳዊ ኃፊነትዎንና ግዴታዎን እንዲወጡ በቅዱሳን ሐዋርያቱ ስም እናሳስባለን፡፡   ክፍያዎን በንግድ ባንክ የሒሳብ ቁጥር 1000633843768 ዮርዳኖስ ወይም/እና ሙሉቀን እንዲሁም  በአሐዱ ባንክ የሒሳብ ቁጥር 0017568711701 ብርሃናተ ዓለም …  በተጨማሪም በሰንበት /ት/ቤቱ የልማት ተቋም ሱቅ በአካል በመሄድ መክፈል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ለበለጠ መረጃ:ስልክ ፡ 0920 47 60 05 0932 18 56 63   እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይባርክ ሒሳብና ንብረት ክፍል

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን የሰ/ት/ቤታችን ልማት ተቋም ለቅዱሳኑ ሐዋርያት በዓልና እንዲሁም ወዳጅ ዘመድ ለምታስመርቁ ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ከልዩ መስተንግዶና የእንኳን አደረ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
የሰ/ት/ቤታችን ልማት ተቋም ለቅዱሳኑ ሐዋርያት በዓልና እንዲሁም ወዳጅ ዘመድ ለምታስመርቁ ልዩ ልዩ ስጦታዎችን ከልዩ መስተንግዶና የእንኳን አደረሳችሁ ስጦታ ጋር አዘጋጅቶ ይጠብቅዎታል።
የፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ልማት ተቋም

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው ፥ በመቅደሱ ለማገልገል ከሰማያዊ ከሐምራዊም ከቀይ ግምጃም በብልኀት የተሠራ ልብስ ለአሮንም የተቀደሰውን ልብስ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው ፥ በመቅደሱ ለማገልገል ከሰማያዊ ከሐምራዊም ከቀይ ግምጃም በብልኀት የተሠራ ልብስ ለአሮንም የተቀደሰውን ልብስ አደረጉ። ዘፀ 39፥1
በሰንበት ት/ቤታችን በተለያዩ ጊዜያት የዝማሬ  አገልግሎት ይከናወናል። ቅዱስ እግዚአብሔርን በዝማሬ ለማመስገን ውድ አባላቶቻችን የተቀደሰውን ልብሰ ስብሐት በመልበስ ያገለግላሉ። የተቀደሰውን አገልግሎት ስናከናውን ከሰንበት ት/ቤት አልፈን በዓለማዊ እንቅስቃሴዎቻችን ላይም አርዓያ የሚሆን ባህርይ ማሳየት እንዳለብን ይታመናል። ሆኖም ግን አንዳንድ አባላቶችቻችን በተለይም ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ የሰንበት ት/ቤታችንን መተዳደርያ ደንብ የሚጥሱ ተግባራትን ሲያደርጉ አስተውለናል። ይህ ድርጊት ባለማወቅ ወይም በመዘንጋት መሆኑን በመገንዘብ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የቤተክርስቲያን ሥነምግባር ያልሆኑ ተግባራትን (ዘፈን ፣ ጭፈራ ...) የምታከናውኑ አባላት ከድርጊታችሁ እንድትታረሙ በጥብቅ እናሳስባለን። ከዚህ ድርጊታችሁ የማትታረሙ አባላት ሰንበት ት/ቤታችን በመተዳደርያ ደንቡ መሰረት ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ እናሳስባለን።
ከመንፈሳዊ ሰላምታ ጋር

መልክአ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በሰንበት ት/ቤታችን ልማት ተቋም ያገኙታል።
መልክአ ጴጥሮስ ወጳውሎስ
በሰንበት ት/ቤታችን ልማት ተቋም ያገኙታል።

🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯 "ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው" (መዝሙረ ዳዊት መዝ 89፤48 ) የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ የሆነችው የምህረት አያል አባት ስላረፉ የቀብር ሥርዓታቸውም ነ
🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯
"ሕያው ሆኖ  የሚኖር ሞትንስ  የማያይ ማን ነው" (መዝሙረ ዳዊት  መዝ 89፤48 )
የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ የሆነችው የምህረት አያል አባት ስላረፉ የቀብር ሥርዓታቸውም ነገ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም.  ከቀኑ በ6:00 በደብራችን በብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ስለሚፈጸም በዕለቱ ከቀኑ 05:30 ጀምሮ በሰንበት ት/ቤታችን በመገኘት ልብሰ ስብሐት እንድትለብሱ በትህትና እንጠይቃለን። በዕለተ ሰኞ (ሰኔ 29 ቀን 2018) ከምሽቱ 12:00 በመኖርያ ቤታቸው ተገኝተን ስለምናጽናና ሁላችሁም እንድትገኙ  በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። ለቤተሰቦቻቸው እግዚአብሔር መፅናናትን ይስጥልን!    📍 አድራሻ: ግሩም ሆስፒታል ጀርባ
"ኢየሱስም ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ይሆናል" ዮሐ 11፥25

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ኬፋ የኪነ ጥበብ ምሽት 🗒 ዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2018 ⏰ ከአመሻሹ 11:30 ጀምሮ 📍 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ኬፋ የኪነ ጥበብ ምሽት
🗒  ዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2018 ⏰  ከአመሻሹ 11:30 ጀምሮ 📍 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል

​🎓 ለሕጻናት ተመራቂዎች የሚሆን ልዩ መንፈሳዊ ስጦታዎች 🎁 ​በፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ልማት ተቋም ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ የሚከተሉትን ያገኛሉ፦ ✨ የተመረጡ መንፈሳዊ የሕጻናት ተረት መጻሕፍ
​🎓 ለሕጻናት ተመራቂዎች የሚሆን ልዩ መንፈሳዊ ስጦታዎች 🎁 ​በፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ልማት ተቋም ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ የሚከተሉትን ያገኛሉ፦ ✨ የተመረጡ መንፈሳዊ የሕጻናት ተረት መጻሕፍት ✨ ልዩ ልዩ ቅዱሳት ሥዕላት ✨ የተለያዩ የሥዕልና ኖርማል ደብተሮች ✨ከለር ፣እስራስ፣መቅረጫ፣ላፒስ ✨ የስጦታ ጥቅል(ፖኬጅ) ✨ እንዲሁም የልጆች የፊደል፣ የቁጥር፣ የሥዕል መለማመጃዎች እና ሌሎችም ለስጦታ የሚሆኑ ንዋያተ ቅድሳት እኛ ጋር ይገኛሉ ይምጡ ይጎብኙን ​📍 አድራሻ፦ ዊንጌት ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ እና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን (ከዋናው በር በስተቀኝ) ​⏰ የስራ ሰዓት፦ ከእሑድ እስከ እሑድ (ጠዋት 1:30 - ማታ 2:00) ​☎️ ለበለጠ መረጃ እና ለማዘዝ፦ 📞 0932185663 📞 0930594059 📞 0974344475 ​📲 የቴሌግራም 👇    @LMATTQUWAM

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ኬፋ የኪነ ጥበብ ምሽት 🗒 እሑድ ሰኔ 21 ቀን 2018 ⏰ ከአመሻሹ 11:30 ጀምሮ 📍 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ኬፋ የኪነ ጥበብ ምሽት
🗒 እሑድ ሰኔ 21 ቀን 2018 ⏰ ከአመሻሹ 11:30 ጀምሮ 📍 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል