ru
Feedback
ሚኒሊክ TV

ሚኒሊክ TV

Открыть в Telegram

He is still our hero!

Больше
2 677
Подписчики
+324 часа
-77 дней
-1730 день

Загрузка данных...

Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июнь '26
июнь '26
+74
в 0 каналах
май '26
+50
в 0 каналах
Get PRO
апрель '26
+68
в 0 каналах
Get PRO
март '26
+41
в 0 каналах
Get PRO
февраль '26
+28
в 0 каналах
Get PRO
январь '26
+36
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '25
+45
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+53
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '25
+70
в 2 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+60
в 1 каналах
Get PRO
август '25
+68
в 6 каналах
Get PRO
июль '25
+76
в 0 каналах
Get PRO
июнь '25
+102
в 0 каналах
Get PRO
май '25
+101
в 2 каналах
Get PRO
апрель '25
+109
в 4 каналах
Get PRO
март '25
+182
в 4 каналах
Get PRO
февраль '25
+131
в 6 каналах
Get PRO
январь '25
+247
в 12 каналах
Get PRO
декабрь '24
+401
в 12 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+444
в 11 каналах
Get PRO
октябрь '24
+512
в 12 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+208
в 13 каналах
Get PRO
август '24
+683
в 16 каналах
Get PRO
июль '24
+715
в 13 каналах
Get PRO
июнь '24
+408
в 9 каналах
Get PRO
май '24
+650
в 12 каналах
Get PRO
апрель '24
+13
в 11 каналах
Get PRO
март '24
+22
в 0 каналах
Get PRO
февраль '24
+80
в 11 каналах
Get PRO
январь '24
+283
в 2 каналах
Дата
Привлечение подписчиков
Упоминания
Каналы
21 июня+1
20 июня+5
19 июня+1
18 июня+1
17 июня+2
16 июня+4
15 июня+3
14 июня+3
13 июня+3
12 июня+5
11 июня+1
10 июня+3
09 июня+3
08 июня0
07 июня+9
06 июня+2
05 июня+5
04 июня+4
03 июня+3
02 июня+8
01 июня+8
Посты канала
2
* ፀረ አምሓራ የኦሮሞ ኃይል፦ ከአረቡም ከጥቁሩም ከምዕራባውያንም ከሩቅምስራቁም ጋር ያለ አጥር ተባብሮ አምሓራ እና ኦርቶዶክሳውያንን ለማጥፋት በስልት ጫካ እና ቤተ መንግስት ተቀጣጥሮ ውድመት በማድ
* ፀረ አምሓራ የኦሮሞ ኃይል፦ ከአረቡም ከጥቁሩም ከምዕራባውያንም ከሩቅምስራቁም ጋር ያለ አጥር ተባብሮ አምሓራ እና ኦርቶዶክሳውያንን ለማጥፋት በስልት ጫካ እና ቤተ መንግስት ተቀጣጥሮ ውድመት በማድረስ ቀጠናውን ከማይፈልጋቸው ሰብዐውያን እያፀዳ ነው። * ህወሓት ከዚህ ቀጣይ እርሷንም የማይምር ጥቃት ለመዳን እና የሀገረ መንግስት ፕጀክቷን ለማሳካት ጠቃሚ ያለችውን የይደር ጠላት ቅነሳ ታክቲካዊ ስልት በማድረግ በከፍተኛ ጥበብ አምሓራውን ያዳክምልኛል ያለችውን የመከፋፈል ስራ እያሳለጠች፣ በመቀሌ ለፀረ አምሓራ ድርጅቶች ቢሮ ከፍታ እያስወጋች ጎን ለጎን ፋኖ ጋር ፅምዶ ፈጠርኩ በማለት የራሷን የመደራደር ሀቅምንም እያፈረጠመች ነው። ከሰሞኑ የG7 ሀገሮች ስብሰባ ላይ ፋሽስቱ አብይ አለመጠራትን በመከለል የመለስን ስም እየጠሩ ወያኔን ናፋቂ ፕሮፖጋንዳ ሰሪ የመብዛቱ ሚስጥር ከሰሞኑም ጀርባውን የሚያሳክከው ተሸካሚዋ የበዛላት ከጠንካራ የጥቅም እና ታክቲካዊ ዲፕሎማሲዋ ውጤት ነው። እዚህ እኛ መንደርስ? መልከ ብዙ መነቋቆር እና መናናቅ፣ መጠራጠር ያለበት የቅርብ አዳሪነት ሽኩቻ ስፍራ ይዟል። ትግሉን ከዐምሓራ ዘላቂ እና የአጭር ጊዜ ጥቅም አንፃር ያልተገመገሙ ጮርቃ ተናባቢ ያልሆኑ የየቀጠናው እርምጃዎች፣ ትምምን አልባ ሰርጎገቦችን አማካሪ ያደረገ አቅጣጫ የህዝብን ትግል አደጋ ላይ ጥሎታል። https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418 ሰኔ 13/2018 ዓ.ም ሞዐ ሚዲያ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ       https://t.me/Moamediamoresh
124
3
+2
Нет текста...
195
4
በአማራ ሕዝብ ላይ የተመዘዘው የጥፋት ሰይፍ ጠላቶቻችን “አማራ አንገቱ አንድ ነው” በሚል እምነት ሁሉንም አማራ ዒላማ ያደረገ ስለመሆኑ ለዘመናት አየተህዋል፡፡ አማራ አዲስ አበባም፣ ራያም፣ ወለጋም፣ ወልቃይትም፣ ደራም፣ መተከልም አርሲም፣ ሐረርጌ፣… ሲገደል የኖረውና እየተገደለ ያለው በማንነቱ ነው፡፡ ይህ ትግል፣ በማንም የማይጠለፍ፣ በማንም የማይደለልና የቆመለትን ታሪካዊ ኃላፊነት በራሱ ክንድ ለመወጣት የተነሳ ኃያል ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ እንዲቀጥል፣ በዕጣ ፈንታህ ላይ የሚጣጣሉ የጽምዶ ደላሎችን በመረጃና በማስረጃ አውቀህ ልትነጥላቸው፣ ልትታገላቸው ይገባል፡፡ ወደፊትም በተከታታይ የምናደርስህን እውነተኛ መረጃ የትግል ስንቅህ እንድታደርገው ጥሪያችንን ከወዲሁ እናቀርባለን፡፡ በአጠቃላይ የግልባል ፋኖ ሚዲያ አመራርና ባልደረቦች የመረጃ ጦርነቱን ስትራቴጂካዊ በሆነ መልኩ እየመራነው እንገኛለን፡፡ በዚህ የህልውና ትግል ላይ በግልጽ መታወቅ ያለበት ጉዳይ፡- ኦሕዴድ ብልጽግና የሚዋጋው ለኦሮሞ ኢምፓየር፤ ህውሃት በጽምዶ ስም ለዳግም ወረራ የተነሳው ለታላቋ ትግራይ ምስረታ በሆነበት ሁኔታ፣ የአማራ ሕዝብ ስትራቴጂካዊ ጥቅሙን ማስጠበቅ እንጅ መናጆ መሆን የለበትም ብለን እናምናለን፡፡ የወልቃይት፣ የራያ፣ የመተከልና የአዲስ አበባ ጥያቄዎች ምላሽ የሚያገኙት በጽምዶ ቸርነት ሳይሆን፣ የአማራ ሕዝብን እና ታሪካዊ ወዳጆችን ማዕከሉ ባደረገ ፍፁም አሸናፊነት ብቻ ነው። ስለሆነም ሕዝባችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ህልውናውን በክንዱ ለማስከበር ከእውነተኛው የፋኖ ትግል ጎን በመቆም መፋለሙን እንዲቀጥል ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ ግሎባል ፋኖ ሚዲያ ኤዲቶሪያል ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድል ለድል አድራጊው ፋኖ! ድል ለአማራ ሕዝብ! ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ! ግልባጭ፡- ለአፋብን ምክትል ሊቀመንበር ለወታደራዊ ጉዳዮች ኃላፊ ለአፋብን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለአፋብን ፖለቲካ መምሪያ ለአፋብን አራቱም ቀጠናዊ ዕዞች ባሉበት፤
181
5
ከ ግሎባል ፋኖ ሚዲያ ኤዲቶሪያል የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ አርበኝነት ውርሳችን፤ ታሪካዊነት ትርፋችን! ግሎባል ፋኖ ሚዲያ የአማራ ሕዝብ የገጠመውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ በሚደረግ እልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ በመረጃ ጦርነት፣ ፊት አውራሪ የትግል ሚዲያ በመሆን የአማራ ሕዝብ እውነተኛ ድምጽ በመሆን ሲሰራ መቆየቱ፤ አሁንም በዚሁ ሕዝባዊ የትግል ዓላማ እንደፀና መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሚዲያችን፣ አማራ ለሕልውናው፣ ለክብሩና ለታሪኩ በጽናት በመፋለም ላይ በሚገኝበት በዚህ ታሪካዊ የትግል ምዕራፍ ውስጥ፣ የመረጃ ጦርነቱን በሀሳብ ከመምራት ባሻገር እውነተኛ የፋኖ አንድነት እንዲመጣ ስትራቴጂካዊ የድጋፍ ሚናውን ተወጥቷል፡፡ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ከፅንሰት እስከ ውልደት ድረስ በተጓዘባቸው አስቸጋሪ የምጥ ጊዜያት ሁሉ ሚዲያችን ትልቅ አሻራውን አሳርፏል፡፡ ንቅናቄውን በሀሳብ በመፍጠር፣ ከምስረታ ጊዜው በኋላም ተቋማዊ የትግል አመራር እንዲኖረው በቀና አስተያየት፣ በሰላ ትችት ያላሰለሰ ድጋፍ ስናደርግ ቆይተናል፡፡ አሁንም በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ ሆኖም በንቅናቄው ውስጥ መላ ሰራዊቱና አብዛኛው አመራር በማያውቀው ሁኔታ፣ በተለይም ሁለት የንቅናቄው አመራሮች ከኦህዴድ ብልጽግና ለይተን ከማናየው ከአማራ ታሪካዊ ጠላት ህውሃት ጋር ያልተቀደሰ ጋብቻ ለመፍጠር የሚያደርጉት የመጋረጃ ጀርባ ሩጫ፣ በህልውና ትግሉ ላይ አደጋ የጋረጠ መሆኑን በመረጃና በማስረጃ በማስደገፍ በተከታታይ የፕሮግራም ሽፋን ሰራዊቱን፣ አመራሩንና አጠቃላይ የአማራ ሕዝብን የማንቃት ስራዎችን መስራታችን ያስደነገጣቸው ጥገኛ ኃይሎች፣ በአማራ ፋኖ ማሊያ የሚሰሩ የጽምዶ ጋዜጠኞች፣ የሚዲያ ዘመቻ ከፍተውብን ተመልክተናል፡፡ ግሎባል ፋኖ ሚዲያ በምስረታ ዓላማው፣ አርበኝነት ውርሳችን፤ ታሪካዊነት ትርፋችን ነው በሚል እምነት፣ በአማራ ትግል ውስጥ ከፍተኛ ዋጋ ሲከፍሉ በቆዩ የሕዝብ ልጆች የሚመራ እንደመሆኑ መጠን፤ ሚዲያው በአማራ ሕዝብ ስትራቴጂካዊ ጥቅሞች ላይ አይደራደርም፡፡ ጠላቶቻችን ኦህዴድና ህውሃት የአማራ ታሪካዊ ርስቶችን በመውረር፣ ህዝባችን በማጥፋት የራሳቸውን አገር አልያም የበላይ ሆነው የሚገዟትን ኢትዮጵያ ለመፍጠር የከፈቱትን ጥቃት የማጋለጥ፣ ሕዝብን የማንቃትና የሚበጀውን የትግል አቅጣጫ የመስጠት ኃላፊነታችንን እንወጣለን፡፡ በተለይም የአማራ ሕዝብ ሲዋደቅላቸው የኖረው ራያ፣ ኮረም፣ ወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ታሪካዊ ርስቶቻችን ልክ እንደ አዲስ አበባ የትግል ግባችን አካል ናቸው፡፡ በምንም መመዘኛ፣ በሁኔታዎች የማይቀያየሩ፣ ቋሚና ዘላቂ የማንነት እና የክብር ጉዳይ ናቸው ብለን እናምናለን፡፡ እነዚህ ታሪካዊ የአማራ ርስቶች ላይ የያዝነው የፀና አቋም፣ ሠራዊቱን፣ አመራሩን እና አጠቃላይ ሕዝባችንን ለማንቃት የሰራናቸው ፕሮግራሞች የጽምዶ አጋፋሪዎችን እንዳስቆጣ፤ የህውሃት አለቆቻቸውን ትዕዛዝ የቀለበሰ እንደሆነ ሳይበሩ ላይ ባለው ጩኽት ገምግመናል፡፡ የጽምዶ ጋዜጠኞች የከፈቱት "የሥም ማጥፋት ዘመቻ" ንቀን ብንተወውም አሁን ግን በታሪካዊው እና የሰማዕታት የደም አሻራ ባረፈበት ዕዛችን ስም መግለጫ መውጣቱን በከፍተኛ ትዝብት ተመልክተነዋል፡፡ አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ፣ በጀግና ሰራዊት የተሞላ፣ በከፍተኛ ወታደራዊ ሳይንስ አዋቂ የጦር መኮንኖች የሚመራ የህልውና ትግሉ ፍሬ እንደሆነ እናምናለን፡፡ ከመሰረቱ ጀምሮ የምስራቅ አማራ ፋኖ ከጸረ-አማራው ህውሃት ጋር በተደረገው የህልውና ትግል ከማንም በላይ በርካታ ጀግኖቹን የሰዋ የሰማዕታት የትግል አደራ ያረፈበት ዕዛችን ነው፡፡ ራያን ጨምሮ በወሎ ቤተ አማራ፣ ሸዋና ጎንደር መሬት ላይ የምስራቅ አማራ ፋኖ ተዘዋውሮ በመዋጋት በጸረ-ህውሃት ትግል በየቦታው መስዋዕትነት ተቀብሏል፡፡ ከጎጃም፣ ጎንደርና ሸዋ ወንድም እህቶቹ ጋር በጋራ ተቀብሯል፡፡ በዚህ ተቋም ስም የሰማዕታትን የትግል አደራ የሸጡ ጥቂት ባንዳዎች የግሎባል ፋኖ ሚዲያ ስም መነሳቱ አሳዝኖናል፡፡ በመሆኑም፡- 1. ዕዛችን አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ከእናት ድርጅቱ ጋር ሆኖ የአማራን የህልውና ትግል በድል እንዲወጣ የሀሳብ ትግል ድጋፋችንን ከወትሮው በላቀ ሁኔታ አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡ በተለይም የሰማዕታቱን የትግል አደራ፣ የአማራ ሕዝብን ስትራቴጂካዊ ጥቅሞች ከመላ ሰራዊቱና እውነተኛ አመራሮች ጋር በመሆን ታሪካዊ ኃላፊነታችንን መወጣት እንደምንቀጥን ስናረጋግጥ፣ ከታሪካዊ ጠላቶች በኩል የሚሸረቡ ሴራዎችንና ከመጋረጃው ጀርባ ሕዝብ፣ መላው ሰራዊትና አብዛኛው አመራር በማያውቀው ሁኔታ የሚሰሩ የጽምዶ ሸፍጦችን በማጋለጥ አማራዊ ግዴታችንን መወጣት እንደምንቀጥል በድጋሚ እናረጋግጣለን፡፡ 2. የትግላችን ውጤት የሆነው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ የአማራ ሕዝብን ታሪካዊ የትግል አደራ የተሸከመ በመሆኑ በሀሳብ ትግሉ፣ በመረጃ ጦርነቱ፣ በድርጅታዊ መርህ እና አቅጣጫ እስከ ቀራኒዮ አብረን ከተቋሙ ጋር እንዘልቃለን። ሆኖም ንቅናቄው በትብብር ጉዳዮች ላይ ያለውን አቋም ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ እየጠየቅን፣ ከፖሊት ቢሮ አመራሩ ዕውቅና ውጭ ከመጋረጃው ጀርባ ሁለት ግለሰቦች የሚያደርጉት ያልቀደሰ የጽምዶ ጋብቻ በአደባባይ ሊወገዝና አቋም ሊያዝበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን እናስገነዝባለን፡፡ ይህ ሲሆን የወሰንና ማንነት ጉዳዮች የአማራ ሕዝብ የዕጣ ፈንታው ወሳኝ ጉዳዮች በመሆናቸው በህልውና ትግሉ ሂደት ቀይ መስመር ሆነው የሚታዩ መሆናቸውን የሚዲያችን አቋም ብቻ ሳይሆን የመላው ሕዝባችን አቋም እንደሆነ በማስገንዘብ ነው፡፡ 3. በአማራ የህልውና ትግል ዙሪያ የምትሰሩ እውነተኛ ሚዲያዎች፡- የአማራ ፋኖ የተነሳለትን ዓላማ ሳይስት፣ የየትኛውም አጀንዳ ጥገኛ ሳይሆን በራስ አቅም አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ እውነተኛ ትግል እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ እውነተኛ ትግል የሚጀምረው፣ የጽምዶ ጋዜጠኞችን ከፍረጃ በራቀ፣ በመረጃና በማስረጃ ወደእውነተኛው ትግል እንዲመለሱ በሀሳብ በመታገል፣ እውነታውን ለሕዝብ በማሳወቅ ነው፡፡ እናም ከእውነት እና ከአማራ ሕዝብ ጎን እንድትቆሙ የተቋማዊ አጋርነት ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ 4. የአማራ የህልውና ትግል ዋና የሀሳብና የፋይናንስ የድጋፍ መሰረት የሆናችሁ ዲያስፖራ ወገኖቻችን፣ ማኅበራትና ልዩ ልዩ አደራጃጀቶች በሙሉ፡- ለዘመናት የደከማችሁለት እና ዋጋ ስትከፍሉለት የኖራችሁትን ትግል በተስፋ መቁረጥ ስሜት መተው የለባችሁም፡፡ ይልቁንም የፋኖ ትግል የቁማርተኞች ፍላጎት ማስፈፀሚያ ወይም ያልተጠና ጥምረት ደላሎች ጥገኛ እንዳይሆን፣ በውጭ አገር የሚኖሩ የጽምዶ ደላሎችን በሀሳብ ታገሏቸው። ከአፋብን በመሸሽ ሳይሆን በመቅረብ ንቅናቄው በራሱ እግር ቆሞ መስመሩን ጠብቆ እንዲጓዝ የበኩላችሁን የሀሳብ ትግል አዋጡ፡፡ ከእውነተኛ የትግል ሚዲያዎች ጎን በመቆም ድጋፋችሁን እንድትቀጥሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ 5. ለተከበርከው አማራ ሕዝብ፡- የዚህ ትግል ባለቤት አንተ ነህ፡፡ የትግሉ ባለቤት ሕዝብ፤ የትግሉ መሪዎች ደግሞ ከአብራክህ የወጡ ልጆችህ ናቸው፡፡ ሆኖም ይህንን ታሪካዊ የህልውና ትግል አንተን ማዕከል አድርጎ ዘላቂ ድሉ እንዲረጋገጥ፣ ያንተን ቀይ መስመር ለይቶ ማስመር ይጠይቃል፡፡ ትግሉ ከታሪካዊ ወዳጆችህ ጋር የትብብር አንድነት የሚደረግበት፣ ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር ደግሞ ፊት ለፊት ገጥመህ በክንድህ ህልውናህን የምታረጋግጥበት ነው፡፡
152
6
https://youtube.com/live/7Xtwm0i1QBs?feature=share
173
7
ይህን ጉዳይ በዝርዝር እንመለከታለን
ይህን ጉዳይ በዝርዝር እንመለከታለን
223
8
https://www.youtube.com/live/hgGzGfDZ1tU?si=q1K8hqQzVQr64al4
242
9
https://vt.tiktok.com/ZS9jXvgf19FLy-jUz5W/
262
10
https://www.facebook.com/61588697781877/posts/122107093233289926/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v
272
11
https://youtube.com/live/I0rSJ4dvN0A?feature=share
320
12
https://youtube.com/live/0QQiZoZaJFw?feature=share
333
13
https://youtube.com/live/XAXNXqoSyxk?feature=share
329
14
https://www.facebook.com/share/v/1D7SKU2GjH/
286
15
ይች ነበልባል ጓዴ፣ በገንዛ ጓዶቿ ተከድታ እና መረጃ ተላልፎ ተሰጥቶባት ወህኒ የተወረወረችበት አቋማ አሁን ታያችሁ? ይችን የልጆች እናት ትዕንግርተ አምሓራዊት "ጣይቱ" እንደ ይሁዳ ለኦሮሙማ አሳልፋ
ይች ነበልባል ጓዴ፣ በገንዛ ጓዶቿ ተከድታ እና መረጃ ተላልፎ ተሰጥቶባት ወህኒ የተወረወረችበት አቋማ አሁን ታያችሁ? ይችን የልጆች እናት ትዕንግርተ አምሓራዊት "ጣይቱ" እንደ ይሁዳ ለኦሮሙማ አሳልፋችሁ ሰጥታችኋት ሾልካችሁ ካምፖላ እና በምናቀው ስፍራ የሰረጋችሁ ሁሉ… የተሰነደው ገመናችሁ ይገለጥ ዘንድ ሳንደክም እየሰራን ነው። ጊዜ ለኩሉ…… https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418 ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ሞዐ ሚዲያ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ https://t.me/moaamediaamharawi              
277
16
ሰበር-መረጃ‼️ የኢራን ሰላም ስምምነት ነገ ይፈረማል - ትራምፕ። ስምምነቱ እንደተፈረመ የሆርሙዝ ስርጥ ወዲያውኒ ሙሉ ለሙሉ ይከፈታል ብለዋል። ነገሮች ሲረጋጉ አሜሪካ ወደ ኢራን ገብታ ለኑክሌር የበ
ሰበር-መረጃ‼️ የኢራን ሰላም ስምምነት ነገ ይፈረማል - ትራምፕ። ስምምነቱ እንደተፈረመ የሆርሙዝ ስርጥ ወዲያውኒ ሙሉ ለሙሉ ይከፈታል ብለዋል። ነገሮች ሲረጋጉ አሜሪካ ወደ ኢራን ገብታ ለኑክሌር የበለፀገውን የዩራኒየም አቧራ እንወስዳለን ብለዋል። ከኢራን ጋር አሁን ላይ የተሻለ ግንኙነት አለን ያሉ ሲሆን ከመሬት በታች ምሽግ ደርማሽ ቦንብ በመጣል የሚታወቀውን የአሜሪካ B-2 የጦር አውሮፕላን አመስግነዋል። ነገ የኢራን እና የአሜሪካ አመራሮች በመይነመረብ ስብሰባ ያደርጋሉ፣ፊርማው ኤሌክትሮኒካሊ ይፈረማል። ኢራን አልስማማም ካለች ይህን እድል መቼም እንደማታገኘው አስጠንቅቀዋል። https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418 ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ሞዐ ሚዲያ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ https://t.me/moaamediaamharawi              
180
17
በአርሲ እገታ ተፈፀመ‼️ በዛሬው ዕለት ሰኔ 5/2018 ዓ.ም ጠዋት በምስራቅ አርሲ ከአቦምሳ ከተማ ወደ አስኮ እየመጣ ያለ አንድ ቅጥቅጥ የህዝብ ማመላለሻ ሙሉ ተሳፋሪዎችን ከቀኑ 6:00 ላይ ባለፈው
በአርሲ እገታ ተፈፀመ‼️ በዛሬው ዕለት ሰኔ 5/2018 ዓ.ም  ጠዋት በምስራቅ አርሲ ከአቦምሳ ከተማ ወደ አስኮ እየመጣ ያለ አንድ ቅጥቅጥ የህዝብ ማመላለሻ ሙሉ ተሳፋሪዎችን ከቀኑ 6:00 ላይ ባለፈው ጥቃት የፈፀሙት በኦህዴድ የተደራጁ የሸኔ ታጣቂዎች በሚል በልማድ የሚጠሩ እግተዉ ይዘው መሄዳቸውን የአካባቢው የአይን እማኞች ገልፀዋል። https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418 ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ሞዐ ሚዲያ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ https://t.me/moaamediaamharawi              
172
18
አድዋ መታሰቢያ በአሜሪካ ‼️ የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ‼️ #በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአ
አድዋ መታሰቢያ በአሜሪካ ‼️ የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ‼️ #በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ። ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው። በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል። ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው። ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው። ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው። https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418 ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ሞዐ ሚዲያ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ https://t.me/moaamediaamharawi              
144
19
“አሜሪካ እና እስራኤል በዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ላይ በተለየ መልኩ ተፅዕኖ እያሳደሩ ነው” — አልጄሪያዊ ተመራማሪ አሜሪካ እና እስራኤል “በጋዛ ለተፈጸሙ ወንጀሎች” የቀረበባቸውን ክስ መታ
“አሜሪካ እና እስራኤል በዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ላይ በተለየ መልኩ ተፅዕኖ እያሳደሩ ነው” — አልጄሪያዊ ተመራማሪ አሜሪካ እና እስራኤል “በጋዛ ለተፈጸሙ ወንጀሎች” የቀረበባቸውን ክስ መታገስ እንዳልቻሉ የፖለቲካ ሶሺዮሎጂ ተመራማሪው አህመድ ሩአጂያ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል። ተመራማሪው አፅንኦት ሰጥተው እንደተናገሩት፤ የፍርድ ቤቱ ዋና ዓቃቤ ሕግ ካሪም ኻን ከኃላፊነታቸው የታገዱት በዋሽንግተን እና በቴል አቪቭ “በተቀነባበረ ሴራ” ነው። “ለእነሱ ዓለም አቀፍ ሕግ መተግበር ያለበት በደሃ እና በተበዳዮች ላይ ብቻ እንጂ፤ በጥቃት አድራሾች ላይ አይደለም” ብለዋል። ካሪም ኻን የቀረበባቸውን የፆታዊ ሥነ-ምግባር ጉድለት ክስ ተከትሎ ከኃላፊነታቸው መታገዳቸው ይታወሳል። https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418 ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ሞዐ ሚዲያ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ https://t.me/moaamediaamharawi              
148
20
ከእርድ የተረፉ የአርሲ አሰኮ ኦርቶዶክሳውያን እና አምሓሮች ድምፅ ትርጉም፦ ".....በ13/09/2018 ዘበነ አበበ የሚባል ሰው ገድለውብናል።አሁን የተቃጠለው  ቤተ እምነት የክርስቲያኖች ቤተ ክርስቲያን  ብቻ ነው። በከተማችን የሙስሊም እምነት ተከታይ ሆኖ የመንግስት ሚሊሻ የሆነ ሰው ቤት ራሱ አልተቃጠለም፣ ጠላትነታቸው ከመንግስት ታጣቂ ሳይሆን ከኦርቶዶስ ክርስቲያኑ እና አምሓራ ተወላጅ ከሆነ ብቻ ነው። ማነው ቤተ ክርስቲያናችንና ቤታችን እንዲቃጠል ያደረገው ? በግንቦት 23 ብዙ የክርስቲያን ቤቶች እኮ ነው የተቃጠሉት። ቤቶቻችን ከቃጠሎ እንዳይተርፉ  "አርባ ቀላ "ላይ የአስተዳድር ሰዎች ለመንግስት ወታደሮች በሬ አርደው በመቀለብ ወደ እኛ መጥተው እንዳይከላከሉ እንዳይንቀሳቀሱ ነው ያደረጉት። ቃጠሎው ከተፈጸመ አላማቸው ከተሳካ በኋላ ነው ወደ ስፍራው እንዲንቀሳቀሱ የተደረገው። ትልቁ የጥፋት እጅ ያለው የመንግሥት አስተዳድር አካላት ጋር ነው። ሸኔ(የወሀቢያ ቡድን) እኛን ሊያጠፋ ከቤቱ ወጥቶ ጫካ ገብቷል። አሁንም ሸኔ(የወሀቢያው ቡድን) ብቻ አይደለም እየዘረፈን ያለው። የሙስሊም ሴቶችም ጭምር ናቸው ተከትለው ሰፈራችንን በመውረር ሀብታችንን የዘረፉት። ሙሉውን በተጎራባች ዞን የሚኖር የሙስሊም ማኅበረሰብ ነው ያዘመቱብን። እኔ ቀበሌው ምክትል አስተዳደር ስለነበርሁ በተማፅኖ እርዳታ ጠይቄ ነበር ለ 26 ሰው  ብቻ  የሚሆን ነበር የተሰጠኝ። ተሰደው በሌላ አከባቢ ላይ  አሉኮ  እነርሱስ ለምን አይመዘገቡም በጥቃቱ ምክንያት አይደል የተሰደዱት? ስላቸው   እኛ ለእነርሱ የሚሆን ዕርዳታ የለንም እነርሱኮ ሊወጉን ነው የተሰደዱት አሉኝ። ማን  ማንን ይወጋል፣ ከሞት ለማምለጥ የተሰደደውን መንግስት እንደሽፍታ ቆጥሯል አከባቢ የሚመራው በመንግሥት አይደለም ወይ? ዛሬም ሆነ ነገ በሥልጣን ላይ ያሉ ሰዎች ሊያስጨርሱን የተነሱ  ናቸው እንጂ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያስቡ አይደሉም። ከወረዳው አስተዳደር ጀምሮ እስከ ዞን አስተዳደር ድረስ ያሉት ያው አንድ ናቸው። አሁን  የተቃጠሉ ቤቶቻችሁን እና የወደመውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራላችኋለን አሉን  በፊት ሁለት ሰው ነው የሞተው ቤተ ክርስቲያኑም አልተቃጠለም እያሉ  ስልክ እየደወሉ ሲረብሹን ነው የቆዩት ።እኛም እውነታውን ለማስረዳት ብዙ ጊዜ ስንደውልላቸው አንሰማም ነው ያሉት። አሁንም የተቃጠሉ ቤቶቻችን ቢሠሩ የተቃጠለው ቤተ ክርስቲያ ቢታነጽ እኛ ወደ ቀዬአችን መመለስ የምንችለው፦አንደኛ፦ የኦሮሚያ ክልልዊ መንግሥትና የፌዴራል የአራጁ ቡድን(ሸኔ)ሴል ሆነው የሚያስጠፉንን ሰዎች ከመዋቅሩ ማጽዳት አለበት፣ አሊያ ጉዳዩ ላይ እነርሱም አሉ። ሁለተኛ ታጥቆ ጫካ ያለውን ጠላት ከአከባቢው አጽድቶ ሰላም የሰፈነበት አከባቢ ሲያደርገው ነው። አከባቢው ሰላም ሳይሆን እኛ እዚያ ተመልሰን እንድንኖር ነው ቤት የሚሠራው? ቤተ ክርስቲያን የሚታነጸው?። ይኽ ጠላት  መያዝ አለበት በ መዋቅር   ውስጥ ያለውም ጠላት ይጋለጥ።እኛ ሦስት ጠላት ነው ያስቸገረን ፦አንደኛው ጠላት  በጫካ ያለው ነው ሁለተኛው ጠላት በማኅበረሰብ ውስጥ ያለው ሦስተኛው ጠላት በመንግሥት መዋቅር ውስጥ  ያለው ከላይ እስከታች ስልጣን የጨበጠ ጠላት ነው" https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418 ሰኔ 6/2018 ዓ.ም ሞዐ ሚዲያ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ https://t.me/moaamediaamharawi              
164