Diinii kee Anaakara (Md Ali)
Відкрити в Telegram
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
Показати більше1 619
Підписники
+424 години
+107 днів
+2530 день
Архів дописів
Repost from Ibnu Muhammedzeyn
ብዙ ዑለሞቻችን በኩኒያ፣ቅፅል ስም(ለቀብ) እና በኒስባ(ወደ ሀገራቸው ወይንም ሙያቸው በመጠጋት) ነው የሚታወቁት በዚህም የተነሳ ብዙዎቹን ስማቸውን አናውቀውም ለማስታወስ የተወሰኑትን ከዚህ በታች ላስቀምጥላችሁ👇
1, ዙህርይ (ኢብኑ ሺሀብ): ሙሐመድ ኢብኑ ሙስሊም
2, አውዘዒይ: ዐብዱረሕማን ኢብኑ ዐምር
3, አቡ ሐኒፋ: ኑዕማን ኢብኑ ሣቢት
4, አሽ–ሻፍዒይ: ሙሐመድ ኢብኑ ኢድሪስ
5, ቡኻሪይ: ሙሐመድ ኢብኑ ኢስማዒል
6, አቡ ዳውድ: ሱለይማን ኢብኑ አሽዐሥ
7, ቲርሚዝይ: ሙሐመድ ኢብኑ ዒሳ
8, ነሳዒይ: አሕመድ ኢብኑ ሹዐይብ
9, ኢብኑ ማጀህ: ሙሐመድ ኢብኑ ተዚይድ
10, ቁርጡቢይ: ሙሐመድ ኢብኑ አሕመድ
11, በርበሀሪይ: ሐሰን ኢብኑ ዐሊይ
12, ኢብኑ ሐዝም: ዐሊይ ኢብኑ አሕመድ
13, ኢብኑል ጀውዚይ: ዐብዱረሕማን ኢብኑ ዐሊይ
14, ነወዊይ (ነዋዊይ): የሕያ ኢብኑ ሸረፍ
15, ኢብኑ ተይሚያ: አሕመድ ኢብኑ ዐብዱል ሐሊም
16, ዘሀቢይ: ሙሐመድ ኢብኑ አሕመድ
17, ኢብኑ ከሢር: ኢስማዒል ኢብኑ ዑመር
18, ኢብኑ ረጀብ: ዐብዱ ረሕማን ኢብኑ አሕመድ
19, ኢብኑ ሐጀር: አሕመድ ኢብኑ ዐሊይ
20, ሰኻዊይ: ሙሐመድ ኢብኑ ዐብዲረሕማን
21, ሲወጢይ: ዐብዱረሕማን ኢብኑ አቢበክር
22, ሶንዐኒይ: ሙሐመድ ኢብኑ ኢስማዒል
23, ሸውካኒይ: ሙሐመድ ኢብኑ ዐሊይ
ሌሎችን ደግሞ ኢንሻ አላህ በሌላ ጊዜ ለመጥቀስ እሞክራለሁ
✍ወንድማችሁ/ ኢብኑ ሙሐመድዘይን
•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈•
t.me/IbnuMuhammedzeyn
t.me/IbnuMuhammedzeyn
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Qafar qunxaaneytaw ama maysaxxagat gaba essegella.
Wagita barittoo kee abak raag kakle maraw.
Repost from NESIHA TV | ነሲሓ ቲቪ
የሸይጧን ተንኮሎችና መፍትሔዎቻቸው በሸይኽ ኢልያስ አህመድ || NesihaTv
https://youtu.be/BuVCj9yToA4
ነሲሓ ቲቪ...
ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም!!
@nesihatv
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
«ያልተጻፈው ህግና የኢትዮጵያ ሙስሊሞች
-----
አፈንዲ ሙተቂ
------
ህንድ ሴኩላር ሪፐብሊክ ናት። BJP የሚባለው የአሁኑ ፓርቲ በህዝቦቿ መካከል ያለውን Cohesion ድብልቅልቁን ከማውጣቱ በፊት እጅግ የሚያመረቃ ዲሞክራሲ ነበራት። ሂንዱና ሙስሊሙ፣ ጄኑ እና ሲኩ ተከባብሮ ይኖርባት ነበር።
ኢትዮጵያም ሴኩላር ሪፐብሊክ ናት ይባላል። ፌዴራላዊ ህገ-መንግሥትም አላት ይባላል። ነገር ግን የኢትዮጵያ ሴኩላሪዝም ከጀርባው ባለ ሌላ ያልተጻፈ ህግ የሚታጀብ ነው። እስቲ ነገሩን በንጽጽር እንየው።
-----
ከህንድ ህዝብ መካከል የሙስሊሞቹ ብዛት 15% ያህል ነው። እንዲህም ሆኖ እስከ ዛሬ ድረስ አራት ህንዳዊያን ሙስሊሞች የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ተመርጠዋል። እነርሱም የሚከተሉት ናቸው።
ዛኪር ሑሴን ኻን (1967-1968)
ሙሐመድ ሂዳያቱላህ (1968-1969)
ፈኽሩዲን ዓሊ አሕመድ (1974- 1977)
አብዱል-ከላም (2002-2007)
እርግጥ በሀገረ ህንድ "ፕሬዚዳንት" ተብሎ የሚመረጠው ሰው ያለው ስልጣን ceremonial ነው። ነገር ግን የህንድ ህዝቦች ሁሉ ርእሰ ብሄር ሆኖ የሚሰየም በመሆኑ symbolic significance አለው።
-------
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ብዛት ከጠቅላላው ህዝብ 46% ያህል ነው (Encarta Encylopedia 2009 ተመልከቱ)። እንዲህም ሆኖ ግን ceremonial ስልጣን ብቻ ባለው በዚህ ስፍራ ላይ ሙስሊም የሆነ ሰው እንዳይመረጥ ባልተጻፈው የኢትዮጵያ ህግ ገደብ ተጥሏል። ይህንንም በተጨባጭ ምሳሌ ላያሳያችሁ።
በ1987 መግቢይ ላይ ኢህአዴግ ታዋቂውን ምሁር ፕሮፌሰር ጀማል አብዱልቃዲርን ለፕሬዚዳንትነት እጩ አድርጎ ነበር። ይሁንና ያልተጻፈው የኢትዮጵያ ህግ አቀንቃኝ የነበሩት የያኔው ፓትሪያርክ አባ ጳውሎስ እና ሌሎች ግለሰቦች "እንዴት ብሎ ነው እስላም የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሆኖ የሚመረጠው?" በማለት ተቃውሞ አሰሙ። አቶ መለስ ዜናዊ "የአሁኑ ፕሬዚዳንት ceremonial ነው። executive አይደለም። የኢትዮጵያ ሙስሊም ህዝብ በቁጥር ብዙ በመሆኑ ፕሬዚዳንቱን ከሙስሊሞች ብንመርጥ ህብረ-ብሄራዊነትን ያሳይልናል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደግሞ ከክርስቲያን ይሆናል" በማለት ሊያሳምናቸው ቢሞክርም አልቻለም። የምዕራቡ ሀገር ዲፕሎማቶችም ከፓትሪያርኩ ጋር ወግነው ተከራክረው መለስ ሃሳቡን እንዲቀለብስ አድርገውታል።
በዚያ ወቅት ወሬው ሾልኮ የደረሳቸው የግል ጋዜጦች ደግሞ "ስምንተኛው ሺህ ደርሷል። እስላም የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሊሆን ነው። ይህ አክራሪ እስልምናን በኢትዮጵያ ለማስፋፋት የተሸረበ ትልቅ ትል ሴራ ነው" እያሉ በጥላቻ መንፈስ ብዙ ጻፉ። በዚህም ምክንያት ሙስሊሙ ፕሮፌሰር ጀማል ሳይመረጡ ቀሩና ክርስቲያኑ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ፕሬዚዳንት ሆኑ (በነገራችን ላይ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ "ዳንዲ" በተሰኘው ግለ-ታሪካቸው ይህንን እውነት በድፍረት ተናግረውታል። እናመሰግናቸዋለን)።
------
አሁንስ ያልተጻፈው የኢትዮጵያ ህግ መስራቱን አቋርጧል? ተባብሶ ነው የቀጠለው እንጂ የተቋረጠ ነገር የለም። ያልተጻፈው ህግ ከመንግሥት ስልጣን አልፎ የሙስሊሙ ህዝብ የግል ንብረት በሆነው "መጅሊስ አል-አዕላ" ድረስ እየገባ ሲበጠብጠን እያየነው ነው። ፈጣሪ ፈረጃውን ያምጣው አቦ!
---
(ሀብታሙ አያሌ እና ዘመድኩን በቀለ ሳምንቱን በሙሉ የሚፈተፍቱበትን አጀንዳ ሰጠኋቸው አይደል? ጎበዝ ነኝ። ሆኖም የጻፍኩት ሁሉ ከውሃ የጠራ እውነት መሆኑን እወቁት)።
---------
አፈንዲ ሙተቂ
ግንቦት 29/2014»
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ብሄርተኝነት ጣኦት ነው!
~~
* የሃይማኖት አጥር የማይከበረበት፣
* ሙስሊም ወገን የሚታረድበት፣ ንብረቱ የሚነጠቅበት፣ የሚቃጠልበት፣
* "ሃይማኖት አይከፋፍለንም" እያሉ የሚሰበክበት፣
* ጣኦታዊ በአላት የሚታደሙበት፣
አማራነት፣ ኦሮሞነት፣ ትግሬነት፣ አፋርነት፣ ... ወሎየነት፣ ጎንደሬነት፣ ሀረሪነት፣ ወለጋነት፣ ... ጣዖት ነው።
* {እሷ የሸህ ልጅ ናት እኔ የመምሬ
ምን ያስጨንቀኛል ወሎ ተፈጥሬ}
የምትዘፍንበት ወሎየነት ቆሻሻ ነው።
* የእምነት የለሾች ውጤት በሆነችው ሉሲ ላይ ተመርኩዞ "አፋር የሰው ዘር መገኛ" እያሉ በክህደት እንዲጀነኑ የሚያደርግ ብሄርተኝነት ገዳይ ነው።
* ታቦት እስከሚሸኙ፣ መስቀል እስከሚጣዱ፣ ገና እስከሚያደምቁ፣ ... የደረሰ የአማራ ብሄርተኝነት ነቀርሳ ነው።
* ኢሬቻ እስከሚካፈሉ፣ ሙስሊም ወገኖች ዘራቸው እየታየ እስከሚጠቁ፣ ... የደረሰ የኦሮሞ ብሄርተኝነት አጥፊ ነው።
ጥፋት በማንም ቢፈፀም ጥፋት ነው። በዘርና በቋንቋ በሚመስሉህ ሰዎች ስለተፈፀመ ወግነህ አትከራከር።
ወገኔ ሆይ! ከምንም በላይ ኢስላምህን አስቀድም። ያንተ ዘር ከዐረብ አይበልጥም። ዐረብ እንኳ አላህን መፍራት ከሌለው በስተቀር በሌላው ላይ ብልጫ የለውም። ዘርህ ከመተዋወቂያነት ባለፈ ስሙኒ ታክል ዋጋ የለውም። ስለዚህ አትኮፈስ፣ አትሸማቀቅ። ዘርን መሰረት አድርገህ በጅምላ አትውድድ፣ በጅምላ አትጥላ።
ሁሌም አኺራህን አስቀድም። በቃልም በፅሁፍም የዘር ጥላቻ እንዳትቀስቅስ ተጠንቀቅ። ጊዜው የሰው ህይወት የረከሰበት ጊዜ ነው። በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እጅህ ላይ የሰው ደም እንዳይኖር ፍራ።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from የኡስታዝ ኢልያስ አሕመድ የትምህርት መድረክ (official)
ይድረስ ለዓብዱላሂ አልሃረሪ ተማሪዎች
1 ጥያቄና 10 መልሶቹ!
------------
"ከዓርሽ በላይ ነው ካላችሁ ዓርሽን ከመፍጠሩ በፊት የት ነበር?"
ለሚለው የአህባሾች ጥያቄ በ 10 መንገዶች ምላሽ የተሰጠበት ድንቅ ፅሁፍ
https://youtu.be/3p54yo_wxSQ
👍ዝግጅት ሸይኽ ኢልያስ አህመድ
© ቅንብር ሁዳ መልቲሚዲያ
@ustazilyas
خطبة الجمعة لفضيلة الشيخ الدكتور محمد حسين ويعسا
تابعنوان: الكفر على النعمة سبب زوال النعمة
التاريخ 28 ربيع الآخر 1443ه
الجامع: نعمة المنان بمدينة لوغيا في إقليم العفر إثيوبيا
Khutba
Maqaanel Yalla faatite waanam kaadu Teetil kaa Cinaanam Maqaane Edde katta sababa
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
