uk
Feedback
Diinii kee Anaakara (Md Ali)

Diinii kee Anaakara (Md Ali)

Відкрити в Telegram

دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol

Показати більше
1 619
Підписники
+424 години
+107 днів
+2530 день
Архів дописів
Repost from Ibnu Muhammedzeyn
ብዙ ዑለሞቻችን በኩኒያ፣ቅፅል ስም(ለቀብ) እና በኒስባ(ወደ ሀገራቸው ወይንም ሙያቸው በመጠጋት) ነው የሚታወቁት በዚህም የተነሳ ብዙዎቹን ስማቸውን አናውቀውም ለማስታወስ የተወሰኑትን ከዚህ በታች ላስቀምጥላችሁ👇 1, ዙህርይ (ኢብኑ ሺሀብ): ሙሐመድ ኢብኑ ሙስሊም 2, አውዘዒይ: ዐብዱረሕማን ኢብኑ ዐምር 3, አቡ ሐኒፋ: ኑዕማን ኢብኑ ሣቢት 4, አሽ–ሻፍዒይ: ሙሐመድ ኢብኑ ኢድሪስ 5, ቡኻሪይ: ሙሐመድ ኢብኑ ኢስማዒል 6, አቡ ዳውድ: ሱለይማን ኢብኑ አሽዐሥ 7, ቲርሚዝይ: ሙሐመድ ኢብኑ ዒሳ 8, ነሳዒይ: አሕመድ ኢብኑ ሹዐይብ 9, ኢብኑ ማጀህ: ሙሐመድ ኢብኑ ተዚይድ 10, ቁርጡቢይ: ሙሐመድ ኢብኑ አሕመድ 11, በርበሀሪይ: ሐሰን ኢብኑ ዐሊይ 12, ኢብኑ ሐዝም: ዐሊይ ኢብኑ አሕመድ 13, ኢብኑል ጀውዚይ: ዐብዱረሕማን ኢብኑ ዐሊይ 14, ነወዊይ (ነዋዊይ): የሕያ ኢብኑ ሸረፍ 15, ኢብኑ ተይሚያ: አሕመድ ኢብኑ ዐብዱል ሐሊም 16, ዘሀቢይ: ሙሐመድ ኢብኑ አሕመድ 17, ኢብኑ ከሢር: ኢስማዒል ኢብኑ ዑመር 18, ኢብኑ ረጀብ: ዐብዱ ረሕማን ኢብኑ አሕመድ 19, ኢብኑ ሐጀር: አሕመድ ኢብኑ ዐሊይ 20, ሰኻዊይ: ሙሐመድ ኢብኑ ዐብዲረሕማን 21, ሲወጢይ: ዐብዱረሕማን ኢብኑ አቢበክር 22, ሶንዐኒይ: ሙሐመድ ኢብኑ ኢስማዒል 23, ሸውካኒይ: ሙሐመድ ኢብኑ ዐሊይ ሌሎችን ደግሞ ኢንሻ አላህ በሌላ ጊዜ ለመጥቀስ እሞክራለሁ ✍ወንድማችሁ/ ኢብኑ ሙሐመድዘይን ​•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈• t.me/IbnuMuhammedzeyn t.me/IbnuMuhammedzeyn

photo content

photo content

~~ ወሳኝ የጥቢ፞ ህግጋት ~~ ~~~~~ በሃገራችን ወላጆች ልጆቻቸውን ጎረቤት ወይም ጓደኛ ዘንድ ጥለው ሲሄዱ የተተወባት እናት ልጁን ማጥባት የተለመደ ነው። ነገር ግን የሚከተለው ሸሪዐዊ ህግጋት እንዳለ ስለማያውቁ ለጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት እንደማይሰጡት የሚታወቅ ነው። ይሄ ከባድ ርእስ ስለሆነ እናቶች ተገቢውን ጥንቃቄና ክትትል ሊያደርጉ ይገባል። በኢስላም ጥቢ፞ ከተራና አላፊ እለታዊ ክስተት ያለፈ ትርጉም አለው፡፡ ማለትም አጥቢና ጠቢን ያማከሉ ሰፋ ያሉ ሸሪዐዊ ህጎች ስላሉ ሙስሊሞች ተያያዥ ብይኖችን ማወቅ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህንን ከሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ውስጥ አንዱ እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ ያስተላለፈችው ሐዲሥ ነው፡፡ በዚህ ሐዲሥ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- "الرَّضَاعَةُ تُحَرِّمُ مَا تُحَرِّمُ الْوِلَادَةُ". “ጥቢ፞ መዋለድ (ከመጋባት) የሚከለክለውን ይከለክላል፡፡” [ቡኻሪ፡ 2646] [ሙስሊም፡ 1444] ስለዚህ ጥቢ፞ ከስጋዊ ዝምድና ጋር የሚጋራቸው ነገሮች አሉ ማለት ነው። እነዚህም አራት ናቸው፡- ① ጋብቻ:– በስጋ እናት ሰበብ ለመጋባት ክልክል የሆነ ሁሉ በተመሳሳይ በጥቢ፞ እናት ሰበብም ክልክል ይሆናል። ዝርዝሩ ወደፊት ይመጣል። ② እይታ (ነዞር):– በስጋ እናት ሰበብ መመልከት የሚፈቀድ ሁሉ በተመሳሳይ በጥቢ፞ እናት ሰበብም የተፈቀደ ይሆናል። ስለዚህ እናቱን፣ እህቱን፣ አክስቱን፣… ማየት፣ መጨበጥ፣ መሳም እንደሚፈቀደው ሁሉ በጥቢ፞ ሰበብ ተመሳሳይ ብይን የሚይዙንም መመልከት፣ በሰላምታ መጨበጥና መሳም ይፈቀዳል። ③ ተገልሎ መቆየት:– እንደሚታወቀው ከአጅነቢያ ሴት ጋር ከሰው እይታ ተገልሎ መቀመጥ አይፈቀድም። ነገር ግን ከስጋ እናት፣ እህት፣… ጋር ተገልሎ መቀመጥ እንደማይከለከለው ከጥቢ፞ እናት፣ እህት፣ አክስትም፣… ጋርም ተገልሎ መቀመጥ አይከለከልም። ④ መሕረምነት:– አንድ ወንድ ለወላጅ እናቱ፣ ለእህቱ፣ ለአክስቱ፣… በጉዞ ላይ መሕረም እንደሚሆነው ሁሉ ለጥቢ፞ እናቱ፣ እህቱ፣ አክስቱም መሕረም መሆን ይችላል። • መጠነኛ ትንታኔ ~ 1. አንድ ሰው ልጅ እያለ አንዲት ወላጅ እናቱ ያልሆነች ሴት ብታጠባው ያቺ አጥቢ እንደ እናቱ ትታሰባለች፡፡ ሴቶች ልጆቿ እንደ እህቶቹ፣ ወላጆቿ እንደ አያቶቹ፣ እህቶቿ እንደ የሹሜዎቹ፣ ስታጠባው ጊዜ ያለው ባሏ እንደ አባቱ፣ የባሏ ወላጆች እንደ አያቶቹ፣ የባሏ እህቶች እንደ አክስቶቹ፣ የባሏ ሌሎች ሚስቶች እንደ አባቱ ሚስቶች፣ ባሏ ከሌላ ሚስት የወለዳቸው ልጆች ልክ እንደ እህትና ወንድሞቹ ይቆጠራሉ፡፡ የጠባችው ሴት ከሆነችም ተመሳሳይ ንፅፅር እንሰራለን፡፡ ባጭሩ የአጥቢዋ ወንዶች ልጆች ለጠቢዋ ወንድሞቿ፣ የአጥቢዋ ወንድሞች ለጠቢዋ አጎቶች፣ … ይሆናሉ፡፡ አጅነቢዮች አይሆኑም። 2. ልክ በመዋለድ (በስጋዊ ዝምድና) የተነሳ ለማግባት እንደማትፈቀድ ሴት፣ በጥቢ፞ የሷን ብይን የምትይዝን ሴትም (ለምሳሌ የጥቢ፞ እህት፣ የጥቢ፞ እናት፣ የጥቢ፞ አክስት፣ የጥቢ፞ የሹሜ፣ …) አንድ ወንድ ሊያገባ አይፈቀድለትም፡፡ ጋብቻ ተፈፅሞ ከሆነም መለያየት ግዴታ ነው፡፡ ማሳሰቢያ፡- ~ 1. ዋጋ የሚኖረው ጥቢ፞ በሁለት አመት የህፃንነት እድሜ ክልል ውስጥ የተጠባ ጥቢ፞ ከሆነ ነው። [አልበቀራ: 233] ከሁለት አመት እድሜ በላይ እያለ የተፈፀመ ጥቢ፞ ከቁምነገር አይቆጠርም። 2· ጥቢ፞ው አምስት ጊዜና ከዚያ በላይ የጠባ ከሆነ ነው፡፡ [ሙስሊም: 1452] አንድ ጊዜ ጡቱን ከያዘ በኋላ ለመተንፈስ፣ ውሃ ለመጠጣት፣ ወደሌላኛው ጡት ለመቀየር የሚኖረው ቆይታ ተፅእኖ የለውም። ረጅም ጊዜ ካልኖረ በስተቀር እንደ አንድ ነው የሚቆጠረው። ይሄ አንድ ተብሎ በዚህ መልኩ አምስት ጊዜ ከተጠባ የጥቢ፞ ህግጋት ታሳቢ ይሆናሉ። ከአምስት ጊዜ ያነሰ ጥቢ፞ ከግምት አይገባም፡፡ 3. የጥቢ፞ ህግጋት የሚመለከተው የጠባውን አካል ብቻ እንጂ ያልጠቡ የስጋ ወንድሞቹንና እህቶቹን አይደለም፡፡ ማለትም የጠባው አካል ከጠባበት ቤት ቤተሰብ ይሆናል፡፡ እንጂ የሱ የስጋ ቤተሰቦች በሱ መጥባት የተነሳ ለጥቢ፞ እናቱ ቤተሰብ አይሆኑም፡፡ ምሳሌ፡- ፋጢማ ሙሐመድን ብታጠባ እሷ ለሱ እናቱ ነች፡፡ ልጆቿም እህቶቹና ወንድሞቹ ናቸው፡፡ ሴቶች ልጆቿን እህቶቹ ስለሆኑ ሊያገባ አይፈቀድለትም፡፡ ነገር ግን ህጉ እሱን እንጂ የስጋ ወንድምና እህቶቹን አይመለከትም፡፡ ምክንያቱም የፋጢማ እናትነት ለሱ እንጂ ለነሱ አይደለምና፡፡ 4. የጥቢ፞ ህግ እስከ መዋረስ፣ ቀለብ መስፈር፣ ለጋብቻ ሃላፊ (ወሊይ) መሆን አይደርስም፡፡ ማለትም ለምሳሌ በጥቢ፞ የተነሳ እናቱ ወይም አባቱ የሆነ ሰው ስለሞተ ንብረት መውረስ አይችልም፡፡ ለጥቢ፞ እህቱ የጋብቻ ወሊይ መሆን አይችልም። ለወላጅ እናቱ ቀለብ የመስፈር ግዴታ ስላለበት ዘካ መስጠት አይፈቀድለትም፡፡ ለጥቢ፞ እናቱ ግን ቀለብ ግዴታ ስላልሆነበት ዘካ መስጠት ይችላል፡፡ 5. ጥቢ፞ ተከስቷል ወይስ አልተከሰተም በሚለው ላይ ጥርጣሬ ካለ መነሻ የሚሆነን ጥቢ፞ውን እንደሌለ መቁጠር ነው፡፡ በጥርጣሬ ላይ ተመርኩዘን የጥቢ፞ን ህግጋት አንተገብርም፡፡ የጥቢ፞ው መጠን ላይ ከተጠራጠርንም እርግጠኛ የሆንበትን ማለትም ዝቅተኛውን እንወስዳለን፡፡ [አልሙግኒ፣ ኢብኑ ቁዳማ: 7/537] 6· በጥቢ፞ ጉዳይ ታማኝ ከሆነች የአንዲት ሴት ምስክርነት ብቻውን በቂ ነው። ለምሳሌ አንዲት ሴት ቀርባ "ሁለቱንም አጥብቻቸዋለሁ" ካለች ምስክርነቷ ተቀባይነት አለው። ተጋብተው ከሆነ ይለያያሉ። [ቡኻሪ: 2659] 7· የተብራራ ያልሆነ ድፍን ምስክርነት ተቀባይነት የለውም። ስለዚህ የጥቢ፞ውን ዘመንና ቁጥር በተጨባጭ መግለፅ ያስፈልጋል። ይሄ ባልሆነበት የጥቢ፞ን ህግጋት አንተገብርም። [አልሙግኒ፣ ኢብኑ ቁዳማ: 7/537] አዋቂው አላ፞ህ ነው። (ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 17/1441) (ህዳር 04/2012) የቴሌግራም ቻናል:- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

photo content

photo content

Qafar qunxaaneytaw ama maysaxxagat gaba essegella. Wagita barittoo kee abak raag kakle maraw.

Repost from Fanajobs
✅ IPDC Job Vacancy 🔻Total Vacancy: 11 Closing Date: June 13, 2022
✅ IPDC Job Vacancy 🔻Total Vacancy: 11 Closing Date: June 13, 2022

photo content

እኛ እንዳያልፍብን

የሸይጧን ተንኮሎችና መፍትሔዎቻቸው በሸይኽ ኢልያስ አህመድ || NesihaTv https://youtu.be/BuVCj9yToA4 ነሲሓ ቲቪ... ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም!! @nesihatv

«ያልተጻፈው ህግና የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ----- አፈንዲ ሙተቂ ------ ህንድ ሴኩላር ሪፐብሊክ ናት። BJP የሚባለው የአሁኑ ፓርቲ በህዝቦቿ መካከል ያለውን Cohesion ድብልቅልቁን ከማውጣቱ በፊት እጅግ የሚያመረቃ ዲሞክራሲ ነበራት። ሂንዱና ሙስሊሙ፣ ጄኑ እና ሲኩ ተከባብሮ ይኖርባት ነበር። ኢትዮጵያም ሴኩላር ሪፐብሊክ ናት ይባላል። ፌዴራላዊ ህገ-መንግሥትም አላት ይባላል። ነገር ግን የኢትዮጵያ ሴኩላሪዝም ከጀርባው ባለ ሌላ ያልተጻፈ ህግ የሚታጀብ ነው። እስቲ ነገሩን በንጽጽር እንየው። ----- ከህንድ ህዝብ መካከል የሙስሊሞቹ ብዛት 15% ያህል ነው። እንዲህም ሆኖ እስከ ዛሬ ድረስ አራት ህንዳዊያን ሙስሊሞች የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ተመርጠዋል። እነርሱም የሚከተሉት ናቸው። ዛኪር ሑሴን ኻን (1967-1968) ሙሐመድ ሂዳያቱላህ (1968-1969) ፈኽሩዲን ዓሊ አሕመድ (1974- 1977) አብዱል-ከላም (2002-2007) እርግጥ በሀገረ ህንድ "ፕሬዚዳንት" ተብሎ የሚመረጠው ሰው ያለው ስልጣን ceremonial ነው። ነገር ግን የህንድ ህዝቦች ሁሉ ርእሰ ብሄር ሆኖ የሚሰየም በመሆኑ symbolic significance አለው። ------- የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ብዛት ከጠቅላላው ህዝብ 46% ያህል ነው (Encarta Encylopedia 2009 ተመልከቱ)። እንዲህም ሆኖ ግን ceremonial ስልጣን ብቻ ባለው በዚህ ስፍራ ላይ ሙስሊም የሆነ ሰው እንዳይመረጥ ባልተጻፈው የኢትዮጵያ ህግ ገደብ ተጥሏል። ይህንንም በተጨባጭ ምሳሌ ላያሳያችሁ። በ1987 መግቢይ ላይ ኢህአዴግ ታዋቂውን ምሁር ፕሮፌሰር ጀማል አብዱልቃዲርን ለፕሬዚዳንትነት እጩ አድርጎ ነበር። ይሁንና ያልተጻፈው የኢትዮጵያ ህግ አቀንቃኝ የነበሩት የያኔው ፓትሪያርክ አባ ጳውሎስ እና ሌሎች ግለሰቦች "እንዴት ብሎ ነው እስላም የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሆኖ የሚመረጠው?" በማለት ተቃውሞ አሰሙ። አቶ መለስ ዜናዊ "የአሁኑ ፕሬዚዳንት ceremonial ነው። executive አይደለም። የኢትዮጵያ ሙስሊም ህዝብ በቁጥር ብዙ በመሆኑ ፕሬዚዳንቱን ከሙስሊሞች ብንመርጥ ህብረ-ብሄራዊነትን ያሳይልናል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደግሞ ከክርስቲያን ይሆናል" በማለት ሊያሳምናቸው ቢሞክርም አልቻለም። የምዕራቡ ሀገር ዲፕሎማቶችም ከፓትሪያርኩ ጋር ወግነው ተከራክረው መለስ ሃሳቡን እንዲቀለብስ አድርገውታል። በዚያ ወቅት ወሬው ሾልኮ የደረሳቸው የግል ጋዜጦች ደግሞ "ስምንተኛው ሺህ ደርሷል። እስላም የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሊሆን ነው። ይህ አክራሪ እስልምናን በኢትዮጵያ ለማስፋፋት የተሸረበ ትልቅ ትል ሴራ ነው" እያሉ በጥላቻ መንፈስ ብዙ ጻፉ። በዚህም ምክንያት ሙስሊሙ ፕሮፌሰር ጀማል ሳይመረጡ ቀሩና ክርስቲያኑ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ፕሬዚዳንት ሆኑ (በነገራችን ላይ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ "ዳንዲ" በተሰኘው ግለ-ታሪካቸው ይህንን እውነት በድፍረት ተናግረውታል። እናመሰግናቸዋለን)። ------ አሁንስ ያልተጻፈው የኢትዮጵያ ህግ መስራቱን አቋርጧል? ተባብሶ ነው የቀጠለው እንጂ የተቋረጠ ነገር የለም። ያልተጻፈው ህግ ከመንግሥት ስልጣን አልፎ የሙስሊሙ ህዝብ የግል ንብረት በሆነው "መጅሊስ አል-አዕላ" ድረስ እየገባ ሲበጠብጠን እያየነው ነው። ፈጣሪ ፈረጃውን ያምጣው አቦ! --- (ሀብታሙ አያሌ እና ዘመድኩን በቀለ ሳምንቱን በሙሉ የሚፈተፍቱበትን አጀንዳ ሰጠኋቸው አይደል? ጎበዝ ነኝ። ሆኖም የጻፍኩት ሁሉ ከውሃ የጠራ እውነት መሆኑን እወቁት)። --------- አፈንዲ ሙተቂ ግንቦት 29/2014»

ብሄርተኝነት ጣኦት ነው! ~~ * የሃይማኖት አጥር የማይከበረበት፣ * ሙስሊም ወገን የሚታረድበት፣ ንብረቱ የሚነጠቅበት፣ የሚቃጠልበት፣ * "ሃይማኖት አይከፋፍለንም" እያሉ የሚሰበክበት፣ * ጣኦታዊ በአላት የሚታደሙበት፣ አማራነት፣ ኦሮሞነት፣ ትግሬነት፣ አፋርነት፣ ... ወሎየነት፣ ጎንደሬነት፣ ሀረሪነት፣ ወለጋነት፣ ... ጣዖት ነው። * {እሷ የሸህ ልጅ ናት እኔ የመምሬ ምን ያስጨንቀኛል ወሎ ተፈጥሬ} የምትዘፍንበት ወሎየነት ቆሻሻ ነው። * የእምነት የለሾች ውጤት በሆነችው ሉሲ ላይ ተመርኩዞ "አፋር የሰው ዘር መገኛ" እያሉ በክህደት እንዲጀነኑ የሚያደርግ ብሄርተኝነት ገዳይ ነው። * ታቦት እስከሚሸኙ፣ መስቀል እስከሚጣዱ፣ ገና እስከሚያደምቁ፣ ... የደረሰ የአማራ ብሄርተኝነት ነቀርሳ ነው። * ኢሬቻ እስከሚካፈሉ፣ ሙስሊም ወገኖች ዘራቸው እየታየ እስከሚጠቁ፣ ... የደረሰ የኦሮሞ ብሄርተኝነት አጥፊ ነው። ጥፋት በማንም ቢፈፀም ጥፋት ነው። በዘርና በቋንቋ በሚመስሉህ ሰዎች ስለተፈፀመ ወግነህ አትከራከር። ወገኔ ሆይ! ከምንም በላይ ኢስላምህን አስቀድም። ያንተ ዘር ከዐረብ አይበልጥም። ዐረብ እንኳ አላህን መፍራት ከሌለው በስተቀር በሌላው ላይ ብልጫ የለውም። ዘርህ ከመተዋወቂያነት ባለፈ ስሙኒ ታክል ዋጋ የለውም። ስለዚህ አትኮፈስ፣ አትሸማቀቅ። ዘርን መሰረት አድርገህ በጅምላ አትውድድ፣ በጅምላ አትጥላ። ሁሌም አኺራህን አስቀድም። በቃልም በፅሁፍም የዘር ጥላቻ እንዳትቀስቅስ ተጠንቀቅ። ጊዜው የሰው ህይወት የረከሰበት ጊዜ ነው። በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እጅህ ላይ የሰው ደም እንዳይኖር ፍራ። = የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor

ይድረስ ለዓብዱላሂ አልሃረሪ ተማሪዎች 1 ጥያቄና 10 መልሶቹ! ------------ "ከዓርሽ በላይ ነው ካላችሁ ዓርሽን ከመፍጠሩ በፊት የት ነበር?" ለሚለው የአህባሾች ጥያቄ በ 10 መንገዶች ምላሽ የተሰጠበት ድንቅ ፅሁፍ https://youtu.be/3p54yo_wxSQ 👍ዝግጅት ሸይኽ ኢልያስ አህመድ © ቅንብር ሁዳ መልቲሚዲያ @ustazilyas

خطبة الجمعة لفضيلة الشيخ الدكتور محمد حسين ويعسا تابعنوان: الكفر على النعمة سبب زوال النعمة التاريخ 28 ربيع الآخر 1443ه‍ الجامع: نعمة المنان بمدينة لوغيا في إقليم العفر إثيوبيا Khutba Maqaanel Yalla faatite waanam kaadu Teetil kaa Cinaanam Maqaane Edde katta sababa

+5
أصول التفسير الدرس الحاد عشر.m4a25.20 MB

الدرس الرابع العقيدة الواسطية .aac23.70 MB

+1
أصول التفسير الدرس الثاني .amr2.31 MB