uk
Feedback
HOP Ministry

HOP Ministry

Відкрити в Telegram

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.

Показати більше
Країна не вказанаКатегорія не вказана
558
Підписники
+424 години
+217 днів
+5430 днів

Триває завантаження даних...

Схожі канали
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
вересень '26
вересень '26
+46
в 1 каналах
серпень '26
+83
в 1 каналах
Get PRO
липень '26
+459
в 3 каналах
Get PRO
червень '260
в 2 каналах
Get PRO
травень '26
+3
в 2 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
19 вересня+3
18 вересня+4
17 вересня+1
16 вересня+2
15 вересня+5
14 вересня+7
13 вересня+2
12 вересня+4
11 вересня+5
10 вересня+2
09 вересня+1
08 вересня+1
07 вересня+1
06 вересня+2
05 вересня0
04 вересня+2
03 вересня+4
02 вересня0
01 вересня0
Дописи каналу
ዘማሪ_ቤተልሄም_ወልዴ_አንተን_የታመነ_መች_አፈረ_Protestant_mezmur_ፕሮቴስታንት_መዝሙሮች128k.m4a6.95 MB

2
#የእግዚአብሔርን_የጊዜ_ሰሌዳ_አለመቅደም። #በእግዚአብሔር_አሳብ_ውስጥ_መቆየት። #እግዚአብሔርን_መታመን። #የእግዚአብሔርን_ፈቃድ_ማወቅ። #የእግዚአብሔርን_ጊዜ_መጠበቅ። #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional https://t.me/hopministry10
349
3
#የማለዳ_ጸሎቴ፦ እግዚአብሔር ሆይ የቀኑ ክፋት እንዳይዘኝ፣ በቀኑ ሸክም እንዳልያዝ፣ አንተን በማሳብ ውስጥ ሕይወቴን እንዳኖር፣ እንዳቆይ እርዳኝ!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 September 18, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
600
4
በጎ ፈቃዱን ማድረግ እንዳለብን ነግሮን፣ አድርጉ ብሎ፣ ለብቻችንን ጥሎን ዘወር የማይል አምላክ እግዚአብሔር! ይልቁንም በጎ ፈቃዱን መፈለግ እንድንችል ልባችንን ያሰፋል፤ ደግሞም በጎ ፈቃዱንም በእኛ ውስጥ በሚኖረው በመንፈሱ በእኛ ውስጥ ይሠራዋል። ታዲያ በእግዚአብሔር #ድግፍ! ማለት፣ እርሱ በእኛ ውስጥ እንዲሰራ ራሳችንን ለእርሱ ማስገዛት እንዴት አያዋጣንም?! እግዚአብሔርን ማክበር ሽቶ በተቃራኒው ደግሞ ያለ እግዚአብሔር ሮጦ፣ በራስ ታግሎ የትም አይደረስም! ይልቁንም እንደ በጎ ፈቃዱ መፈለግንና ማድረግን በእኛ ውስጥ በሚሠራው በእግዚአብሔር እርፍ፣ ድግፍ ብሎ፣ እርሱን ተጠግቶ ሲኖር ክርስትና ቀላል ነው። ፊልጵስዩስ 2 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹² ስለዚህ፣ ወዳጆቼ ሆይ፤ ሁልጊዜም ታዛዦች እንደ ነበራችሁ ሁሉ፣ አሁንም እኔ በአጠገባችሁ ሳለሁ ብቻ ሳይሆን፣ ይልቁንም አሁን በሌለሁበት ጊዜ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ፤ ¹³ እንደ በጎ ፈቃዱ መፈለግንና ማድረግን በእናንተ ውስጥ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና። ✍️ መክሊት አየለ 📆 September 15, 2024 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
945
5
#በየዕለቱ_የሚጨምር_እምነት። ከእግዚአብሔር ጋር በቆየን፣ በፊቱ በሰነበትን መጠን እግዚአብሔር ላይ ራስን ወደ መጣል፤ ይበልጥ እርሱ ላይ ጥገኛ ወደ መሆን ማደግ፣ በእውቀት በበሰልን እና ከእግዚአብሔ
#በየዕለቱ_የሚጨምር_እምነት። ከእግዚአብሔር ጋር በቆየን፣ በፊቱ በሰነበትን መጠን እግዚአብሔር ላይ ራስን ወደ መጣል፤ ይበልጥ እርሱ ላይ ጥገኛ ወደ መሆን ማደግ፣ በእውቀት በበሰልን እና ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ብዙ በቆየን መጠን እምነታችንን እያደረጀን መሄድ እንዴት መታደል ነው?! ትናንት በመንፈሳዊው ነገር ልጅ በነበርኹ ጊዜ፣ የእግዚአብሔርን ቃል በቅጡ ሳልረዳ እግዚአብሔር ላይ የበረታ እምነት ነበረኝ። ከእርሱ በላይ ስለእኔ የሚያውቅልኝ እንደሌለ ጠንቅቄ አውቃለሁ። በሆነው ባልሆነው፣ ሰበብ አስባብ እየፈለግኹ ወደ እግዚአብሔር ለመሮጥ፣ ራሴንና ነገሬን እርሱ ላይ ለመጣል አቅም ነበረኝ። በእግዚአብሔር ቤት ስጎለምስ፣ በእውቀትም እንዳደግኹ ሲሰማኝ፣ አእምሮዬም ሁሉን ለመመርመር ሲቸኩል እግዚአብሔርን አምኖ ከመከተል ይልቅ ለሁሉ ነገር ማብራሪያ መጠየቅ ሲቀናኝ ራሴን አገኘሁ። በእድሜ፣ በእግዚአብሔር ቤትና በፊቱ በመሰንበት፣ በእውቀት እያደግኹ በሄድኹ መጠን እምነቴም እየጨመረ፣ እግዚአብሔርን መደገፌ እየበረታ ቢሄድ ብዬ ተመኘሁ፤ በዚህ ማለዳም ለእግዚአብሔር ይህንን ልመና ላቀርብ ወደድኹ፦ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ ከአንተ ጋር በመሰንበት በነገር ሁሉ ሳድግ በየዕለቱ በሚያድግ እምነት፣ ዘወትር በሚጨምር አንተን መደገፍ ባርከኝ። አንተን ይበልጥ እያወቅሁኽ ስመጣ፣ የቃልህ ፍቺ ሲበራልኝ አንተ ላይ ያለኝ መደገፍ፣ ራሴን አንተ ላይ መጣሌ ይጨምር። አቤቱ ያለ ቅድመ ሁኔታ የሆነ እምነት፤ ሳያይ፣ ለእያንዳንዱ ነገር ማብራሪያ ሳይጠይቅ አንተን የሚከተል ልብ፤ ከሚያየው ነገር በላይ ቃልህን የሚያምን ማንነት ስጠኝ!! አሜን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 September 15, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
922
6
ቃልህ___Kalih(128k).m4a
867
7
#ከእግዚአብሔር_ቃል_ጋር_መቆየት። ከእግዚአብሔር ቃል ጋር በምንወስደው ጊዜ፣ በምንቆየው ቆይታ እጅግ አትራፊዎች ነን። ሕያው፣ የሚሰራ ብቸኛው ቃል የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው። እኛን በሚያይ፣ በሚያውቅ በእግዚአብሔር ፊት ሁሉ ነገራችን የተገለጠና የተራቆተ ነው። ሆኖም እግዚአብሔር ድካምን ቢያይብን፣ እንከን ቢያገኝብን፣ ገልጦ ሊያዋርደን ሳይሆን፣ በቃሉና በመንፈሱ ሊሰራን፣ ሊገራን፣ እርሱ የወደደውን ቅርጽ ሊያስይዘን የታመነ ነው። የክርስቲያናዊ ሕይወት ቱምቢ፣ የእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት መለኪያ የእግዚአብሔር ቃል ነው። በቃሉ ተመዝኖ ያለፈ፣ ይሁንታን እንደሚያገኝ ሁሉ፣ በቃሉ ተመዝኖ የወደቀም ከቃሉ መስፈርት የራቀ መሆኑ ይገለጣል። የእግዚአብሔር ቃል በአንባቢው ላይ ያለውን ሥራ እንደማንኛውም መጽሐፍ ንባብ፣ አእምሮአዊ እውቀትን ማስፋት ላይ ብቻ አያቆምም። ይልቁንም የአንባቢውን ሁለንተና አንዳች ሳያስቀር ይመረምራል፣ ይሰራል፣ ይቀይራል። ምክንያቱም ቃሉ ሕያውና የሚሰራ ነውና። ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ለመቆየት ብርታት ከሚሆነን ነገር መካከል አንዱ፣ የቃሉ ሕያው መሆንና የሚሰራ መሆኑ ነው። በምንም ዓይነት ሁኔታ ወደ እርሱ ብንቀርብ እንደነበርን የማይተወን፣ ዘወትር ሊሰራን የታመነ፣ አላስፈላጊ ሸክሞቻችንን አራግፎ በእግዚአብሔር ሸክም የሚሞላን፣ ቸሩ እግዚአብሔር የሰጠን የሕይወታችን መመሪያ ቅዱስ ቃሉ ነው። እውቀትን ከመቅዳት እልፍ ያለ ዓላማ ይዞ ወደ እግዚአብሔር ቃል የተጠጋ፣ ከቃሉ ጋር የቆየ፣ ቃሉን ሁነኛ ወዳጅ ያደረገ ሰው፣ መቼም የማይሳሳት መካሪ፣ እውቀት የማይጎድለው አስተማሪ፣ መስራትና ማበጃጀት የማይደክመው ፍጹም አድርጎ ሰሪ ያገኛል። ከሁኔታዎች እልፍ እያልን ከቃሉ ጋር እንቀመጥ፣ እንቆይ፤ እስከ ዛሬ ያላየነውን እልፍ በረከት እናገኛለን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 September 14, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
1 092
8
https://t.me/HOPMinistryBSGroup
978
9
ሰላም ቤተሰቦቼ እንዴት ናችሁ። ትናንት እና ከትናንት በስቲያ በተከፈተው ድምጽ መስጫ Poll ላይ በመሳተፍ ድምፅ የሰጣችሁ ሰዎችን እያመሰገንኹ፤ ቋሚ፣ ሳምንታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለመጀመር ታስቦ ድምፅ ለመሰብሰብ በተከፈተው Poll ላይ ከ50 % በላይ የሚሆነው  ድምጽ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቱ ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ የሆኑ ሰዎች እንዳሉ ያሳያል። በዚህ መሰረት ጥናቱን ለመጀመር እንዲረዳን ይህ የቴሌግራም ግሩፕ ተከፍቷል። ስለሆነም ጥናቱ ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ የሆናችሁ ሰዎች ግሩፑን በመቀላቀል ቢጠና ብላችሁ የምታስቡትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እና ለእናንተ አመቺ የሆነውን የጥናት ቀንና ሰዓት እንድትጠቁሙ እንጠይቃለን። በዚህ መሰረት ከሁሉም ተሳታፊ ጥቆማ ከሰበሰብን በኋላ የሚጠናውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እና ምቹ ጊዜ የቴሌግራም Poll በመጠቀም መርጠን ጥናቱን እንጀምራለን። ተባረኩ!!🙏
1
10
#የአዲሱ_ዓመት_ጸሎቴንና_የትኩረት_አቅጣጫዬን_ላጋራችሁ። አዲስ ዓመት ነገሮችን አንድ ብሎ፣ በአዲስ ኃይል፣ በታደሰ ጉልበት፣ በተስፋ ለመጀመር እድል ስለሚሰጥ ለእኛ ለክርስቲያኖች ምንም ያህል ትናንት የጀመረ ትጋት፣ መልካም ልማድ ቢኖረንም እንኳ፤ እንደ አዲስ እግዚአብሔርን የመከተል፣ ኢየሱስን የመምሰል፣ እርሱን ተጠግቶ የመኖር ረሃብ፣ በፊቱ የመቆየት ጉልበት፣ ቃሉን እንደ አዲስ የመውደድ መሻት እንዲኖረን ይረዳናል። ከትናንት ይበልጥ ወደ ተጨመረልን ቀን፣ ወደ አዲሱ ዘመን ሊሻገሩ የሚገቡ በጎ ልማዶች፣ ፣መልካም መሻቶች፣ ሊተገበሩ የሚገባቸው ዕቅዶችን ለመሰነቅ እድል ይሰጣል። ስለዚህ እኔም በዚህ እድል ተጠቅሜ ራሴን ለማየት ሞክሬ፣ ደግሞ ከፊት ላለው ዘመን የያዝኹት የትኩረት አቅጣጫ፣ ለእግዚአብሔር ያቀረብኹት ልመና አለኝ። ባጋራችሁ ይጠቅማል ብዬ ስላሰብኹ እንደዚህ ለማቅረብ ሞክሪያለሁ። ጸሎትና ልመናዬን በመጋራት፣ ተግባር በሚሻው ነገርም በመትጋት ማትረፍ ይሁንልን!! እግዚአብሔርን ከምለምነው ቁልፍ ልመናዎቼ መካከል፦ 1. የማለዳ ሰው አድርገኝ፦ በቀኔ መጀመሪያ ላይ ወደ የዕለት ተግባሬ ሳልዘረጋ በፊት ከአንተ ልብ፣ ከአንተ ፊት የዕለት ስንቅ መያዝ ይሁንልኝ። ደግሞ ለአንተ የምሰጠው ጊዜ ማለዳዬን፣ የነቃውን፣ ኃይል ያለበትን፣ የተከፈተ ልብ፣ የተዘጋጀ አእምሮ፣ የሚሮጡ እግሮች፣ የበረታ ጉልበት ያለበትን እንጂ፤ ከብዙ ነገር የተራረፈውን፣ ሽርፍራፊ ሰዓት፣ የተበላ ጉልበት፣ በዛለ ልብ የሆነውን የአመሻሽ ጊዜ አይሁንብኝ። 2. እንደ ሰው ብዙ የሚያስፈልገኝ፣ የሚያስጨንቀኝ ጥያቄ ቢኖር፤ መፍትሄ ፍለጋ ወደ ማንም፣ ወደ ምንም ዘወር ከማለቴ በፊት ወደ አንተ ልመልከት፤ ወደ አንተ ልጠጋ፣ አቅጣጫና ምሪትን ከአንተ ልቀበል። ደግሞ ጸሎቴና ልመናዬ እንዳይቀር፣ ለይምሰል አይሁንብኝ፤ ይልቁንም እግዚአብሔር እንዳለ፣ ከልብ ለሚፈልጉትም ዋጋን እንደሚሰጥ በማመን፣ በእምነት የሚቀርብ ይሁንልኝ። 3. በየዕለቱ የነቃ ማንነት፣ የሚሰራ፣ የሚዘጋጅ፣ ሁሉን ከዘላለም አንጻር የሚያይ፣ የሚገመግም፣ የሚያደርግ ማንነት፤ በእግዚአብሔር እርሻ ውስጥ፣ በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ድርሻውን በአግባቡ የሚወጣ ማንነት እንዲኖረኝ እርዳኝ። ድንገት አንተ ብትመጣ፣ ወይም የእኔ ቀን ደርሶ ብትወስደኝ በመክሊቴ እያተረፍኹ እንድገኝ፣ ያለ አንዳች ጸጸት ወደ አንተ እንድሰበሰብ እርዳኝ። 4. ታላቁ ተልዕኮ የሁልጊዜ የጠረጴዛ ላይ ጉዳዬ ይሁን። 5. ከእግዚአብሔር የተሰጡኝ፣ ነገር ግን የጣልኻቸውን መክሊቶቼን፣ የዘነጋኹትን ትጋቴን ማንሳት፣ በመክሊቴ ማትረፍ ይሁንልኝ። መስራት ያለብኝን ነገር የባከነ ሰዓት ላይ እንዳ ሰው በፍጥነት፣ በትጋት መስራት ይሁንልኝ። 6. መንፈስ ቅዱስ የዘወትር ወዳጄ፣ ናፍቆቴ፣ መደገፊያዬ ይሁነኝ። በማልፍበት ሁሉ የእግዚአብሔር ጸጋ በእኔ የወደደውን ይፈጽም። አሜን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 መስከረም 2, 2019 (September 12, 2026) #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
1 279
11
በቴሌግራም ግሩፕ ቋሚ የሆነ ሳምንታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ቢጀመር፤ ለመሳተፍ ዝግጁ ነዎት?
1 122
12
በዚህ ቻነል ላይ ከሚቀርቡ የተለያየ ይዘት ካላቸው አገልግሎቶች በየትኛው ይበልጥ ተጠቅመዋል? የቱ ተጠናክሮ ይቀጥል?
1 173
13
መዝሙር 23 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ የዳዊት መዝሙር መልካሙ እረኛ ¹  እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፤ አንዳች አይጐድልብኝም። ² በለመለመ መስክ ያሳርፈኛል፤ በዕረፍት ውሃ ዘንድ ይመራኛል፤ ³ ነፍሴንም ይመልሳታል። ስለ ስሙም፣ በጽድቅ መንገድ ይመራኛል። ⁴ በሞት ጥላ ሸለቆ ውስጥ፤ ብሄድ እንኳ፣ አንተ ከእኔ ጋር ስለ ሆንህ፣ ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ፣ እነርሱ ያጽናኑኛል። ⁵ ጠላቶቼ እያዩ፣ በፊቴ ማዕድ አዘጋጀህልኝ፤ ራሴን በዘይት ቀባህ፤ ጽዋዬም ሞልቶ ይፈስሳል። ⁶ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣ በጎነትና ምሕረት በእርግጥ ይከተሉኛል፤ እኔም በእግዚአብሔር ቤት፣ ለዘላለም እኖራለሁ። #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
1 098
14
04 azeb 4.mp3
1 091
15
ኤርምያስ 29 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹¹ ለእናንተ ያለኝን ዕቅድ እኔ ዐውቃለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ዕቅዱም ፍጻሜው ያማረና ተስፋ የሚሰጥ፣ እናንተንም የሚጠቅም እንጂ የሚጐዳ አይደለም። ¹² እናንተም ትጠሩኛላችሁ፤ ቀርባችሁ ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፤ እኔም እሰማችኋለሁ። ¹³ እናንተ ትፈልጉኛላችሁ፣ በፍጹም ልባችሁም ከፈለጋችሁኝ ታገኙኛላችሁ፤ ¹⁴ እኔም እገኝላችኋለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤” https://t.me/hopministry10
1 244
16
ኤርምያስ 29 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹¹ ለእናንተ ያለኝን ዕቅድ እኔ ዐውቃለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ዕቅዱም ፍጻሜው ያማረና ተስፋ የሚሰጥ፣ እናንተንም የሚጠቅም እንጂ የሚጐዳ አይደለም። ¹² እናንተም ትጠሩኛላችሁ፤ ቀርባችሁ ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፤ እኔም እሰማችኋለሁ። ¹³ እናንተ ትፈልጉኛላችሁ፣ በፍጹም ልባችሁም ከፈለጋችሁኝ ታገኙኛላችሁ፤ ¹⁴ እኔም እገኝላችኋለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤” #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
1 049
17
ሰላም ተወዳጆች #መስከረም_1_እንጀምራለን ። ጌታ ቢፈቅድና ብንኖር 2019 ላይ ሙሉ የመጽሐፉ ቅዱስ ክፍል የማጥናት ሀሳብ አለን። የጥናቱ ሂደት የሚሆነው በያለንበት ስፍራ በቀን 4 ምእራፍ ማንበብ ወይም በድምጽ መስማት እንደ ጌታ ፍቃድ 2019 ከማለቁ በፊት ሙሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የማጥናት እድል ይኖረናል። በዚ መሳተፍ ምትፈልጉ ለጥናት እንዲረዳን የተከፈተ ቴሌግራም ግሩፕ አለ join ያድርጉ ። 🙏🙏 https://t.me/+jEruievHWbAwMjM0
141
18
ያ_ሰው_Ezra_Nigussie_ya_sewu_Live_worship_እዝራ_ንጉሴ_New_protestant_mezemur.m4a
181
19
“በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣ በጎነትና ምሕረት በእርግጥ ይከተሉኛል፤ እኔም በእግዚአብሔር ቤት፣ ለዘላለም እኖራለሁ።”   — መዝሙር 23፥6 (አዲሱ መ.ት) “ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።”   — መዝሙር 23፥6 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
1 376
20
“ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።”   — መዝሙር 23፥6 https://t.me/hopministry10
1