uk
Feedback
HOP Ministry

HOP Ministry

Відкрити в Telegram

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.

Показати більше
Країна не вказанаКатегорія не вказана
446
Підписники
+124 години
+197 днів
+6730 день
Архів дописів
መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁹⁷ አቤቱ፤ ሕግህን ምንኛ ወደድሁ! ቀኑን ሙሉ አሰላስለዋለሁ። ⁹⁸ ትእዛዛትህ ምንጊዜም ስለማይለዩኝ፣ ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረጉኝ። ⁹⁹ ምስክርነትህን አሰላስላለሁና፣ ከአስተማሪዎቼ ሁሉ የላቀ አስተዋይ ልብ አገኘሁ። ¹⁰⁰ መመሪያህን ተከትዬ እሄዳለሁና፣ ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋይ ሆንሁ። ¹⁰¹ ቃልህን እጠብቅ ዘንድ፣ እግሬን ከክፉ መንገድ ሁሉ ከለከልሁ። ¹⁰² አንተው ራስህ አስተምረኸኛልና፣ ከድንጋጌህ ዘወር አላልሁም። ¹⁰³ ቃልህ ለምላሴ ምንኛ ጣፋጭ ነው! ለአፌም ከማር ወለላ ይልቅ ጣዕም አለው። ¹⁰⁴ ከመመሪያህ ማስተዋልን አገኘሁ፤ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ሁሉ ጠላሁ።

#በማረፍ_ማትረፍ_መትረፍ! በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ከሚገጥሙ ፈተናዎች የተነሳ ችግረኛው (መፍትሄ ፈላጊው) ፍቱን መድኃኒት፣ መፍትሄ ፍለጋ የማይዞርበት፣ የመፍትሄ መገኛ ከመሰለው የማይቆምበት ፌርማታ አይኖርም። ይህንን ሁሉ ነገር አድርጎ ሲያበቃ የዞረው ዙረት፣ የፈለገው ፍለጋ ከመፍትሄው ጋር ካላገናኘው ተስፋ በቆረጠ ልብ #ያልዞርኹበት_የለም ሲል እልኽ አስጨራሽ፤ ነገር ግን ፍሬአልባ ጥረቱን ይመሰክራል። መንፈሳዊ ተሃድሶን፣ የሕይወት ለውጥን ለማምጣት የምንዞርበት ብዙ ስፍራ ቢኖረን የዞርንበት ሁሉ ወደ መድኃኒታችን ላያስጠጋን ይችላል። #አንድ_ነገር ግን ብቸኛና ፍቱን መድኃኒት፣ ከዙረት የሚገላግል የመሰሪያና የፈውስ ቦታ ነው። ዓለም በመዞርና፣ እግር እስኪቀጥን መድኃኒትና መፍትሄ ፍለጋ በመሄድ መፍትሄ ይገኛል ብላ ስታስተምር፤ እግዚአብሔር ግን በመመለስና በማረፍ መዳን እንዳለ፤ በጸጥታና በመታመን ኃይል እንደሚሆንልን፣ እንደምንበረታ ይነግረናል። ታዲያ የእኛ የአሁናዊ ሁኔታ እውነት ለማረፍ የተመቸ፣ ጸጥታን የወደደ፣ ለመመለስ የቆረጠ፣ ይሄ ሁሉ ይቅርና ለመዳን እንኳ መመለስ፣ ማረፍ፣ ጸጥታ፣ መታመን ቁልፍ እንደሆነ ያውቃል፣ ያምናል? አይመስለኝም! የበላን ሌላ ቦታ የምናከው ሌላ፤ መዳኛችን የተሰወረበት ስፍራና ለፍለጋ ስንዞር የምንውልበት ስፍራ ለየቅል፤ ሕመማችን ሌላ፣ መድኃኒት ብለን የምናግበሰብሰው ነገር ሌላ! ስንዞር የዋልንበት ስፍራ ሳይሆን፤ በማስተዋል ዘወር ብለን ብናየው፣ ወደ እርሱ መለስ ብንል፣ ብናርፍ፣ ጸጥ ብለን ልንሰማው ብንወድ፣ ብንታመነው፦ የቅርብ ሆኖ፣ እንደ ወገግታም ተገልጦ የምናገኘው እግዚአብሔር ዛሬም #የሚያስተውል፣ #እግዚአብሔርን_የሚፈልግ_መኖሩን_ለማየት_ከሰማይ_ወደ_ሰው_ልጆች_ይመለከታል። ወደ እርሱ ለመመለስ፣ እርሱን ለመመልከት፣ ለማረፍ፣ ጸጥ ለማለት፣በእርሱ ለመታመን፣ ለመዳን ዝግጁ ነን? ከሆንን ያን ጊዜ እውነተኛ ፈውስ ይሆንልናል፣ ኃይል ገንዘባችን ይሆናል፤ እንበረታለን። መመለስ፣ ማረፍ፣ ጸጥ ማለት፣ መታመን፣ መዳን፣መበርታት ይሁንልን!! ጸጋ ይብዛልን!!

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸⁹ እግዚአብሔር ሆይ፤ ቃልህ በሰማይ፣ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል። ⁹⁰ ታማኝነትህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ሁሉ ይኖራል፤ ምድርን መሠረትሃት፤ እርሷም ጸንታ ትኖራለች። ⁹¹ ሁሉም አገልጋይህ ነውና፣ በሕግህ መሠረት እስከ ዛሬ ድረስ ጸንተው ይኖራሉ። ⁹² ሕግህ ደስታዬ ባይሆን ኖሮ፣ በመከራዬ ወቅት በጠፋሁ ነበር። ⁹³ በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና፣ ትእዛዝህን ከቶ አልረሳም። ⁹⁴ እኔ የአንተ ነኝ፤ እባክህ አድነኝ፤ ሕግህንም ፈልጌአለሁና። ⁹⁵ ክፉዎች ሊያጠፉኝ አድብተዋል፤ እኔ ግን ምስክርነትህን አሰላስላለሁ። ⁹⁶ ለፍጹምነት ሁሉ ዳርቻ እንዳለው አየሁ፤ ትእዛዝህ ግን እጅግ ሰፊ ነው።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸¹ ነፍሴ ማዳንህን እጅግ ናፈቀች፤ ቃልህንም ተስፋ አደርጋለሁ። ⁸² “መቼ ታጽናናኛለህ?” እያልሁ፣ ዐይኖቼ ቃልህን በመጠባበቅ ደከሙ። ⁸³ ጢስ የጠጣ የወይን አቍማዳ ብመስልም፣ ሥርዐትህን አልረሳሁም። ⁸⁴ የባሪያህ ዕድሜ ስንት ቢሆን ነው? ታዲያ፣ በሚያሳድዱኝ ላይ የምትፈርደው መቼ ይሆን? ⁸⁵ በሕግህ መሠረት የማይሄዱ፣ እብሪተኞች ማጥመጃ ጒድጓድ ቈፈሩልኝ። ⁸⁶ ትእዛዛትህ ሁሉ አስተማማኝ ናቸው፤ ሰዎች ያለ ምክንያት አሳደውኛልና ርዳኝ። ⁸⁷ ከምድር ላይ ሊያስወግዱኝ ጥቂት ቀራቸው፤ እኔ ግን ትእዛዛትህን አልተውሁም። ⁸⁸ እንደ ምሕረትህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ፤ እኔም የአፍህን ምስክርነት እጠብቃለሁ።

_ቃልህ_KALIH_by_Gospel_singer_Yoseph_Bekele,_Yigerem_Wondwosen_,_Tinsae.m4a7.50 MB

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷³ እጆችህ ሠሩኝ፤ አበጃጁኝም፤ ትእዛዛትህን እንድማር ማስተዋልን ስጠኝ። ⁷⁴ ቃልህን ተስፋ አድርጌአለሁና፣ የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይበላቸው። ⁷⁵ እግዚአብሔር ሆይ፤ ፍርድህ የጽድቅ ፍርድ፣ ያስጨነቅኸኝም በታማኝነት እንደሆነ ዐወቅሁ። ⁷⁶ ለአገልጋይህ በገባኸው ቃል መሠረት፣ ምሕረትህ ለመጽናናት ትሁነኝ። ⁷⁷ ሕግህ ደስታዬ ነውና፣ በሕይወት እኖር ዘንድ ቸርነትህ ትምጣልኝ። ⁷⁸ እብሪተኞች ያለ ምክንያት በደል አድርሰውብኛልና ይፈሩ፤ እኔ ግን ትእዛዛትህን አሰላስላለሁ። ⁷⁹ አንተን የሚፈሩህ፣ ምስክርነትህንም የሚያውቁ ወደ እኔ ይመለሱ። ⁸⁰ እኔ እንዳላፍር፤ ልቤ በሥርዐትህ ፍጹም ይሁን።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵⁷ እግዚአብሔር ዕድል ፈንታዬ ነው፤ ቃልህን ለመታዘዝ ቈርጫለሁ። ⁵⁸ በፍጹም ልቤ ፊትህን ፈለግሁ፤ እንደ ቃልህ ቸርነትህን አሳየኝ። ✨ SELAH ✨
መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵⁷ እግዚአብሔር ዕድል ፈንታዬ ነው፤ ቃልህን ለመታዘዝ ቈርጫለሁ። ⁵⁸ በፍጹም ልቤ ፊትህን ፈለግሁ፤ እንደ ቃልህ ቸርነትህን አሳየኝ። ✨ SELAH ✨ A Week of Reading, Meditation, Prayer & Obedience Through God’s Word Join us and invite others to grow together in God’s Word. 📍 Facebook Page: https://www.facebook.com/hopministry10 📍 Telegram Channel: https://t.me/hopministry10

4_5854770414269501786.mp34.90 MB

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁶⁵ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቃልህ፣ ለአገልጋይህ በጎ ውለሃል። ⁶⁶ በትእዛዛትህ አምናለሁና፣ በጎ ማስተዋልንና ዕውቀትን አስተምረኝ። ⁶⁷ እንዲያው ሳይቸግረኝ መንገድ ስቼ ሄድሁ፤ አሁን ግን ቃልህን እጠብቃለሁ። ⁶⁸ አንተ መልካም ነህ፤ የምታደርገው መልካም ነው፤ እንግዲህ ሥርዐትህን አስተምረኝ። ⁶⁹ እብሪተኞች ስሜን በሐሰት አጠፉ፤ እኔ ግን ትእዛዝህን በፍጹም ልብ እጠብቃለሁ። ⁷⁰ ልባቸው የሠባና የደነደነ ነው፤ እኔ ግን በሕግህ ደስ ይለኛል። ⁷¹ ሥርዐትህን እማር ዘንድ፣ በመከራ ውስጥ ማለፌ መልካም ሆነልኝ። ⁷² ከአእላፋት ብርና ወርቅ ይልቅ፣ ከአፍህ የሚወጣው ሕግ ይሻለኛል።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵⁷ እግዚአብሔር ዕድል ፈንታዬ ነው፤ ቃልህን ለመታዘዝ ቈርጫለሁ። ⁵⁸ በፍጹም ልቤ ፊትህን ፈለግሁ፤ እንደ ቃልህ ቸርነትህን አሳየኝ። ⁵⁹ መንገዴን ቃኘሁ፤ አካሄዴንም ወደ ምስክርህ አቀናሁ። ⁶⁰ ትእዛዝህን ለመጠበቅ፣ ቸኰልሁ፤ አልዘገየሁምም። ⁶¹ የክፉዎች ገመድ ተተበተበብኝ፤ እኔ ግን ሕግህን አልረሳሁም። ⁶² ስለ ጻድቅ ሥርዐትህ፣ በእኩለ ሌሊት ላመሰግንህ እነሣለሁ። ⁶³ እኔ ለሚፈሩህ ሁሉ፣ ሥርዐትህንም ለሚጠብቁ ባልንጀራ ነኝ። ⁶⁴ እግዚአብሔር ሆይ፤ ምድር በምሕረትህ ተሞላች፤ ሥርዐትህን አስተምረኝ።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴⁹ ለአገልጋይህ የገባኸውን ቃል ዐስብ፤ በዚያ ተስፋ ሰጥተኸዋልና። ⁵⁰ ቃልህ ሕያው ያደርገኛልና፣ ይህች በመከራዬ መጽናኛዬ ናት። ⁵¹ እብሪተኞች እጅግ ተሣለቁብኝ፤ እኔ ግን ከሕግህ ንቅንቅ አልልም። ⁵² እግዚአብሔር ሆይ፤ ከጥንት የነበረውን ድንጋጌህን ዐሰብሁ፤ በዚህም ተጽናናሁ። ⁵³ ሕግህን ከተዉ ክፉዎች የተነሣ፣ ቍጣ ወረረኝ። ⁵⁴ በእንግድነቴ አገር፣ ሥርዐትህ መዝሙሬ ናት። ⁵⁵ እግዚአብሔር ሆይ፤ ስምህን በሌሊት ዐስባለሁ፤ ሕግህንም እጠብቃለሁ። ⁵⁶ ሥርዐትህን እከተላለሁ፤ ይህችም ተግባሬ ሆነች።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴⁷ እኔ እወደዋለሁና፣ በትእዛዝህ ደስ ይለኛል። ⁴⁸ እጆቼን ወደምወዳቸው ትእዛዛትህ አነሣለሁ፤ ሥርዐትህንም አሰላስላለሁ።
መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴⁷ እኔ እወደዋለሁና፣ በትእዛዝህ ደስ ይለኛል። ⁴⁸ እጆቼን ወደምወዳቸው ትእዛዛትህ አነሣለሁ፤ ሥርዐትህንም አሰላስላለሁ።

#ጸሎት እግዚአብሔር ሆይ ይህ ሞኝነት በሚመስል መንገድ እያደረግን ያለነው ነገር በውሎአችን ውስጥ ከቃልህ ጋር የተደጋገመ ንክኪ እንዲኖረን እያደረገን፣ ቃልህን ደጋግመን እንድንመለከተው፣ እንድናሰላስለው እየረዳን ስላለ እናመሰግንሃለን። እናምናለን ይሄ ጊዜ በትእዛዛትህ መንገድ እንድንሮጥ ልባችንን የምታሰፋበት ጊዜ ነው። በዚህ ፍለጋ ውስጥ የአንዳንዶቻችን የፈረሰ መሠውያ እየታደሰ ነው። ቃልህን በእጅና በአፋችን ብቻ ሳይሆን፤ በልባችን የምንይዝበት፣ የምንሰውርበት ጊዜ ይሁንልን። ሸማ ሰሪ ጥጡን በወደደው መንገድ ፈትሎ፣ አንዱን ክር ከሌላው ጋር እንደፈቀደው አጋምዶ አልባሳቱን ይሰራል፤ ውበት ያላብሰዋል። እግዚአብሔር ሆይ አንተም እንዲሁ ፈጣሪያችን፣ ሰሪያችን ነህና ሕያው፣ የሚሰራ በሆነው ቃልህ ሕይወታችንን እንደገና ፈትለህ ስራው፣ እንደወደድኽ አበጃጀን። ከልዑል አምላክ ማዕድ፣ ገበታ ያለመከልከል መቁረስ እንዴት መታደል ነው?! የተከበሩ የምንላቸው ሰዎች እንኳ በማዕዳቸው ማን መታደም እንዳለበት መስፈርት ያወጣሉ፤ የተመረጡ ለሚሏቸው ሰዎች ስፍራ፣ የክብር ወንበር ያዘጋጃሉ። እግዚአብሔር ሆይ አንተ ግን በሰው አይን የማይገቡ፣ የተናቁ የሚመስሉትን ሳትንቅ፤ የተሰበረና የተዋረደውን መንፈስ በማዕድኽ ዙሪያ የምትሰበስብ፣ የተራቡና በመንፈስ ድሆች የሆኑትን ከሕይወት ቃል፣ ከሕይወት እንጀራ የምታጠግብ ቸር አባት ነህና ስምህ ይባረክ። አቤቱ እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ የፊትህ ብርሃን በላያችን ያብራ፣ የቃልህ ፍቺ፣ ትርጓሜ አስተዋዮች ያድርገን፣ በትእዛዛትህ መንገድ እንድንሮጥ ልባችን ይስፋ!! አሜን!!

ቃልህ___Kalih(128k).m4a4.75 MB

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴¹ እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ወደ እኔ ይምጣ፤ ማዳንህም እንደ ቃልህ ይላክልኝ። ⁴² በቃልህ ታምኛለሁና፣ ለሚሰድቡኝ መልስ እሰጣለሁ። ⁴³ ሕግህን ተስፋ አድርጌአለሁና፣ የእውነትን ቃል ከአፌ ፈጽመህ አታርቅ። ⁴⁴ ከዘላለም እስከ ዘላለም፣ ሕግህን ዘወትር እጠብቃለሁ። ⁴⁵ ሥርዐትህን እሻለሁና፣ እንደ ልቤ ወዲያ ወዲህ እመላለሳለሁ። ⁴⁶ ምስክርነትህን በነገሥታት ፊት እናገራለሁ፤ ይህን በማድረግም ዕፍረት አይሰማኝም። ⁴⁷ እኔ እወደዋለሁና፣ በትእዛዝህ ደስ ይለኛል። ⁴⁸ እጆቼን ወደምወዳቸው ትእዛዛትህ አነሣለሁ፤ ሥርዐትህንም አሰላስላለሁ።

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³³ እግዚአብሔር ሆይ፤ የሥርዐትህን መንገድ አስተምረኝ፤ እኔም እስከ መጨረሻው እጠብቀዋለሁ። ³⁴ ሕግህን እንድጠብቅ፣ በፍጹም ልቤም እንድታዘዘው፣ ማስተዋልን ስጠኝ። ³⁵ በእርሷ ደስ ይለኛልና፣ በትእዛዝህ መንገድ ምራኝ። ³⁶ ከራስ ጥቅም ይልቅ፣ ልቤን ወደ ምስክርነትህ አዘንብል። ³⁷ ከንቱ ነገር ከማየት ዐይኖቼን መልስ፤ በራስህ መንገድ እንደ ገና ሕያው አድርገኝ። ³⁸ ትፈራ ዘንድ፣ ለአገልጋይህ የገባኸውን ቃል ፈጽም። ³⁹ የምፈራውን መዋረድ ከእኔ አርቅ፤ ደንብህ መልካም ነውና። ⁴⁰ እነሆ፤ ድንጋጌህን ናፈቅሁ፤ በጽድቅህ ሕያው አድርገኝ።

4_5866430421549503743.mp37.56 MB

መዝሙር 119 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁵ ነፍሴ ከዐፈር ተጣበቀች፤ እንደ ቃልህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ። ²⁶ ስለ መንገዴ ገልጬ ነገርሁህ፤ አንተም መለስህልኝ፤ ሥርዐትህን አስተምረኝ። ²⁷ የድንጋጌህን መንገድ እንዳስተውል አድርገኝ፤ እኔም ድንቅ ሥራህን አሰላስላለሁ። ²⁸ ነፍሴ በሐዘን ተዝለፈለፈች፤ እንደ ቃልህ አበርታኝ። ²⁹ የሽንገላን መንገድ ከእኔ አርቅ፤ ሕግህን በጸጋህ ስጠኝ። ³⁰ የእውነትን መንገድ መርጫለሁ፤ ሕግህንም ፊት ለፊቴ አድርጌአለሁ። ³¹ እግዚአብሔር ሆይ፤ ከምስክርነትህ ጋር ተጣብቄአለሁ፤ አሳልፈህ ለውርደት አትስጠኝ። ³² ልቤን አስፍተህልኛልና፣ በትእዛዛትህ መንገድ እሮጣለሁ።

#Testimony #ከሕይወቴ_የተቀዳ_ምስክርነቴና_ጸሎቴ! #ለእግዚአብሔር_ስለመኖር፣ #ስለ_አገልግሎት_ሳሰላስል_ከነበረው_ነገር_ጥቂት_ነገር_ላካፍላችሁ፤ #ጸሎቴንም_አብረን_እንጸልይ🙏 የእግዚአብሔርን ዕቃ የሚሸከም ሰው #ሊለይ ይገባዋል፣ እልፍ ሊል ይገባዋል፣ ከፊት ከፊቱ የሚሄደውን እግዚአብሔርን ብቻ እያየ ሊሄድ ይገባዋል። የሰው ንብረት ተሸክሞ የእኔ ነው እያለ የሚኩራራ፣ ራሱንም የሚያሳይ ሰው እጅጉን የተሞኘ፣ ተላላ ነው። የእግዚአብሔርን ዕቃ ለመሸከም ማን በብርታቱ የሚበቃ አለ? በራሳችን ቢሆን ሁላችንም ከክብሩ የጎደልን ነን። ብቁ የሆነው እግዚአብሔር ግን በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል ብቁዎች አደረገን። የከበረን መዝገብ በሸክላ ዕቃ ውስጥ ሊያኖር ወደደ። የማንበቃው እኛ እርሱ በብርታቱ ብቁዎች አድርጎን የከበረውን የእርሱን ዕቃ ለመሸከም በቃን። የእግዚአብሔርን ዕቃ የምሸከም መሆኔን ረስቼ፣ ችላ ብዬ፣ አቃልዬ፤ የማይረባኝ፣ የሚገድለኝ፣ ከእግዚአብሔር ሰፈር ከሚያጎድለኝ ሰፈር ጋር ተቆራኘው። የዛን ጊዜ #ሰው ብቻ (እንደማንኛውም ሰው) የምገባ የምወጣ፣ የምበላ የምጠጣ፣ የምለብስ የማጌጥ፣ የምተኛ የምነሳ.....በሰው መስፈርት አስፈላጊ የተባለ ነገር ሁሉ ያልጎደለብኝ፣ በእግዚአብሔር አይን ግን የከሰርኩ፣ ሞገስ የሌለኝ፣ የራሴን ፈቃድ አድራጊ፣ ባካኝ ሆኜ ተገኘው። በተለያየ ጊዜ የተለያየ አይነት ፈተና፣ በሰው አይን ስኬት የሚባል የተለያየ ነገር ገጥሞኝ ከእግዚአብሔር ፊት እያራቀኝ ነው፣ እያባከነኝ ነው.... ብዬ ያዙኝ ልቀቁኝ ያልኩበት ብዙ ጊዜ አለ። እንደዚህኛው #ጠላቴ ግን ክፉ ሆኖብኝ አያውቅም። ይሄኛው ጠላቴ ስላችሁ ግን ከውጪ የሚመጣ ሌላ ጀብደኛ ሰው፣ ፈርጣማ ጦረኛ፣ አጋንንት....አትጠብቁ። #ጠላቴ እኔው፣ እኔነቴ ነው። በፊት በፊት ካለመጸይ ይልቅ መጸለይ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ካለማጥናት ይልቅ ከቃሉ ጋር መቆየት ለእኔ እጅግ ቀላሉ ነገር ነበር። አንዳንዴማ "ሰው እንዴት ሳይጸልይ ይኖራል?!  የእግዚአብሔርን ቃል ሳያነቡ መዋል ይቻላል?!" ብዬ ስጠይቅ እንደ እኔ የሚታበይ ሌላ ሰው ያለ አይመስለኝም። በዚህ ሁኔታ ስኖር ሕይወት ዘርፈ ብዙ ጓዝ፣ አቅጣጫም አላትና የስራ ጫና፣ የቤተሰብ ጉዳይ፣ ከሰዎች ጋር ያሉ ግንኙነቶች፣ አገልግሎት፣ የጤና ችግር፣ አድካሚ ውሎ፣ ማህበራዊ ሚዲያ.....ምክንያት ይሁን ከተባለ ሌላም  የሚዘረዘር እልፍ ነገር አለና ይህ ሁሉ #ከእኔነቴ፣ ጎኑን ከሚጠብቀውና ምቾቱን በምንም ማስነካት ከማይፈልገው ማንነቴ፣ ሥጋዬ ጋር ተባብሮ በአፍ ሳይሆን በተግባር እግዚአብሔርን ጠል፣ ሰነፍ፣ ዳተኛ፣ ስንፍና የተጠናወተው ሌላ ሰው ወለደ። እግዚአብሔርን ከሚወደው፣ በፊቱ መቆየት ከሚናፍቀው፣ ቃሉን ከሚራበው መንፈሴ ይልቅ በተግባሬ አልጎስም ያልኩት ሥጋዬ ሲያሸንፍ፣ አለመጸለይ፣ እግዚአብሔርን አለመፈለግ፣ ቃሉን አለማንበብ ስራዬ ሲሆን፤ ለብታ ሲውጠኝ በደንብ ይታወቀኛል። ይሄ ሁሉ ሲሆን #መንፈስ_ቅዱስ የት ሄዶ ነው?! እንደምትሉኝ እርግጠኛ ነኝ። ስለ መንፈስ ቅዱስ የገባኝ አንድ ቁልፍ ነገር ቢኖር ግን፦ እርሱ የሥርዓት፣ የመርህ አምላክ መሆኑን እና ማንንም ያለ ፈቃዱ ጎትቶ እንደማይገዛ፣ ፈቃዳቸውን ለእርሱ ለሰጡና በራሳቸው እንደማይችሉ አምነው እጆቻቸውን ወደ እርሱ ላነሱ ሰዎች ግን ደራሽ፣ አጋዥ፣ ለእግዚአብሔር የመኖሪያ አቅም መሆኑን ነው። #በራሴ_አልቻልኩም፣ #በቃኝ_አቅቶኛል ብዬ ራሴን ለእርሱ ስሰጥ ግን ካለሁበት ነጥቆ ሊያወጣኝ ብርቱ እና የታመነ መሆኑን ነው። በዚህ ሂደት ውስጥ ሌላው ቁልፍ ነገር መርህ (#Discipline)፣ ራስን ማስለመድ፣ ማስገዛት ነው። ዓላማችን ልክ ያልሆነውን መንገድ ትቶ ወደ እግዚአብሔር መመለስ፤ ለእርሱ መገኘት፣ መገዛት ከሆነ በዚህ መጽናት እጅግ አስፈላጊ ነው። ምክንያቱም ለድካምም ሆነ ለብርታት፣ ለመጸለይም ሆነ ላለመጸለይ.... #ድግግሞሹ  ወሳኝ ነገር ነው፤ ተደማምሮ ልማድ (#Habit) ይሆናል። በተሰበረ መንፈስ፣ በተሰበረ ልብ ወደ እግዚአብሔር ፊት ስቀርብ፤ የሆንኹትን ሆኜ፣ አንዳች ሳልደብቀው፣ "ተመልከተኝ፤ እኔ እንደዚህ ነኝ፤ አልቻልኩም፤ አቅቶኛል፤ ጸጋህና ምህረትህ ያስፈልገኛል" ስለው ከወደቅኹበት እፍስፍስ አድርጎ ሲያነሳኝ፣ ስብራቴን ሲጠግን፣ ጸጋውን ሲያበዛልኝ፣ እንደገና አድሶ ሲያቆመኝ እልፍ ጊዜ አይቼዋለሁ። ይሄ ሁሉ የእኔ ውጣ ውረድ ነው። የኔ ህመም ህመሙ የሆነ፣ በፈተናዬ የተፈተነ፣ በመንገዴ ያለፈ ብዙ ሰው እንደሚኖር ስለማምን ከብርታቴ ብቻ ሳይሆን ከድካሜም ይማራል ስል ይሄን ጻፍኹ። ይሄ ደግሞ ጸሎቴ ነው። የሚሰማ፣ ሰምቶም የሚመልስ አምላክ እንዳለ በማመን ይሄን እላለሁ፦ ጌታ ሆይ ዛሬ በድካም፣ በስንፍና፣ በኃጢአት፣ በለብታ ለዛለች ነፍሴ የምነግራት አንተ የነገርኸኝ አንድ ነገር ቢኖር "የእግዚአብሔርን ዕቃ የምትሸከሚ ነሽ፣ የእግዚአብሔርን ዕቃ የምሸከም ነኝ።" የሚል ብቻ ነው። ይሄን እውነት በውል፣ በቅጡ ስረዳ ሁሉ ነገር፣ አዋዋሌ፣ አመለካከቴ፣ ምግባሬ፣ ረሃቤ፣ ዝግጅቴ ይቀየራል። ማገልገል የእግዚአብሔርን ዕቃ መሸከም ነውና ያንተን ዕቃ ለመሸከም እንደተጠራ፣ እንደተሸከመ ሰው ለአንተ እንድለይ፣ በመንፈስ ቅዱስ ራሴን እንድጠብቅ፤ ከአንተ የሚያርቅ፣ ከአንተ በልጦ ጣዖት ሊሆን የሚወድ፣ በእኔ ላይ ሊነግስ የሚወድ ነገር ሁሉ ርኩስ ነውና ርኩስ ነገር እንዳልነካ፣ ፊት ፊቴ የሚሄደውን እግዚአብሔርን ብቻ እያየሁ እንድከተል፣ እንድከታተል ጸጋ ይብዛልኝ!! መንፈስህ ይርዳኝ!! አሜን!!

4_5769383569617070333.mp34.55 MB