ልህቀት የንባብ ባህል ማጎልበቻ ማዕከል
Відкрити в Telegram
እናንብብ እንለወጥ !! " ንባብ የአእምሮ ምግብ ነው " 📞 +25190 112 2031 https://t.me/Lihket_Reading
Показати більше2 509
Підписники
-124 години
-17 днів
-1030 день
Архів дописів
“የሕይወታችን ጥራት የሚወሰነው በውሳኔዎቻችን ጥራት ነው” ይባላል!
በጊዜ ሂደት ደጋግመን የምናደርጋቸው ምርጫዎች፤ ግንኙነታችንን፣ ጤናችንን፣ ፋይናንሳችንን (የኢኮኖሚ ደህንነታችንን) እና በመጨረሻም ባህሪያችንንና ማንነታችንን ይቀርጻሉ።
ትልቅም ይሁን ትንሽ፣ እያንዳንዱ ውሳኔ የራሱ የሆነ ውጤት አለው። አንድ ነጠላ ውሳኔ እምብዛም አስፈላጊ እንዳልሆነ ሊመስል ይችላል፤ ነገር ግን የበርከቶች ዕለታዊ ምርጫዎች ድምር ውጤት የሕይወታችንን አቅጣጫ እና ጥራት ይወስናል።
መልካም ውሳኔዎች አወንታዊ ውጤቶችን የማስገኘት ዝንባሌ ያላቸው ሲሆን፣ ደካማ ውሳኔዎች ደግሞ ብዙውን ጊዜ ወደማይፈለጉ መዘዞች ይመራሉ ።
ሕይወት በአንድ አስገራሚ ውሳኔ ብቻ የመቀየር አጋጣሚዋ ጠባብ ነው። ይልቁንም፣ ቀስ በቀስ ወደ ልማድ በሚቀየሩ ወጥ የሆኑ ዕለታዊ ምርጫዎች የምትቀረጽ ናት።
እነዚህ ልማዶች ባህሪያችንን ይገነባሉ፣ ባህሪያችን ደግሞ ዕጣ ፈንታችንን ይወስናል።
ይህንን አንዘንጋ . . .
የወደፊት ሕይወታችን በአብዛኛው ዛሬ የምናደርጋቸው ውሳኔዎች ውጤት ነው።
የሕይወታችንን ጥራት ማሻሻል ከፈለግን፣ መጀመሪያ የውሳኔዎቻችንን ጥራት በማሻሻል እንጀምር።
ዛሬ እነዚህን ጥያቄዎች ለመጠየቅና ለመመለስ እንሞክር
* እስካሁን በሕይወቴ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ያሳደሩት አስፈላጊ ውሳኔዎች የትኞቹ ናቸው?
* ዕለታዊ ምርጫዎቼን ወደ ግቦቼ እያስጠጉኝ ነው ወይስ ከግቦቼ እያራቁኝ?
* ለወደፊት ሕይወቴ አወንታዊ ተጽዕኖ ሊያበረክት የሚችል፣ ዛሬ ልወስነው የምትችለው አንድ ውሳኔ ምንድን ነው?
* የበለጠ ጥበባዊ ውሳኔዎችን የማድረግ ልማድን እንዴት ማዳበር እችላለሁ?
እያንዳንዱ ምርጫችን፣ ወደፊት ለምንሆነው ማንነትና ለምንኖረው ኑሮ እጅግ ወሳን መሆኑን አንዘንጋ፡፡
ሳትገደዱ ለውጡ!
(“የትራንስፎርሜሽን አመራር” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)
“ልክ ሕይወትን እንዴት መኖር እንዳለብኝ ያወቅሁ ሲመስለኝ ህይወት ትለወጣለች” - Hugh Prather
በሕይወታቸው ባሉበት ከመርገጥና ወደኋላ ከመቅረት ራሳቸውን ነጻ ያወጡ ሰዎች የለውጥን እውነታ የተገነዘቡ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ዛሬ አወኩት፣ ተገነዘብኩት፣ ለመድኩት ያሉት ሁኔታ ነገ ካለምንም ማስጠንቀቂያ ተለወጦ እንደሚያገኙት በሚገባ ገብቷቸዋል፡፡ ስለሆነም ካለማቋረጥ አመለካከታቸውን፣ አደራረጋቸውንና ሕይወታቸውን እያሻሻሉና እየለወጡ ይኖራሉ፡፡
የሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ትንቢቶች
ሃርቫርድ የተሰኘው ታዋቂ ዩኒቨርስቲ ለውጥን አስመልክቶ ሶስት እውነታዎችን እንደተነበየ ብራያንና ፒተር ያስታውሱናል፡፡
1. አሁን በተሰማራህበት የስራ ወይም የንግድ ዘርፍ ውስጥ በመጪው ጥቂት አመታት ውስጥ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ በርካታ ለውጦች ይከሰታሉ፡፡
2. አሁን በተሰማራህበት የስራ ወይም የንግድ ዘርፍ ውስጥ በመጪው ጥቂት አመታት ውስጥ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ የጋለ ውድድርና ፉክክር ይከሰታል፡፡
3. አሁን በተሰማራህበት የስራ ወይም የንግድ ዘርፍ ውስጥ በመጪው ጥቂት አመታት ውስጥ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ በርካታ የእድል በሮች ይከፈታሉ፤ ሆኖም እነዚህ እድሎች አሁን ከምታደርጋቸው ነገሮች እጅግ የተለዩ ናቸው፡፡
ከቻላችሁ የለውጥ መልእክተኛ ሁኑ፡፡ ያንን ማድረግ ካልቻላችሁ ግን ቢያንስ ከለውጥ ጋር የምትራመዱ ሁኑ!
ሰላም የልህቀት ቤተሰቦች ዛሬ እንደተለመደው ወንድማችን ሳሙኤል ልዩ ሀሳብ ይዞ ብቅ ይላል በተለየ መልክ ማታ 3 ሰዓት እንገናኝ የተወደደች እህታችን ማርቲና ፕሮገራም በማሳለጥ አለች ።
የማይካድ ሀቅ!!!
• ለራሳችሁ ፕሮግራም ካላወጣችሁ፣ ሰዎች ፕሮግራም ያወጡላችኋል፡፡
• የራሳችሁን ሕይወት ካልመራችሁ፣ ሰዎች ወደፈለጉበት ይመሯችኋል፡፡
• ሕይወታችሁን በመልክ በመልኩ ካላደረጃችሁት፣ የመጣውን ሁኔታ ሁሉ እየተቀበላችሁ ለመኖር ትገደዳላችሁ፡፡
• እቅድ አውጥታችሁ የምትከተሉት ነገር ከሌላችሁ፣ ከሁኔታዎች እንደሸሻችሁ ትኖራላችሁ፡፡
• ብዙ እምቅ ብቃት ኖሯችሁ ካለምንም እቅድ እና አደረጃጀት ከኖራችሁ፣ ምንም እውቀት የሌላቸውና የተደራጁት እንደነዷችሁ ትኖላችሁ፡፡
አስቡበት
Addis Admass:
ከ4 ወጣቶች አንዱ ከሰው ይልቅ ከቻትጂፒቲ
ጋር ማውራት ይመርጣል - አዲስ ጥናት
በቅርቡ ይፋ የሆነ አዲስ የጥናት መረጃ እንደሚያሳየው፤ ከአራት ወጣቶች መካከል አንዱ ከእውነተኛ ሰው ይልቅ ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር መገናኘትና ማውራትን ይመርጣል። በዩናይትድ ኪንግደም ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 29 በሆኑ 2,000 ወጣቶች ላይ የተደረገው ይህ ጥናት፤ ከሁለት ሶስተኛ በላይ የሚሆኑት ወጣቶች ከሰዎች ጋር ያላቸውን ቀጠሮ ሰርዘው በኢንተርኔት ላይ ጊዜ ማሳለፍን እንደሚመርጡ አረጋግጧል።
በተጨማሪም ከተጠኚዎቹ መካከል ሁለት ሶስተኛ የሚሆኑት ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜ የብቸኝነት ስሜት እንደሚሰማቸው የተናገሩ ሲሆን፣ ወደ ግማሽ የሚጠጉት ደግሞ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸው የብቸኝነት ስሜታቸውን ይበልጥ እንዳባባሰው ገልጸዋል።
ብዙ ወጣቶች ወደ ኤአይ የሚሳቡት ያለምንም ፍርሃትና መፈረጅ የራሳቸውን እውነተኛ ማንነት ማንጸባረቅ ስለሚችሉ እንደሆነ በጥናቱ ተመልክቷል። ለአብነት ያህል፣ አንዲት የ22 ዓመት ወጣት በጭንቀትና በብቸኝነት ወቅት የነበራትን ተሞክሮ ስትገልጽ፤ የሰዎችን ትችት በመፍራት ስሜቷን ለማጋራት ወደ ChatGPT ትሮጥ እንደነበርና ይህም ስሜቷ ትክክል መሆኑን እያረጋገጠ ያጽናናት እንደነበር ተናግራለች። ነገር ግን ከጊዜ በኋላ ኤአይ ሰዎችን ለማስደሰት ብቻ ታቅዶ የተሰራ በመሆኑ ሁልጊዜ እኛን ደጋፊና ሚዛናዊ ያልሆነ ምላሽ እንደሚሰጥ መረዳቷን አክላለች። ይህ የብቸኝነት ስሜት በወጣቶች የአእምሮ ጤና፣ በራስ መተማመን፣ እንቅልፍና በትምህርት አፈጻጸማቸው ላይ ጭምር አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል።
ይህንን እያደገ የመጣውን የቴክኖሎጂ ጥገኝነትና የወጣቶች ብቸኝነት ተከትሎ፣ የማርማሌድ ትረስት የተባለው የበጎ አድራጎት ድርጅት መስራች፣ ብቸኝነት ተፈጥሯዊ ስሜት መሆኑንና በግልፅ መወያየት መፍትሄ ለማግኘት እንደሚረዳ አሳስበዋል። በሌላ በኩል፣ ይህንን በማህበራዊ ሚዲያና በቴክኖሎጂ ምክንያት በወጣቶች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ መንግስታት የተለየ ትኩረት እየሰጡት ይገኛሉ። ለምሳሌ በዩናይትድ ኪንግደም ከ16 ዓመት በታች ለሆኑ ታዳጊዎች የማህበራዊ ሚዲያ እገዳ ለመጣል የመንግስት ባለስልጣናት እያሰቡበት ሲሆን፣ በቅርብ ሳምንታት ውስጥም ትልቅ ለውጥ የሚያመጡ የአሰራር እርምጃዎች ይፋ እንደሚደረጉ ይጠበቃል።
#የቴክኖሎጂተፅዕኖ #አርቲፊሻልኢንተለጀንስ #የወጣቶችጤና #ብቸኝነት #የማህበራዊሚዲያ
ሰላም ወዳጆቼ ዛሬ እለተ አርብ ነው ደግሞ በተከታታይ አርቦች ባለመቻላችን ፕሮግራማችን ተቋርጦ ቆይቷል ዛሬ ማታ ተገናኝተን አንዳንድ ሀሳቦቸሰ ብናወራ ምን ይመስላችኋል ?
ለማንኛውም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ይጠብቁን
Addis Admass:
በየቀኑ ጥቂት ፍሬ ለውዝ መመገብ
የሚያስገኟቸው አስገራሚ ጥቅሞች!
ለውዝ እና መሰል የዛፍ ፍሬዎችን (Nuts) በዕለት ተዕለት የምግብ ዋስትናችን ውስጥ ካላካተትን፣ ልባችንን የሚጠብቁ፣ የኮሌስትሮል መጠንን የሚቀንሱና የተለያዩ በሽታዎችን የሚከላከሉ እጅግ ጠቃሚ ንጥረ ነገሮችን እያጣን ነው። እነዚህ የኮሌስትሮል መጠንን ዝቅ የሚያደርጉ የፋይበር ዓይነቶች ለረጅም ጊዜ የመጥገብ ስሜት እንዲሰማን በማድረግ የምግብ ፍላጎትን ያስተካክላሉ። በውስጣቸው የያዙት "ጥሩ" ስብ፣ ኦሜጋ-3 ፋቲ አሲድ እና ቫይታሚን ኢ በደም ቅዳ ቧንቧዎች ውስጥ የስብ ክምችት እንዳይፈጠር ይከላከላሉ።
ጥናቶች እንደሚያሳዩት በብዛት ለውዝ መመገብ የልብ በሽታ ተጋላጭነትን በ24 በመቶ ከመቀነሱም በላይ፣ በዕድሜ የገፉ ሰዎችን የአእምሮ ንቃት ያሻሽላል፣ አጠቃላይ የዕድሜ ዘመንን ይጨምራል። ነገር ግን፣ ከፍተኛ የካሎሪ መጠን ስላላቸው፣ መጠናቸውን ጠብቆ (በቀን 1 አውንስ ወይም አንድ እጅ ጭብጥ) እና ሳይቀመሙ (በጨው፣ በስኳር ወይም በቸኮሌት) መመገብ ይመረጣል።
1. ዋልናት (Walnuts)፣ አልሞንድ (Almonds) እና ካሼው (Cashews)
እያንዳንዱ የለውዝ ዝርያ የራሱ የሆነ ልዩ የጤና ጠቀሜታ አለው። ለምሳሌ ዋልናት ከፍተኛ የአንቲኦክሲዳንት እና የኦሜጋ-3 ይዘት ስላለው የአእምሮን ስራ ያሻሽላል፣ እንዲሁም የልብ በሽታ፣ ድብርት እና ስኳር በሽታን በመከላከል የአእምሮ መርሳት አደጋን ይቀንሳል። አልሞንድ ደግሞ በከፍተኛ የፋይበር ይዘታቸው ይታወቃሉ፤ ይህም የሆድ አካባቢ ስብን ለመቀነስና ክብደትን ለመቆጣጠር ከመርዳቱ ባለፈ፣ በሆዳችን ውስጥ ያሉ ጠቃሚ ባክቴሪያዎችን (Prebiotics) ያሻሽላል። ካሼው በበኩላቸው የሰውነታችን ሴሎች ኦክስጅን እንዲያገኙ የሚያደርገውን ብረት (Iron) እና በሽታ የመከላከል አቅምን የሚያጠናክረውን ዚንክ ይዘዋል። በተጨማሪም መካከለኛ የኮሌስትሮል ችግር ላለባቸው ሰዎች የ‘መጥፎ’ ኮሌስትሮል መጠንን ለመቀነስና የአእምሮን ተግባር ለማነቃቃት ይረዳሉ።
2. ፒካን (Pecans)፣ ብራዚል ነት (Brazil Nuts) እና ማካዳሚያ (Macadamia Nuts)
በአንቲኦክሲዳንት የበለፀጉት ፒካን በደም ቅዳ ቧንቧዎች ላይ ቆሻሻ እንዳይከማች የሚከላከሉ ሲሆን፣ በውስጣቸው ያለው ፖሊፊኖል (የተባለ ንጥረ ነገር የኢንሱሊን ስሜትን በማሻሻል ለስኳር በሽታ የመጋለጥ እድልን ይቀንሳል። በአንጻሩ ብራዚል ነት ለአንድ ሰው በቀን የሚያስፈልገውን የሴሊኒየም (Selenium) ማዕድን ከ100 በመቶ በላይ በአንድ ፍሬ ብቻ ማሟላት ይችላሉ፤ ይህ ማዕድን ለታይሮይድ እጢ፣ ለዲኤንኤ ምርት እና ለሰውነት መከላከያ ወሳኝ ቢሆንም፣ ከልክ በላይ መውሰድ ጉዳት ስላለው በብዛት መወሰድ የለበትም። ማካዳሚያ ምንም እንኳን ከፍተኛ ካሎሪ ቢኖራቸውም፣ የልብ ጤንነትን የሚጠብቅ "ጥሩ ስብ" (Monounsaturated fat) የያዙ በመሆናቸው፣ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ አጠቃላይ የኮሌስትሮል እና የደም ግፊት መጠንን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ይችላሉ።
3. ፒስታቺዮ (Pistachios) እና ሄዘልናት (Hazelnuts)
በመጨረሻም ፒስታቺዮ ቅርፊታቸው እየተላጠ ስለሚበላ በዝግታ እንድንመገብና የምግብ ፍላጎታችንን እንድንቆጣጠር የሚያደርጉ ለየት ያሉ ፍሬዎች ናቸው። አዲስ ሴል ለመስራት የሚረዳውን ፎሌት፣ ለዓጥንት ጤንነት የሚጠቅመውን ቫይታሚን ኬ ፣ እንዲሁም መዳብ እና ማንጋኒዝ የተባሉ ማዕድናትን አምቀው የያዙ ናቸው። ሄዘልናት ደግሞ የልብና የደም ቧንቧ ጤንነትን የሚያሻሽሉ እና ዓይነት 2 የስኳር በሽታን ለመቆጣጠር የሚረዱ እጅግ በጣም ጠቃሚ ፍሬዎች ናቸው። እነዚህ ፍሬዎች ሥር የሰደዱ እንደ ካንሰር፣ የልብ ሕመም እና የተለያዩ የማበጥ በሽታዎችን የመከላከል ከፍተኛ አቅም አላቸው። ባጠቃላይ፣ እነዚህን የተለያዩ የለውዝ አይነቶች በየቀኑ በተመጣጠነ መልኩ መመገብ ለጤናችን ዘላቂ ዋስትና ይሰጣል።
EVERY DAY HEALTH-
ወደ ቦታችሁ ተመለሱ!
በቅርቡ መንታ ወልዶ ያስደመመን ወዳጄ ኢብሳ ቡርቃ፣ "ማኅደረ አቦል" በተሰኘው መጽሐፉ ያካፈለውን እውነት፣ ትዝብት፣ ብሶት፣ ... እጋራለሁ። በተለይ "ወደ ቦታችሁ ተመለሱ!" የሚለው መጣጥፍ የእኔም ጩኸት ነው።
ምን የሚያስጮህ ነገር ተገኘ? ያላችሁ እንደው ጽንፈኝነታችን።
ለዘመናት ሴቶች ላይ ይደርስ ለነበረው ጥቃት ፍትሕ፣ ለጨቋኙንም ሥርዐት መስመር ከማበጀት ይልቅ የወንድን ሥነ ልቦና መምታት ቀሎናል። ከአንዱ ጥግ ወደ ሌላኛው ጥግ የተስፈነጠርንበት ፍጥነት የሚያስከትለው አደጋም የታየን አይመስልም። ደራሲው፣ አባታዊ ሽንቁር (Father wound) ያመጣብንን የስሜት ቀውስ ሳናክም የሆሊውድ መንደር ሠርቶ የሰጠንን ተቀባዮች ነን ሲል ይተቻል። ትችቱ አግባብነት ያለው ነው።
- "ወንዶች የዘር ፍሬ ከማቀበል በዘለለ በማኅበረ ሰብ ግንባታ ውስጥ የረባ ሚና የላቸውም" ስንባል ተባብረን "ሐሰት!" አላልንም። እንደውም በርግጥ ለማለት ቸኮልን።
- "ወንድነት ልፍስፍስነት፣ ሴትነት ሕጸጽ አልባነት ነው" ስንባልም ወዴት ሊወስዱን ፈልገው ነው? አላልንም። ብለንም ከኾነ ድምፃችን አልተሰማም።
- በፊልሞቻችን ክፉና ደግ ያልለዩ ሕጻናት አባቶቻቸውን በዕውቀት የሚበልጡ ኾነው ሲሣሉ ለምን አላልንም። አባቶች ተላላ ኾነው መቅረባቸው አላስደነገጠንም። ኧረ እንደውም "ሞኝ አይሙት እንዲያጫውት" እያልን ሳንስቅ አንቀርም።
ታዲያ ይኼ ምን አስከተለ?
ደራሲው እንዳለው እናቶች ብቻቸውን ልጆቻቸውን ማሳደግ ይችላሉ የሚል ሐሳብ ጫነብን። እንዲኽ ያሉም ሴቶች ራሳቸውን የቻሉ፣ የበቁና የነቁ ተደርገው ተሣሉ። በየሰበቡ የቤተ ሰብ መሠረት ተናደ።
እና ምን ተሻለን?
የጠቀስኩት መጣጥፍ፣ መላው ባሎችና አባቶች ወደ ቤታቸው መመለሳቸው ነው። ወደ ቦታ መመለስ ኅብረተ ሰባዊ ቀውስን ይፈወሳል የሚል ጥቅል ሐሳብ ተሸክሟል። "ከወንድ ወገብ ያልወጣች ሴት፤ በሴት ማሕፀንም ያላደረ ወንድ የለም"ብሎም ይደመድማል።
እስቲ አንብቡት።
ሊዲያ እንደከተበችሁ
በሳይንስ የተረጋገጡ የሙዝ አስደናቂ ጥቅሞች!
ሙዝ በውስጡ እንደ ማግኒዚየም፣ ፖታሲየም፣ አይረን እና ልዩ ልዩ ቪታሚኖችን አምቆ የያዘ ድንቅ ፍሬ ነው። ይህ ፍሬ ለሰውነታችን ቀዳሚ የኃይል ምንጭ ከመሆኑም ባለፈ፣ ከፍተኛ የፋይበር ይዘት ስላለው የምግብ መፈጨት ሥርዓትን ያቀላጥፋል። በተለይም የጨጓራ አሲድን በመቀነስ የጨጓራ ግድግዳን የሚያጠናክር ሲሆን፣ በፖታሲየም የበለፀገ በመሆኑም የልብን ጤንነት ለመጠበቅና የደም ግፊትን ለማመጣጠን ወደር የሌለው የጤና ጠቀሜታ ይሰጣል።
ከውስጣዊ ጤና ባለፈ ሙዝ ለውበትና ለቆዳ ጥበቃ ትልቅ ሚና አለው። በቪታሚን ኤ ይዘቱ የአይንን ጤና ከማሻሻሉም በላይ፣ የቆዳ መሸብሸብንና መሰንጠቅን ይከላከላል። የሚገርመው ደግሞ የሙዝ ልጣጭ ጥርስን ለማንጣትና በወባ ትንኝ የተነደፈን የቆዳ አካል ለማከም መርዳቱ ነው። በተጨማሪም በብረት (Iron) ማዕድን የበለፀገ ስለሆነ የደም ማነስን (አኔሚያን) ለመከላከልና ነፍሰጡር እናቶችን ከጠዋት ህመም ለመታደግ እጅግ ተመራጭ ፍሬ ያደርገዋል።
ክብደትን ለመቀነስ ለሚፈልጉ ሰዎች ሙዝ አነስተኛ ቅባትና ከፍተኛ ፋይበር ስላለው ሆድን የመሙላት ስሜት በመፍጠር ለረጅም ሰዓት የምግብ ፍላጎትን ይቆጣጠራል። እንዲሁም በውስጡ ባለው ከፍተኛ የፖታሲየም ክምችት የኪንታሮት በሽታን ለማከም ይረዳል። በአጠቃላይ ሙዝን የዕለት ተዕለት የምግባችን አካል ማድረግ ማንም ሊነጥቀን የማይችለውን የተፈጥሮ የጤና ሀብት በቤታችን እንድናገኝ ያስችለናል።
እንደዚሁ ከየረድፉ አምስት አምስት ሣጥኖች እያስከፈትኩ ከመረመርኩ በኋላ የምርመራዬን ውጤት ለሳቡሬ ወኪል አሳየሁት። ለፊታውራሪ ኃብተዮርጊስ ጠመንጃዎቹ ዝገው የተጠረጉ አሮጌ ጠመንጃዎች እንጂ አዲስ አለመሆናቸውን፣ ጥይቶቹም ሁሉም የተበላሹ እና ጥቅም የማይሰጡ መሆናቸውን በመዘርዘር መሳሪያዎቹን እንደማልረከበው ሪፖርት ጽፌ ላኩላቸው።
©️ ኦቶባዮግራፊ የህይወቴ ታሪክ ፣ ፊታውራሪ ተክለሐዋሪያት ተክለማርያም ፤ አአዩ ፕሬስ ፣ ገጽ 208 -- 209
ታሪክን_ወደኋላ
+2
Addis Admass:
የ 50 ሺህ ብር ጉቦ የተጠየፉት ጀግና ኢትዮጵያዊ
ፊታውራሪ ተክለሐዋርያት ተክለማርያም
ፊታውራሪ ኃ/ጊዮርጊስ ዲነግዴ አስተጠርተውኝ ሙሴ ሳቡሬ የሸጠልን የመስኮብ ጠመንጃና 40 ሚሊዮን ጥይት ድሬዳዋ ስለደረሰ ወደ ድሬዳዋ ሄደክ ርክክብ እንድፈጽም ጠየቁኝ።
አቤቶ ልጅ እያሱ ግን ለዚሁ ጉዳይ እኔ እንደማላስፈልግ በመግለፅ ሌላው ሰው እንዲሄድ ቢያዙም ከተማረኩባት ሩሲያ የመጡትን መሳሪያዎች ለመመርመር የኔ መሄድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጬ በማሳመን ወደ ድሬዳዋ እንድሄድ ፈቀደለኝ።
ድሬዳዋ ደርሼ ሆቴል እንዳረፍኩ ማካልዲስ የሚባል የግሪክ ሰው የመሴ ሳቡሬ ወኪል ነኝ በማለት ወዳረፉኩበት ሆቴል መጣ። ነገ ጠዋት መሣሪያዎቹን እያወረድን መመርመር እንጀምራለን ፣ ጠዋት ጉሙሩክ እንድትመጣ ብየው ተለያየን።
ይኸው ሠው በድጋሚ ማታ ወዳረፉኩበት ሆቴል በመምጣት ልክ ብዙ ዘመን እንደሚያውቀኝ በወዳጅነት አይነት ያነጋግረኝ ጀመረ። በመጨረሻም ወጪ ይበዛቦታል በማለት ሙሴ ሳቡሬ ሃምሳ ሺህ ብር እርዳታ ስጥ ብለውኛል በማለት ገንዘቡን ሊሰጠኝ ሞከረ። በከንቱ አትድከም ፣ ምንም አያስፈልግም ፣ ይልቅስ ነገ ጠዋት እንድትመጣና ስራችንን እንድንሰራ ብዬ አሰናበትኩት።
በነጋታው በቀጠሮአቸው መሠረት ለናሙና አንድ ሣጥን ጠመንጃ እና አስር ሣጥን ያህል ጥይቶች አስከፍቼ መመርመር ጀመርኩ ጠመንጃዎቹ ዝገዋል ፣ በብርጭቆ ወረቀት እየተፈገፈገም ተቀብተዋል ጥይቶቹም ተበላሽተዋል ፣ ቀለሆቹ ተቦርቡረው ተጎድተው አረሮቹና ቀለሆቹ ተለያይተዋል ፣ ባሩዱም ከቀለሆቹ ውስጥ እየተዘረገፈ በስብሶ ነጥቶ ጨው መስሏል። ይህንን ባሩድ በእሳት እያቃጠልኩ ስመረምረው መቃጠል አይችልም።
©️
1. ‹‹ዝናህን ለመገንባት ሃያ ዓመት ይወስድብሃል፡፡ ዝናህን ለማበላሸት ግን ሃያ ደቂቃ በቂህ ነው፡፡ ይሄን ጉዳይ ካሰብክ ነገሮችን በተለያየ መንገድ ታከናውናቸዋለህ፡፡››
---ዋረን በፌት
2.‹‹ፍ/ቤት በተወሰኑ ዳኞች የተገነባ ሲሆን የዳኝነቱን ሥራ የተሻለ ጠበቃ ላለው ሰው መፍረድ ብቻ ነው::”
----ሮበርት ፍሮስት
3." የራስን ስሜት መቆጣጠር አለመቻል አቅጣጫ ጠቋሚ በሌለው መርከብ እንደመጓዝ ነው። "
----ማህተመ ጋንዲ
4."ተኩላዎች ዳኞች ሆነው በተሰየሙበት ችሎት የበጎች ቀጣይ እጣፋንታ ምን ሊሆን እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም።"
---ይዲሽ
5.‹‹ሐብታሞችን ድሃ በማድረግ ድሆችን ሃብታም ማድረግ አይቻልም፡፡››
----ዊንስተን ቸርችል
6."ሃሳባቸውን መለወጥ የማይችሉ ሰዎች፣ ምንም ነገር ሊለውጡ አይችሉም፡፡"
----ጆርጅ በርናርድ ሾው
7." ብልህ ሰው አንድ ቃል ሰምቶ ሁለት
ይረዳል።"
---አይሁዶች
8.‹‹ ብዙ ጊዜ ብቻህን መሆን ካልቻልክ ከሌሎች ጋር ያለህ ግንኙነት ሁሉ የውሸት ነው፡፡ ይሄ ብቸኝነትህን ለመሸወድ የምታደርገው እንጂ ሌላ ነገር አይደለም፡፡ ››
----ኦሾ
9.‹‹መሻሻል ማለት መለወጥ ማለት ነው፡፡ ፍፁም መሆን ማለት ደግሞ ሁልጊዜ መለወጥ ማለት ነው፡፡››
----ዊንስተን ቸርችል
10. "በዕውቀት ላይ የሚደረግ ኢንቨስትመንት የላቀ ትርፍ ያስገኛል፡፡"
----ቤንጃሚን ፍራንክሊን
11."በአቋሙ የፀና ሰው ከሆንክ አቋምህን ሊያስቀይሱ ከሚጥሩ ሰዎች ጋር ኣንገት ለአንገት ተናንቀህ የክብር ሞት ትሞታለህ፡፡በተቃራኒው አቋም የሌለው ወለዋይ ከሆንክ ደግሞ በጌቶችህ መዳፍ ሥር ወድቀህ በየቀኑ የቁም ሞት ትሞታለህ"
----ባልዛክ
12. ‹‹ጨለምተኛ ሠው በየትኛውም አጋጣሚዎቹ ችግሮች ይታዩታል፤ መልካም አሳቢ ግን በችግሮች ውስጥ መልካም አጋጣሚን ያማትራል፡፡››
----ዊንስተን ቸርችል
13. "በምስጋና የተከፈተ ዘመን አስደሳች ነው፤ በፀሎት የተከፈተ ቀን መልካም ነው፤
በእምነት የሆነ ኑሮ እረፍት ነው፤
በይቅርታ የሆነ ጓደኝነት ዘላቂ ነው፤"
---አቡነ ሺኖዳ
14. "ህልምና ምኞት በሌላቸው ሰዎች መሃል ታላቅ ከመሆን ይልቅ፣ህልምና ምኞት ባላቸው ሰዎች መሀል ደካማ መሆንን እመርጣለሁ፡፡”
--- ካህሊል ጅብራን
15. “በሕይወት ውስጥ የተለመዱ ነገሮችን
ባልተለመደ መንገድ ስታከናውን የዓለምን ቀልብ ትቆጣጠራለህ፡፡”
---ጆርጅ ዋሺንግተን
16. "መጠጥ ቤቶች እብደት በጠርሙስ
የሚሸጥባቸው ቦታዎች ናቸው"
---ሶቅራጥስ
17. በገንዘብህ የጥቅም ጓደኞችን ልታፈራ ትችላለህ በውበትህ የስሜት ጓደኞች ልታፈራ ትችላለህ በእምነትህና በስነምግባርህ ግን..
የህይወት ጓደኞችን ታፈራለህ።
---ያልታወቀ
18. "ሁላችንም የሰራናቸውን ስህተቶች ለምን እንደፈፀምናቸው በቂ ምክንያት ለመስጠት እና ለማስረዳት የምንጠቀምበት ሀይል፣ትክክለኛ ነገሮችን ለመስራት ከምናውለው መብለጡ አስገራሚ ነው፡፡"
---ካህሊል ጂብራን
19. "መፍራት ያለብህ ቀስ ብለህ ማደግህን ሳይሆን ከአለህበት ቁመህ እንዳትቀር ነዉ፡፡ተራራን ከቦታ ወደቦታ የሚያንቀሳቅሰዉ ሰዉ ትንንሽ ድንጋዮችን ያለመታከት የሚያጓጉዝ ሰዉ ነዉ፡፡"
--- ቻይናውያን
20. ‹ልምድ ንድፈሃሳብ ከሌለው እውር ነው፡፡ ነገር ግን ንድፈሃሣብ ራሱ ልምድ ከጎደለው እንደው ዝምብሎ የምሁር ጨዋታ ነው የሚሆነው፡፡››
---ኢማኑኤል ካንት
21. ‹‹ደስታ ከምክንያታዊነት ጋር የሚስማማ ሳይሆን ከምናብ ጋር የሚዋሃድ ነው፡፡››
---ኢማኑኤል ካንት
22. ‹‹ሌላ ሠው ማፍቀር የፈጣሪን ሌላኛውን ፊቱን ማየት ነው፡፡››
---ቪክቶር ሂጎ
23. "አእምሮ አስደናቂ አገልጋይ ነው ፣ ግን አስፈሪ ጌታ ነው።"
---ሮቢን ሻርማ
24. "አንድን ነገር መቼም ላላውቀው አልችልም በሚል ስሜት ተማረው፤ስታውቅ ደግሞ መቼም ላጣው እችላለሁ በሚል ስሜት አጥብቀህ ያዘው!!"
---ኮንፊሽየስ
25. "ሁለት የሞኝነት መንገድ አለ ። አንደኛው እውነት ያልሆነውን ማመን ሲሆን ሌላኛው እውነት የሆነውን አለማመን ነው ።"
----ሶረን ኪድጋርድ
26. ‹‹ሠዎች ጥንካሬ አላጠራቸውም፡፡ ያጠራቸው ፈቃድ ወይም ፍላጎት ብቻ ነው፡፡››
---ቪክቶር ሁጎ
27. "የሴቶች ዋነኛ ችግር ወንዶች ስለሴቶች የሚኖራቸውን ፅንሰ ሃሳብ አሟልተው ለመገኘት ሁልጊዜም መጣራቸው ነው።"
---ላውረንስ
28. "ከኑሮህ ለመማር የምትከፍለው ትልቁ ዋጋ ትዕግስት ነው።"
---ካቴና
ወዳጆቼ ሰሞኑን መፅሐፉን የሚዳስስልን ልጅ ባለመገኘት ፕሮግራማችን ዛሬም አይኖረንም በጣም ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን ።
አዕምሮ ታሟል የምንለዉ መቼ ነዉ ?
(በዶክተር ኃይለልዑል መኮንን - የአዕምሮ ሕክምና ስፔሻሊስት)
የአዕምሮ ጤና ማለት አንድ ግለሰብ የዕለት ተዕለት የሕይወት ጫናዎችን መቋቋም የሚችልበት ውጤታማ እና ፍሬያማ ሥራን መሥራት የሚችልበት እንዲሁም ለማህበረሰቡ አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችልበት የደህንነት ሁኔታ ነው።
የአዕምሮ ጤና ማለት የአዕምሮ ሕመም ወይም የአካል ጉዳት አለመኖር ብቻ ሳይሆን የተሟላ አካላዊ፣ አዕምሯዊ እና ማህበራዊ ደህንነት መኖር ነው።
የአእምሮ ህመም ምንድነው ?
የአእምሮ ህመም በአስተሳሰብ፣ በስሜት ወይም በባህሪ ላይ የሚከሰት የጤና መታወክ እንዲሁም ግለሰቡ በቤተሰብ፣ በስራ ወይም በማህበራዊ ህይወቱ ላይ የነበረውን የተለመደ ተግባር በብቃት እንዳያከናውን እንቅፋት ይሆንበታል።
አንድ ሰው የሚከተሉት ሶስት ዋና መስፈርቶች ሲሟሉ የአዕምሮ ህመም ተከስቷል ማለት እንችላለን።
1. የምልክቶች መኖር ፦ ከወትሮው የተለየ የአስተሳሰብ መዛባት፣ የባህሪ ለውጥ ወይም ስሜትን መቆጣጠር አለመቻል።
2. የቆይታ ጊዜ፦ እነዚህ ምልክቶች ለአጭር ጊዜ ሳይሆን ለተከታታይ ሳምንታት ወይም ወራት አብረውት ሲቆዩ።
3. የተግባር መስተጓጎል ፦ ችግሩ በግለሰቡ ስራ፣ ትምህርት፣ ማህበራዊ ግንኙነት ወይም የግል እንክብካቤ ላይ ግልጽ የሆነ መስተጓጎል ሲፈጥር የህመም ደረጃ ደርሷል እንላለን።
የአዕምሮ ህመም ልክ እንደ ደም ግፊት እና ስኳር ህመም የህክምና ድጋፍ የሚያስፈልገው ጉዳይ እንጂ የድክመት መገለጫ አይደለም። ስለዚህ ማንኛውም የአዕምሮ ጤና እክል ቀደም ብሎ በባለሙያ ቢታይ የመዳን ወይም የማገገም እድሉ ሰፊ ስለሆነ ወደ ባለሙያ በመሄድ የህክምና እርዳታ ማድረግ ተገቢ ነዉ።
#የአዕምሮ_ጤና_ግንዛቤ_ወር
Repost from ልህቀት የንባብ ባህል ማጎልበቻ ማዕከል
📚 የዕውቀት ግብዣ! 📚
ዛሬ ልዩ ምሽት ነው! ካለፈው ሳምንት የቀጠለውና ብዙዎቻችሁ በጉጉት ስትጠብቁት የነበረው ድንቅ ፕሮግራማችን እነሆ ደርሷል! ✨
"ሥነ አመክንዮ" (Logic) የተሰኘውን፣ የአስተሳሰብ አድማስን የሚያሰፋና የነገሮችን እውነታ የምንረዳበትን ጥልቅ መፅሀፍ ሳሙኤል ጋር በመሆን በዝርዝር እንዳስሳለን! 🧠💡
🔍 በዛሬው ዳሰሳችን ምን ይጠብቃችኋል?
🧐 የአመክንዮ ሚስጥሮች፡ ነገሮችን በስሜት ሳይሆን በማስረጃና በምክንያት እንዴት መተንተን እንደምንችል...
🧩 የተሳሳቱ ድምዳሜዎች፡ በዕለት ተዕለት ንግግራችንና ውሳኔያችን ውስጥ የምንሰራቸውን የስህተት ወጥመዶች እንዴት እንለይ?
🚀 ለተግባራዊ ህይወት፡ ይህ መፅሀፍ ለስራችን፣ ለግንኙነታችንና ለውሳኔ አሰጣጣችን የሚሰጠው ፋይዳ...
🗣️ የሳሙኤል ጥልቅ ትንታኔ፡ ሳሙኤል መፅሀፉን አብራርቶና አጣፍጦ ለሁላችንም በሚገባ መልኩ ያቀርብልናል!
⏰ መቼ? የት?
📅 ዛሬ ምሽት
🕒 ሰዓት፡ በትክክል ከምሽቱ 3:00 ላይ
📍 ቦታ፡ እዚሁ በቴሌግራም ቻናላችን ላይ!
አምልጦት ቢቆጩ የማይመለስ ድንቅ ዝግጅት! 🏃♂️💨 🏃♀️💨
ይህ ፕሮግራም አእምሮን የሚያድስ፣ አመለካከትን የሚቀይርና አዳዲስ ዕውቀቶችን የምንገበይበት ልዩ መድረክ ነው። የ logic (አመክንዮ) አቅም ካላችሁ፣ አለምን የምታዩበት መነፅር ይቀየራል! 🌍👓
ባለፈው ሳምንት ያልነበራችሁም ቢሆን ዛሬውኑ ተቀላቀሉን፤ ሳሙኤል ካለፈው ጋር እያያያዘ በግልፅ ያቀርብልናል! 🎤📖
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል! 🤝✨ ጓደኞቻችሁንም ጋብዙ፣ ሊንኩን ሼር አድርጉ! 🔗🔥
ከምሽቱ 3:00 ላይ እንገናኝ! 👋😊
🎯 የዕውቀት ጥማታችሁን የምታረኩበት ሰዓት አሁን ነው! 🎯
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
