es
Feedback
ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

Ir al canal en Telegram

በብ/ዓ/ቅ/ጴጥሮስ ወጳውሎስ እና ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ የፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ገጽ ነው

Mostrar más
3 115
Suscriptores
+724 horas
+347 días
+7630 días
Archivo de publicaciones
🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯 "ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው" (መዝሙረ ዳዊት መዝ 89፤48 ) የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ የሆኑት የነፃነት ፍቃዱ እና ኢየሩሳሌም ፍቃዱ አባት ስላረፉ የ
🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯
"ሕያው ሆኖ  የሚኖር ሞትንስ  የማያይ ማን ነው" (መዝሙረ ዳዊት  መዝ 89፤48 )
የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ የሆኑት የነፃነት ፍቃዱ እና ኢየሩሳሌም ፍቃዱ አባት ስላረፉ የቀብር ሥርዓታቸውም ነገ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም.  ከቀኑ 8:00 በአዲስዓለም ማርያም ስለሚፈጸም መሄድ የምትፈልጉ አባላት እስከ ነገ ጠዋት 3:00 ድረስ ከዚህ በታች በተቀመጠው ስልክ እየደወላችሁ እንድትመዘገቡ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። ለመመዝገብ: ☎️ 0921392941 በመኖርያ ቤታቸው ተገኝተን የምናጽናናበትን ጊዜ በቅርቡ እናሳውቃለን። ለቤተሰቦቻቸው እግዚአብሔር መፅናናትን ይስጥልን! 📍 አድራሻ: አዲስዓለም
"ኢየሱስም ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ይሆናል" ዮሐ 11፥25

Surafel: በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን የተከበራችሁ ውድ የሰንበት ት/ቤታችን ባለትዳር አባላት ፣ ሰንበት ት/ቤታችን በቅርቡ ለሚያዘጋጀው የባለትዳሮች ጉባዔ ይረዳን ዘንድ ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠርያ በመጠቀም መረጃውን እንዲሞሉ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። https://airtable.com/appgeor2lPSqEVxQ8/pagB98OYM90PqldID/form
ዓላማ: የዚህ ቅፅ መሞላት ዋና ዓላማ ሰንበት ት/ቤታችን ለሚያዘጋጀው ኦርቶዶክሳዊ የቤተሰብ ቀን (የባለትዳሮች ጉባዔ) በሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆኑ ባለትዳሮችን መረጃ መሰብሰብ ነው።
ለበለጠ መረጃ: ☎️ 0911885015 ☞ ዘገየ ከበደ ☎️ 0930389858 ☞ ዓለማየሁ ሽታው

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! አንደኛው በመስቀል ላይ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ አንደኛው ክብርት አንገቱን ተቆረጠ። የቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ የሰማዕትነት ክብረ በዓል የመዝሙ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
አንደኛው በመስቀል ላይ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ አንደኛው ክብርት አንገቱን ተቆረጠ።
ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ የሰማዕትነት ክብረ በዓል የመዝሙር ጥናት ዛሬ ሰኔ 7/2018 ዓ.ም. 11:30 ላይ በልዩ ጉባዔ ይጀመራል።
ሁላችሁም የሰንበት ት/ቤታችን አባላት ተጋብዛችኋል።

🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯 "ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው" (መዝሙረ ዳዊት መዝ 89፤48 ) የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ የሆነቸው የአበበች አያሌው አባት ስላረፉ እና የቀብር ሥርዓታቸ
🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯
"ሕያው ሆኖ  የሚኖር ሞትንስ  የማያይ ማን ነው" (መዝሙረ ዳዊት  መዝ 89፤48 )
የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ የሆነቸው የአበበች አያሌው አባት ስላረፉ እና የቀብር ሥርዓታቸውም ስለተፈፀመ በነገው ዕለት እሑድ (ሰኔ 7 ቀን 2018) ከምሽቱ 12:00 በመኖርያ ቤታቸው ተገኝተን ስለምናጽናና ሁላችሁም እንድትገኙ  በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። ለእህታችን እና ለመላው ቤተሰብ እግዚአብሔር መፅናናትን ይስጥልን!    በስልክ ማፅናናት ለምትፈልጉ ... ☎️ 0911833699 | አበበች አያሌው 📍 አድራሻ: ሸጎሌ ከቴሌው ገባ ብሎ
"ኢየሱስም ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ይሆናል" ዮሐ 11፥25

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው ፥ በመቅደሱ ለማገልገል ከሰማያዊ ከሐምራዊም ከቀይ ግምጃም በብልኀት የተሠራ ልብስ ለአሮንም የተቀደሰውን ልብስ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው ፥ በመቅደሱ ለማገልገል ከሰማያዊ ከሐምራዊም ከቀይ ግምጃም በብልኀት የተሠራ ልብስ ለአሮንም የተቀደሰውን ልብስ አደረጉ። ዘፀ 39፥1
በሰንበት ት/ቤታችን በተለያዩ ጊዜያት የዝማሬ  አገልግሎት ይከናወናል። ቅዱስ እግዚአብሔርን በዝማሬ ለማመስገን ውድ አባላቶቻችን የተቀደሰውን ልብሰ ስብሐት በመልበስ ያገለግላሉ። የተቀደሰውን አገልግሎት ስናከናውን ከሰንበት ት/ቤት አልፈን በዓለማዊ እንቅስቃሴዎቻችን ላይም አርዓያ የሚሆን ባህርይ ማሳየት እንዳለብን ይታመናል። ሆኖም ግን አንዳንድ አባላቶችቻችን በተለይም ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ የሰንበት ት/ቤታችንን መተዳደርያ ደንብ የሚጥሱ ተግባራትን ሲያደርጉ አስተውለናል። ይህ ድርጊት ባለማወቅ ወይም በመዘንጋት መሆኑን በመገንዘብ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የቤተክርስቲያን ሥነምግባር ያልሆኑ ተግባራትን (ዘፈን ፣ ጭፈራ ...) የምታከናውኑ አባላት ከድርጊታችሁ እንድትታረሙ በጥብቅ እናሳስባለን። ከዚህ ድርጊታችሁ የማትታረሙ አባላት ሰንበት ት/ቤታችን በመተዳደርያ ደንቡ መሰረት ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ እናሳስባለን።
ከመንፈሳዊ ሰላምታ ጋር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የእርዳታ ጥሪ የሰንበት ት/ቤታችን የህፃናት እና አዳጊ ትምህርት የአዳጊ 2 (4ኛ ክፍል) ተማሪ የሆነችው ህፃን ማዕዶት ስለሺ ለገሰ ባጋጠማት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የእርዳታ  ጥሪ
የሰንበት ት/ቤታችን የህፃናት እና አዳጊ ትምህርት የአዳጊ 2 (4ኛ ክፍል) ተማሪ የሆነችው ህፃን ማዕዶት ስለሺ ለገሰ ባጋጠማት የደም ካንሰር ህመም ምክንያት ሆስፒታል ውስጥ በካንሰር ህሙማን ክትትል ውስጥ ትገኛለች። የተከበራችሁ ውድ የፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ቤተሰቦች ይህችን የ9 ዓመት ታዳጊ ለመርዳት በፀሎት እንድታስቡዋት እና የምትችሉትን ሁሉ እንድታደርጉላት ስንል በአምላከ ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ስም እንጠይቃለን። CBE | 1000471352431 | ኪያ አቦማ እና ሄኖክ ታደሰ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! አንደኛው በመስቀል ላይ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ አንደኛው ክብርት አንገቱን ተቆረጠ። የቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ የሰማዕትነት ክብረ በዓል የመዝሙ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
አንደኛው በመስቀል ላይ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ አንደኛው ክብርት አንገቱን ተቆረጠ።
ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ የሰማዕትነት ክብረ በዓል የመዝሙር ጥናት ሰኔ 7/2018 ዓ.ም. 11:30 ላይ በልዩ ጉባዔ ይጀመራል።
ሁላችሁም የሰንበት ት/ቤታችን አባላት ተጋብዛችኋል።

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በአዲሱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መዋቅር የሚመረጡ የሥራ አመራር አባላት የሚያስተባብሩት ክፍላት እነማን ናቸው? የብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
በአዲሱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መዋቅር የሚመረጡ የሥራ አመራር አባላት የሚያስተባብሩት ክፍላት እነማን ናቸው?
የብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ እና ቅዱስ ገብርኤል አብያተ ክርስቲያናት ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መዋቅር መሰረት የከፍተኛ መደብ 1 መዋቅር ላይ እንዳረፈ ይታወቃል። በዚህም መሰረት በከፍተኛ መደብ 1 ላይ የሚኖሩት ክፍላት የሚከተሉት ናቸው።
የሥራ አመራር ጽ/ቤት
💢 ሰብሳቢ 💢 ምክትል ሰብሳቢ 💢 ዋና ጸሐፊ 🔸 የጽ/ቤት ኃላፊ
ዋና ዋና ማስተባበርያ ክፍላት
1⃣ ዕቅድ ፣ ጥናትና ምርምር ማስተባበርያ 2⃣ ሚዲያና ሕዝብ ግንኙነት ማስተባበርያ 3⃣ የትምህርትና እቅበተ ዕምነት ማስተባበርያ 4⃣ የአባላትና ተቋም አደረጃጀት ማስተባበርያ 5⃣ መረጃና ወቅታዊ ጉዳይ ማስተባበርያ 6⃣ ምጣኔ ሀብትና ማሕበራዊ አገልግሎት ማስተባበርያ 7⃣ ሒሳብና ንብረት አስተዳደር ማስተባበርያ 8⃣ ቴክኖሎጂ ትስስር ማስተባበርያ 🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸 በምልዓተ ጉባኤው ሰንበት ት/ቤታችንን ለቀጣይ 3 ዓመታት የሚያገለግሉ የሥራ አመራር አባላት ከተመረጡ በኋላ በተመረጡት ሥራ አመራሮች አማካኝነት 10 የሥራ አስፈፃሚ አባላት ይመረጣሉ።
የሥራ አስፈፃሚ ዋና ዋና ክፍላት
💢 የሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት 1⃣ ዕቅድ ትግበራ እና ክትትል 2⃣ ትምህርት እና ሥልጠና 3⃣ መርሐግብር እና ጉባኤያት 4⃣ መረጃ እና የውስጥ ግንኙነት 5⃣ መዝሙር እና በዓላት ዝግጅት 6⃣ ኪነ ጥበብ እና ሥነ ጥበብ 7⃣ የሰው ሀብት አስተዳደር 8⃣ ልማት እና በጎ አድራጎት 9⃣ በጀት እና ንብረት አስተዳደር
🗒 ነገ ግንቦት 30 | ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ

🗒 ነገ ጠዋት ከ2:30 ጀምሮ
🗒 ነገ ጠዋት ከ2:30 ጀምሮ

🗒 ግንቦት 30 ⏰ ጠዋት 2:30 📌 የተተኪ ሥራ አመራር አባላት ምርጫ ሰንበት ት/ቤታችንን ለቀጣይ 3 ዓመታት በሥራ አመራርነት የሚያገለግሉ አባላት ይመረጣሉ።
🗒 ግንቦት 30 ⏰ ጠዋት 2:30
📌 የተተኪ ሥራ አመራር አባላት ምርጫ
ሰንበት ት/ቤታችንን ለቀጣይ 3 ዓመታት በሥራ አመራርነት የሚያገለግሉ አባላት ይመረጣሉ።

በአዲሱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መዋቅር መሰረት በከፍተኛ መደብ 1 መዋቅር አማካኝነት ሰንበት ት/ቤታችንን ለቀጣይ 3 ዓመታት የሚያገለግሉ የሥራ አመራር አባላትን ለመምረጥ 3 ቀናት ብቻ ቀርተዋል
በአዲሱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መዋቅር መሰረት በከፍተኛ መደብ 1 መዋቅር አማካኝነት ሰንበት ት/ቤታችንን ለቀጣይ 3 ዓመታት የሚያገለግሉ የሥራ አመራር አባላትን ለመምረጥ 3 ቀናት ብቻ ቀርተዋል።
ግንቦት 30 ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በፍፁም አይቀርም!

🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯 "ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው" (መዝሙረ ዳዊት መዝ 89፤48 ) የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ የሆኑት የዲ/ን እሱባለው ይሁኔ እና ማናየሽ ይሁኔ አባት ስላረ
🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯
"ሕያው ሆኖ  የሚኖር ሞትንስ  የማያይ ማን ነው" (መዝሙረ ዳዊት  መዝ 89፤48 )
የሰንበት ት/ቤታችን አገልጋይ የሆኑት የዲ/ን እሱባለው ይሁኔ እና ማናየሽ ይሁኔ አባት ስላረፉ የቀብር ሥርዓታቸውም ነገ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.  ከቀኑ በ9:00 በአስኮ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ስለሚፈጸም በዕለቱ ከቀኑ 08:00 ጀምሮ በሰንበት ት/ቤታችን በመገኘት ልብሰ ስብሐት እንድትለብሱ በትህትና እንጠይቃለን። በዕለተ ሐሙስ (ግንቦት 27 ቀን 2018) ከምሽቱ 12:00 በመኖሪያ ቤታቸው ተገኝተን ስለምናጽናና ሁላችሁም እንድትገኙ  በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። ለቤተሰቦቻቸው እግዚአብሔር መፅናናትን ይስጥልን!    📍 አድራሻ: ዊንጌት ካ.ኦ.ጄ.ጄ አለፍ ብሎ
"ኢየሱስም ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ይሆናል" ዮሐ 11፥25

ውድ የፍሬ ሃይማኖት ልጆች እንደምን ከረማችሁ? እንደ እግዚአብሔር መልካም ፍቃድ ከደብሩ በተቀበልነው ቦታ ላይ ለሰንበት ት/ቤታችን ሁለገብ አገልግሎት የሚሆን ደረጃውን የጠበቀ ሕንጻ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተጥሎ ፣ ኮሚቴ ተዋቅሮ በእንቅስቃሴ ላይ እንገኛለን።

🗓 ግንቦት 30 | 2018 ⏰ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ 🎯 ሰንበት ት/ቤታችንን ለቀጣይ 3 ዓመታት የሚያገለግሉ የተተኪ ሥራ አመራር አባላት ምርጫ ይከናወናል።
🗓 ግንቦት 30 | 2018 ⏰ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ
🎯 ሰንበት ት/ቤታችንን ለቀጣይ 3 ዓመታት የሚያገለግሉ የተተኪ ሥራ አመራር አባላት ምርጫ ይከናወናል።